የሥራና ክህሎት ቢሮ-ድሬዳዋ

የሥራና ክህሎት ቢሮ-ድሬዳዋ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ

ጳጉሜን 2  የማንሰራራት ቀን
07/09/2026

ጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን

06/09/2026
05/09/2026

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዘመኑን የሚመጥን እና በሙያ ክህሎቱ ብቁ የሆነ ዜጋን ከማፍራት ባሻገር ወጣቶችን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት ለማሸጋገር በመስራት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ።

©️ DireTv

ድሬዳዋ በሥራና ክህሎት ዘርፍ ላስመዘገበችው ውጤት የዋንጫ ተሸላሚ ሆነች፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሰኞ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የቆየው የአም...
04/09/2026

ድሬዳዋ በሥራና ክህሎት ዘርፍ ላስመዘገበችው ውጤት የዋንጫ ተሸላሚ ሆነች፤

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሰኞ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የቆየው የአምስት ዓመታት የልማት ጉዞ የምክክር መድረክ ለዘርፉ ዕድገት አስተዋጽዖ ላበረከቱ ተጠሪ ተቋማት፣ የክልል አስፈጻሚ አካላት፣ ስኪል ኢትዮጵያና ኢንተርፕራይዞች ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።

በመድረኩ የአምስት ዓመቱ የልማት ጉዞ ዋና ዋና ውጤቶች፣ ተሞክሮዎች፣ ተግዳሮቶችና ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎች በስፋት የተገመገሙ ሲሆን፣ ለዘርፉ ዕድገት የላቀ አስተዋጽዖ ያበረከቱ ተቋማትና ባለድርሻ አካላትም ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

አማራ ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ድሬዳዋ አስተዳደር፣ ኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች፣ ድሬዳዋ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

በዚህ የዕውቅናና የሽልማት መርሐ ግብር የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በዘርፉ ባስመዘገበው ውጤት የዋንጫ ተሸላሚ በመሆኑ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የተገኘው ዋንጫ በአምስት ዓመቱ የልማት ጉዞ የተመዘገቡ ውጤቶችን ከማመስገን ባለፈ፣ በድሬዳዋ የሥራና ክህሎት ዘርፍ ለተከናወኑ የተቋማዊ ለውጥ፣ የክህሎት ልማት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራና የሥራ ዓለም ትስስር ሥራዎች የተሰጠ ዕውቅና መሆኑ ገልጸዋል።

አቶ ሮቤል ጌታቸው የተገኘውን ውጤት እንደ ተቋማዊ ስኬት በመቀበል፣ የተጀመሩ የለውጥ ሥራዎችን በማጠናከርና የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ለቀጣይ የልማት ዘመን በበለጠ ቁርጠኝነት ለመሥራት የሚያነሳሳ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሥራና ክህሎት ቢሮ ሕዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ

03/09/2026
03/09/2026
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናን ለገጠሩ ማህበረሰብ በፍትሃዊና ተደራሽ መልኩ ለማድረስ በ2019 የሥልጠና ዘመን ተንቀሳቃሽ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ለመተግበር መዘጋጀቱ ተገለጸ።ተንቀሳቃሽ ሥልጠናው ‹...
02/09/2026

የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናን ለገጠሩ ማህበረሰብ በፍትሃዊና ተደራሽ መልኩ ለማድረስ በ2019 የሥልጠና ዘመን ተንቀሳቃሽ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ለመተግበር መዘጋጀቱ ተገለጸ።

ተንቀሳቃሽ ሥልጠናው ‹‹ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ለገጠሩ ማህበረሰብ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት›› በሚል መሪ ቃል የሚተገበር ሲሆን፣ ዓላማውም በገጠር የሚኖሩ ማህበረሰቦች ከቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማስቻል የምርትና ምርታማነት አቅማቸውን ማሳደግ ነው።

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኤጀንሲ ከግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ የግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ሥልጠናውን በድሬዳዋ በሚገኙ ሁለት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች አማካኝነት ለማስፈጸም አቅጣጫ ተይዟል።

