Freedom and equality party -Dire Dawa

Freedom and equality party -Dire Dawa እኩልነት በተግባር

የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን ያበርክት!! የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሀምሌ 8፣ 2018 በይፋ መጀመሩ ይታወሳሉ። ሀገራዊ ምክክሩ ቀደም ሲል በተመረጡ እና በስምንት አን...
12/08/2026

የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን ያበርክት!!

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሀምሌ 8፣ 2018 በይፋ መጀመሩ ይታወሳሉ። ሀገራዊ ምክክሩ ቀደም ሲል በተመረጡ እና በስምንት አንጓዎች በተደራጁ አጀንዳዎች ዙሪያ ከተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እና የማህበረሰብ ክፍሎች በተወከሉ በሺህ የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች እየተካሄደ እንደሚገኝ የሂደቱ አስተባባሪ የሆነው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል።

ምክክሩ ቀደም ሲል በተነደፈ የውይይት ስርዓት መሰረት በመካሄድ ላይ እንድሚገኝ እና ባለፉት ጥቂት ቀናት በአጀንዳዎች ላይ ምክክር በማካሄድ የተወሰኑት የስራ ቡድኖች ውይይታቸውን ማገባደድ መጀመራቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሀገራዊ ምክክሩ በንቃት በመሳተፍ ላይ ይገኛል።

በሀገራችን ለረዢም ጊዜ የልዩነት እና የግጭት ምንጭ ሆነው በቆዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሚደረግ ምክክር እጅግ አከራካሪ እና አጨቃጫቂ ሊሆን እንደሚችል ይጠበቃል። በሀገራዊ ምክክሩ ውይይት እየተደረገባቸው የሚገኙ አጀንዳዎች፡ የማንነት ጉዳይ፣ የአስተዳደር ወሰን፣ የእኩል ተሳታፊነት እና እኩል ተጠቃሚነት፣ የታሪክ እና ትርክት ጉዳዮች፣ ሀገራዊ ምልክቶች እና መገለጫዎች፣ የከተሞች አስተዳደር፣ ቋንቋ፣ የህዝብ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት እና ሌሎች እጅግ መሰረታዊ ጉዳዮች ሰፊ የሀሳብ ልዩነት እና ፍጭት ሊያስከትሉ የሚችሉ ናቸው። በእነዚህ አጀንዳዎች ዙሪያ ስምምነት ላይ መድረስ አልጋ በአልጋ እንደማይሆን መገመት ይቻላል።

በታሪካዊም ሆነ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያየ እይታ፣ አስተሳሰብ፣ ፍላጎት፣ የታሪክ ግንዛቤ፣ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ወዘተ ያላቸው ግለሰቦች፣ ቡድኖች፣ የፖለቲካ ኃይሎች በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ያላቸውን አስተሳሰብ በማቀራረብ፣ ሁሉንም አሸናፊ ሊያደርጉ በሚችሉ ምክረ ሀሳቦች ላይ ለመድረስ ከፍተኛ ትእግስት፣ ጥበብ እና ኃላፊነት ይጠይቃል። በተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ሀገራችንን ካለችበት ውስብስብ ችግሮች አላቆ የተሻለ ሰላም እና እድገት የተረጋገጠባት ሀገር ለመፍጠር ከራስ እና ከራስ ቡድን ፍላጎት በላይ ሀገርን እና ህዝብን ያስቀደመ እይታ፣ ዝግጅት እና ቅንነት ያስፈልጋል።

ባለፈት ጥቂት ሳምንታት በሁሉም አጀንዳዎች ዙሪያ እየተደረጉ ያሉ ውይይቶች ከሞላ ጎደል በመግባባት እና በሰላማዊ ሁኔታ በመካሄድ ላይ መሆናቸው ተስፋ የሚሰጥ ቢሆንም፣ አልፎ አልፎ የምክክር ሂደቱን ሊያውኩ የሚችሉ አካሄዶች እና ፍላጎቶች ሲከሰቱ ይስተዋላል። ሀገራዊ ምክክሩ ዓላማውን በትክክል ያሳካ ዘንድ ሂደቱ ሳይንሳዊ በሆነ የምክክር ስነ ዘዴ፣ ገለልተኛ እና አካታች በሆነ መልኩ ሊካሄድ ይገባል።

በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የምክክር ሂደቱ ተሳታፊዎችም ሆነ ከሂደቱ ውጪ ያሉ ባለድርሻ አካላት ሂደቱን በተመለከተ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ፣ የሚወስዱት አቋም እና የሚሰጡት አስተያየቶች በሀገራዊ ምክክሩ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ሊያሳድሩ እና ሂደቱ የታለመለትን ዓላማ እንዳይመታ ሊያደርጉ ይችላሉ። በአንድ ወይም በጥቂት አጀንዳዎች ዙሪያ በሚፈጠር አለመግባባት አጠቃላይ የምክክር ሂደቱ ቅርቃር (Deadlock) ውስጥ እንዲገባ በማድረግ ሀገራዊ ምክክሩ ዓላማውን እንዳያሳካ ምክንያት ሊሆኑ ይችላል።

በመሆኑም የተጀመረው ሀገራዊ ምክክሩ በመሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የቆዩ እና ጥልቅ አለመግባባቶችን ለመፍታት በሚያስችል ሁኔታ ይጠናቀቅ ዘንድ፣ የምክክሩ ቀጥተኛ ተሳታፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለሂደቱ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋጾ ሊያበረክቱ ይገባል። በምክክሩ የሚሳተፉ አካላት ይህ ታሪካዊ ሂደት በስኬት ይጠናቀቅ ዘንድ፣ ከራስ ፍላጎት ባሻገር የሌሎችን ፍላጎት እና ስጋት በቅጡ ለመረዳት፣ ለመደራደር እና የሌሎችን ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ መግባባት ላይ ለመድረስ ተነሳሽነት እና ቁርጠኝነት ማሳየት ይጠበቅባቸዋል።

የምክክር ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ የአንድ ወገን ፍላጎትን በሌሎች ላይ ለመጨን ከሚደረግ ሙከራ መራቅ፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በምክክር ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ከሚያደርጉ አፍራሽ ተግባራት መቆጠብ ያስፈልጋል።

የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር በሀገራችን ካሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች መካከል የተወሰኑትን ለመፍታት እና ቀሪ የሀሳብ ልዩነቶች በሂደት የሚፈቱበትን ልምድ እና ተግባራዊ ተሞክሮ ሰጥቶን እንደሚያልፍ ይጠበቃል። ነእፓ በሀገራችን አካታች ሀገራዊ ምክክር እንዲካሄድ ባለፉት ዓመታ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ እንደቆየው ሁሉ፣ የተጀመረው የምክክር ሂደት እንዲሳካ የበኩሉን አስተዋጾ እንደሚያደርግ በዚህ አጋጣሚ ያረጋግጣል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ነሀሴ 6፣ 2018

29/06/2026
" ሃሳባችን ብርታታችን፣ ተግባራችንም ንቃታችን ነው! "ይህ የነእፓ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ነው ፤      አሸናፊነትን፣ ኩራትን፣ ደስተኛነትን፣ ጥንካሬን በቀጣዩ ንግርት እናስመሰክራለን።     "...
28/06/2026