በዚህም በግብርና፣ ከግብርና ውጪ በሆኑ ዘርፎች እና በገጠር ቴክኖሎጂ ልማት ላይ ያተኮሩ ሥልጠናዎችን ወደ ገጠር ማህበረሰቡ በማድረስ፣ በሥራ ላይ ያሉና ከዋና ሥራቸው ውጪ በሆኑ የሥልጠና ዘርፎች ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸውን 4,000 አርሶ አርብቶ አደሮች በማብቃት ምርትና ምርታማነትን ማሻሻል ታስቧል።

ይህንንም አስመልክቶ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ የገጠሩ ማህበረሰብ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ሥልጠናን ከተግባራዊ ቴክኖሎጂ ጋር ማጣመር እና የሥልጠና ይዘትን ከአካባቢው ትክክለኛ ፍላጎትና የገበያ አቅጣጫ ጋር ማስማማት ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም ሥልጠና በኮሌጅ ግቢ ብቻ የሚሰጥ አለመሆኑን የሚያረጋግጥ ሲሆን አሰልጣኞችና የሥልጠና ግብዓቶች ወደ ገጠር የሥልጠና ቦታዎች በመንቀሳቀስ ማህበረሰቡ በሚገኝበት አካባቢ ሥልጠና እንዲያገኝ የሚያስችል አተገባበር ይከተላል።

የአተገባበሩ ዋና ዋና እርምጃዎች

* የገበያ ተኮር አጫጭር ሥልጠና ፍላጎት ዳሰሳ ማካሄድ፤
* ተገቢ የሥልጠና ቦታዎችን ማመቻቸትና ለሥልጠና የሚስማማ ጥበቃ ማድረግ፤
* አሰልጣኞችንና የሥልጠና ግብዓቶችን ከኮሌጆች ወደ ገጠር ማንቀሳቀስ፤
* ለማህበረሰቡ በቂ ግንዛቤ መፍጠር፤
* ሰልጣኞችን መመልመልና በፍላጎታቸው መሠረት ወደ ሥልጠና ማቅረብ፤
* አንገብጋቢ የልማት ችግሮችን በመለየት በሥልጠናና በቴክኖሎጂ አማራጮች መፍትሔ ማመቻቸት፤
* ተግባራዊ ሥልጠና መስጠት፤
* የሥልጠና ተጠቃሚዎችን በድጋፍና በክትትል ማጠናከር፤
* የሙያ ብቃት ምዘና ማከናወን።

በመሆኑም ተንቀሳቃሽ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናው የሥልጠና አገልግሎትን ከከተማ ወደ ገጠር በማስፋፋት የተደራሽነት ክፍተትን ለማጥበብ፣ የገጠር ማህበረሰብን በተግባራዊ ክህሎት ለማብቃት እና ሥልጠናን ከአካባቢያዊ የልማት ችግሮች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ የኢኮኖሚና የኑሮ ለውጥ ለማምጣት የሚያግዝ ተግባራዊ የክህሎት ልማት አቅጣጫ መሆኑ በቢሮው የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ተጠቁሟል።

“ሥልጠና ወደ ማህበረሰቡ፤ ክህሎት ወደ ምርት፤ ሙያ ወደ ልማት!”

የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ‹‹ብቃት›› የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ 4ኛ ዙር አተገባበርን በተሳካና በተቀናጀ መልኩ ለማስፈጸም ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።መድረኩ ...
02/09/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ‹‹ብቃት›› የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ 4ኛ ዙር አተገባበርን በተሳካና በተቀናጀ መልኩ ለማስፈጸም ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።

መድረኩ የተዘጋጀው በ4ኛ ዙር የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም አፈጻጸም ላይ የሚሳተፉ የተለያዩ ኮሚቴ አባላትና ባለድርሻ አካላት ስለፕሮግራሙ ዓላማ፣ አፈጻጸምና የተሳትፎ ሚና የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል ነው።

በመድረኩ የ4ኛ ዙር የሥራ ላይ ልምምድ አተገባበር ሂደት፣ የተሳታፊዎችና የባለድርሻ አካላት ሚናና ኃላፊነት፣ የአፈጻጸም ቅንጅትና ክትትል ጉዳዮች ላይ ውይይትና ግንዛቤ ማስጨበጫ ተካሂዷል።