" ሃሳባችን ብርታታችን፣ ተግባራችንም ንቃታችን ነው! "ይህ የነእፓ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ነው ፤
አሸናፊነትን፣ ኩራትን፣ ደስተኛነትን፣ ጥንካሬን በቀጣዩ ንግርት እናስመሰክራለን።
" ሃሳብ ብርታት፣ ተግባራችንም ንቃታችን ነውና።
ህልምና አላማ ሰንቀን መድረስ የምገባን ሀገራዊ ግብ አለን፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ አማራጭ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴን በመከተል በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ አካባቢ ላይ ይሁኝታና ተቀባይነትን ለማግኘት በመሻት ታግሎ ቅቡልነት የማግኘት ድል በመጎናፅፍ አሸናፊነትን ጀምረናል፤መላው የነእፓ አባልና ደጋፊዎች ለሀገርና ህዝብ ተቆርቋሪነትን በመፍጠር ከመልካምና ከሰላም ጎራ እንድሰለፉ የማድረግና የማብቃት፤የሀገር ፍቅርና በአብሮነት የማሸነፍ ወኔ እንድፈጠር የማብቃት አሸናፊነት፣ለዚህም ነው ሀገራዊ ግብና ዓላማ ከመረጡት ከነእፓ በመላው ሀገሪቱ ካሉት ቅርንጫፎች ጋር በመሆን ከተጎናፀፍነዉ አሸናፊነት አንዱ ድል አለን የምንለው፤ለዚህ ነው የቻሉትን እየሞከሩ ፤የአቅማቸውን እየጣሩ በፍፁም ተስፋ ከማይቆርጡት ጋር በመሆን ለዛሬ ስንበቃ አሸናፊዎች ነን፤ ዛሬ ለነእፓ እንደ ሀገር ትልቅ ስኬት አለን የምንለው በውጤታማ ተግባራት የተሞላ የሀገራችን የዲሞክራሲ ግንባታ ምልክት ሆነን በትልቅ ቁመና ላይ ለመገኘት የበቃ ፓርቲ ነዉ ብለን አሸናፊነትን የምናበስረው።
ጊዜያችንን በአግባቡ በመጠቀም፣የምርጫ ሰሞን ፓርቲ ሳንሆን ከምርጫ በፊትና በሁዋላ የፓርቲ ስራን ትርጉም ባለው ሁኔታ በአደረጃጀት እስትራቴጂ በበመቀየስ ጭምር ለዛሬ የበቃ ፓርቲ ነው፤ይህ ሁሉ ሆኖ የስራ ፍሬ ውጤት የምለካው በቁጥር ስሌት ሳይሆን በተግባር ልኬት ላይ የሆነና የተሳካ ብዙ የማይቆጠሩ የአሸናፊነት ድል ተጎናፅፈናልና አሸንፈናል፤ ስኬቶቻችንን በጥቂት ግዜ ውስጥ መፍጠር ችለናል፤ በአቀድነው መንገድ መጓዝን በፍላጎት ተቀብለን፤ የምገጥሙንን በጎና መሰናክል ሁሉ እያሸነፍን ለዛሬ የበቃ ፓርቲ ለመባል በቅተናል፤ ለዚህም መመስገን የሚገባውን እያመሰገንን፣ መሸለም ያለበትን እራሳችንን በመሸለም ወደ ቀጣዩ የድል መዳረሻ ጉዞ ቀጥለናል።
" ሃሳብህ ብርታትህ ነው፣ ተግባርህም ንቃትህ ነው። " ያሰብናቸው ትላልቅ ሃሳቦች ምክንያት የሆነው በብርታታችን ነው፤ የንቃታችን ዋነኛው ሚስጥር ተግባራችን ነው፤ በሰራነው ስራ ተነቃቅተን፣ በድንቅ ሃሳቦቻችን ተበረታተናል፣ በትልቁ ህልማችን የምናግጥበትና የምንኮራበት ይሆናል።
ያለንበት ደረጃ ቀላል አይደለም፤ የፓርቲያችን የምርጫ ስትራቴጂ የሚያሳንስን አይደለም፤ከብርቱዎች ጎራ መመደብ፣ ከጠንካሮች ተርታ መሰለፍ፣ እለት እለት የተሻሉና የተዋቡ የአሸናፊነት ቀናትን መፍጠር ቀልድ አይደለም።
መሰጠትን፣ መስወዓትነትን፣ ትልቅ ጥረትን ይፈልጋልና ከጀመርነው መንገድ ፍንክች አንልም፤በፍፁም አንቆምም፤ከውጤታችን እኩል ሂደቱ፣ ጎዳናውም እንደሚያስፈልገን በብርታት በመጓዝ፤በንቃት በመራመድ አምነን የአሸናፊነት ጉዞ ቀጥለናል። በአሸናፊነት ሁሌም እንጠንክር!

ማንኛውም ድል ትግል የሚጠይቅ በመሆኑ የሚነሳው ከችግር እንጂ ልክ እንደ አበባና ቀስተደመና ከመሬት የሚነሳ አይደለም፡፡   ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የፓርቲ ቁመናን ለ...
18/06/2026

ማንኛውም ድል ትግል የሚጠይቅ በመሆኑ የሚነሳው ከችግር እንጂ ልክ እንደ አበባና ቀስተደመና ከመሬት የሚነሳ አይደለም፡፡
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የፓርቲ ቁመናን ለመያዝ ከአባላት ምልመላ ጀምሮ የፓርቲን አደረጃጀትን ለማጠናከር ጐን ለጐን፤ ተደራሽነቱን በመላው አገሪቱ ለማዳረስ የቅርንጫፍ ፅ/ቤቶችን በማቋቋም ጭምር በምያደርጋቸው እንቅስቃሴና ዘርፈ ብዙ የኢኮኖሚና ሎጀስቲክ ችግሮች ሁሉ ብዙ የትግል ውጣውረድ በጋራ ያለፈ፤አልፎና ተሻግሮ ለዛሬ ለፓርቲ ቁመና አመርቂ ውጤት ላይ የምገኝ ሀገራዊ የህዝብ ፓርቲ ፤ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ነው።
የትግል ሕይወት ሁልጊዜ በፅጌረዳ ያሸበረቀ ሊሆን አይችልም፤ ስቃይ አልባ የትግል ሕይወት ሊኖር የማይችል መሆኑን ተረድተን ስንቀበል ይሆናል በትግል ውስጥ የሚንገኘውና ፤ድሎችን መጎናፅፍ የምንችል መሆናችንን እያረጋገጥንና በቀጣይ ለመጎናፀፍም ጭምር ጉዞ ቀጥለናል፡፡
ይህ ስለ ቆራጥነት ወይም ጥርስን ስለመንከስ አይደለም፡፡ ይህ “ህመም ከሌለ ማግኘት የለም” የሚለው አይነት ሌላ ግሳፄ አይደለም፤ ይህ ትግላችን ስኬታችንን ይወስናል፤ችግሮቻችን የግቦቻችን ድል መፈጠሪያ ናቸው የሚል የሕይወት በጣም ቀላሉና መሰረታዊ አካል ነው፡፡
ይህ መጨረሻ የሌለው ቀጥ ብሎ የቆመ ጠመዝማዛ ብረት ነው፡፡ የሆነ ነጥብ ላይ መውጣት ማቆም እንደሚፈቀድልን ካሰብን፣ ነጥቡን ስተናል ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ደስታው ያለው በራሱ በመውጣቱ ላይ ነው፤ነእፓ መውጣቱን ይቀጥላል ።

የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ፤ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት መርህ ተግባራዊነት የምስራቅ ኮኮብ የነእፓ ድሬዳዋ ና ሶማሌ ክልል ቅርንጫፍና የዋና ፅ/ቤት የምርጫ አስተባባሪ ኮምቴና መላው አመራሮችና...
10/06/2026

የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ፤ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት መርህ ተግባራዊነት የምስራቅ ኮኮብ የነእፓ ድሬዳዋ ና ሶማሌ ክልል ቅርንጫፍና የዋና ፅ/ቤት የምርጫ አስተባባሪ ኮምቴና መላው አመራሮችና መላው አባሎቻችንና ደጋፊዎች የጋራ ድል ፤። የነእፓ ተቀዳሚ ልቀመንበር ዶ/ር አብዱልቃድር አደም የፖለቲካ ሰላማዊ የትግል ስልት እንጂ በመላተም እንዳልሆነ በተግባር ድል ያየንበት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነበር፤በስህተት የድላችን ፍሬ ያልሆነውን ለምርጫ ቦርድ አቅርበን እየተጠባበቅን ያለው ክስተቶች ብኖሩም እንኳን።
በድሬ ዳዋ ከተማ አስተዳደር ከቀረቡት አስር ፓርቲዎች ነእፓ የምርጫ ቦርድ አጠቃላይ ውጤት እስከምገለፅ ድረስ የተረጋገጠ በከተማ ወረዳዎች አራትና በገጠር ቀበሌዎች አምስት ጠቅላላ ዘጠኝ የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ትክክለኛ መረጃ አሸንፈናል።
የድሬ ዳዋ የነእፓ ሊቀመንበርና በባለቤቱ የብልፅግና አባል የሆኑ የአንድ ቤተስብ ባልና ሚስት ደግሞ የነእፓ የድሞክራሲ ምልክት ነፀብራቅ የሆነ የመነጋገርያ አጀንዳ ሆኖ አልፏል።
ድል ለኢትዮጵያ ፤ድል ለነእፓ!