የወጣቶችን የሥራ ዓለም ተሞክሮ ለማሳደግ፣ የተግባር ክህሎታቸውን ለማጎልበትና ከሥራ ዓለም ጋር ያላቸውን ትስስር ለማጠናከር የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የሚኖረው ሚና ከፍተኛ መሆኑ በመድረኩ ተጠቁሟል።

በተለይም የፕሮግራሙ ውጤታማነት በአንድ ተቋም ብቻ የሚረጋገጥ ሳይሆን፣ የተለያዩ ኮሚቴዎችና ባለድርሻ አካላት በጋራ አቅጣጫ፣ በግልጽ ኃላፊነትና በተቀናጀ አፈጻጸም መሥራታቸው ወሳኝ መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል።

በመድረኩ ተሳታፊዎች ጥያቄዎችን አንስተው ምላሽ የተሰጠባቸው ሲሆን የተካሄደው የጋራ ግንዛቤ ማስጨበጫና ውይይት የ4ኛ ዙር የ‹‹ብቃት›› የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ አፈጻጸምን ይበልጥ ተቀናጅቶ፣ ተጠያቂነት ባለውና ውጤት ተኮር በሆነ መልኩ ለማስፈጸም መሠረት ያስቀምጣል።

የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ፤ ከሥራ ፈላጊነት ወደ ሥራ ዓለም የሚያሻግር የብቃት ድልድይ!

የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

02/09/2026
“አዲሱ የዘርፉን ዕሳቤ ተግባራዊ በማድረግ ለተቋማዊ ውጤታማነት መሠረት መጣል ችለናል።”— አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊአቶ ሮቤል ባለፉት አምስት አመታት ...
02/09/2026

“አዲሱ የዘርፉን ዕሳቤ ተግባራዊ በማድረግ ለተቋማዊ ውጤታማነት መሠረት መጣል ችለናል።”
— አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ

አቶ ሮቤል ባለፉት አምስት አመታት በዘርፉ አስተዳደሩ ላይ የተሰሩ ስራዎችን በሥራና ክህሎት ሚንስቴር በተዘጋጀው የአምስት አመት የልማት ጉዞ ቅኝት የፓናል ውይይት ላይ ፓናሊስት ሆነው ቀርበው በሰፊው አብራርተዋል።

በዚህም የሥራና ክህሎት ዘርፍ የፖሊሲና የተቋማዊ ዕሳቤ ለውጦችን ከሰነድ ወደ ተግባር፣ ከአሠራር ወደ ውጤት በመተርጎም የተሻለ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት እየተሠራ እንደሆነ፤

የድሬዳዋ ሥራና ክህሎት ቢሮ ይህንን የለውጥ አቅጣጫ በተግባር በመተርጎም፣ የአደረጃጀት ወጥነትን በማረጋገጥ፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ አሠራሮችን በመዘርጋት፣ የሕግ ማዕቀፎችን በማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማስፋፋትና የሰው ሀብት አቅምን በማጎልበት የተቋማዊ ለውጥ ሥራዎችን እያጠናከረ እንደሚገኝ፤

እነዚህ ለውጦች የሥራ ሂደቶችን በተቀናጀ መልኩ ለመምራት፣ የተቋማትን ተጠያቂነትና ቅንጅት ለማሳደግ፣ የሰው ኃይልን አቅም ለማሳደግና ለተገልጋዮች የተሻለ አገልግሎት ለማቅረብ ጠንካራ መሠረት እንደሚፈጥሩ፤

በአምስት ዓመቱ የዘርፉ የልማት ጉዞ የተገኙ ልምዶችን በመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫዎችን በመለየት፣ የተጀመሩ ለውጦችን የበለጠ ማጠናከር የዘርፉን ተቋማዊ አቅምና ውጤታማነት ወደ ቀጣይ ደረጃ ለማሸጋገር ወሳኝ ነው ብለዋል።

“ለውጥ የሚለካው በዕሳቤ ብቻ ሳይሆን፣ በተግባር በሚመዘገብ ውጤት ነው።”

የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

Address

Close By Triangle Hotel
Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሥራና ክህሎት ቢሮ-ድሬዳዋ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share