27/05/2026
🖊️ ለኛ ድምቀት ስትል ራሷን ከኋላ አሰልፋ ወደፊት ስትገፋን የቆየች፤ከመላው ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽፈት ቤቶች የሚደርሷትን በተለይ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እጩዎች ምዝገባን ጨምሮ ...
26/05/2026

🖊️ ለኛ ድምቀት ስትል ራሷን ከኋላ አሰልፋ ወደፊት ስትገፋን የቆየች፤ከመላው ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽፈት ቤቶች የሚደርሷትን በተለይ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እጩዎች ምዝገባን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲው ጠቅላላ ስራዎችና ማንኛውንም አቤቱታና ሪፖርት ስትመራና ስትፈጽም የቆየችው፤ ብርቱ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት ኃላፊ ሌይላ አሊ ኑር ሁሴን፥ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ለክልል ምክር ቤት ዕጩ፤
🖊️ እጩ ሆነሽ በቀረብሽበት ባለድል ሆነሽ ለኛ ማበርከት የቻልሽውን ብቃትና ችሎታ ህዝብሽ መርጦሽ የአገልጋይነት ችሎታሽን ዳግም የምናይሽ እንደምሆን ጥርጥር የለንም።
🖊️ 🖊️ ብዕርን እንምረጥ 🖊️🖋️

🖊️ 🖊️ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ከባለፈው ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ትምህርት በመቅሰም"ከአምስት ዓመት በኋላስ ውጤታችን ከምን ድረስ  ይሆናል?" የሚለው ጥያቄ ነበር ። 🖊️ሳን ገታ ትልቅ ...
24/05/2026

🖊️ 🖊️ ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ከባለፈው ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ትምህርት በመቅሰም"ከአምስት ዓመት በኋላስ ውጤታችን ከምን ድረስ ይሆናል?" የሚለው ጥያቄ ነበር ።
🖊️ሳን ገታ ትልቅ ግብ በመያዝ እንደ ጅማሬ ቀጥለን ፤ ትልቁ ግባችንን የትልቅ ስብዕና መጀመሪያ በማድረጋችን ለዛሬ ደርሰናል።
🖊️ ሽንፈት ማለት መጨረሻ ማለት አይደለም፤ሽንፈት ማለት ለስኬት የሚከፈል "የትምህርት ክፍያ" ነበር በማለት ስድስተኛው ሃገራዊ ምርጫን ብዙ ትምህርት ቀስመን ለዛሬው ሀገራዊ ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነን የቀረብነው። 🖊️ ስኬት በአንድ ጀምበር የሚገኝ ተአምር አይደለም። ስኬት በየቀኑ የምታደርጋቸው ትናንሽ ጥርቅም ውጤቶች ናቸው። ዛሬ የምናረጋት ትንሿ አስተዋፅኦ፣ ዛሬ የምንሮጣት አንዲት ኪሎ ሜትር፣ ዛሬ የምታጠራቅማት እያንዳንዱ ድል... እነዚህ ሁሉ ነገ ነገሮችህን የሚወስኑ ጡቦች ናቸው።
🖊️ መንገዱ ረጅም ሊሆን ይችላል፣ ዳገቱ ሊከብድ ይችላል፤ ነገር ግን አንተ ከዳገቱ በላይ ጠንካራ ነህ።
🖊️ የሰው ልጅ አእምሮ ሊያስበውና ሊያምነው የሚችለውን ማንኛውንም ነገር ማሳካት ይችላል። አንተ የእራስህ ታሪክ ጸሐፊ ነህ።
🖊️ ብዕሩን በእጅህ ይዘሃል፤ ታዲያ ዛሬ ምን የሚል ታሪክ መጻፍ ትጀምራለህ? 🖊️ 🖊️ ብዕርን እንምረጥ 🖊️ 🖊️

🖊️ منطقة الصومال الإثيوبية، مقاطعة ديكا سوفتو؛ رحّبت أهالي المقاطعة التي ترشحت فيها الدكتورة رن أحمد، إحدى المرشحات عن ح...
22/05/2026

🖊️ منطقة الصومال الإثيوبية، مقاطعة ديكا سوفتو؛ رحّبت أهالي المقاطعة التي ترشحت فيها الدكتورة رن أحمد، إحدى المرشحات عن حزب الحرية والمساواة من شرق البلاد، في الانتخابات الوطنية السابعة.
🖊️ هذا هو حزب الحرية والمساواة.
🖊️ 🖊️ لقد اخترتمونا! 🖊️ 🖊️

🖊️ 🖊️ Gobolka Soomaalida Itoobiya, Degmada Deka-Sufto; Dr. Run Axmed, oo ka mid ah musharixiinta haweenka ah ee ka soo j...
22/05/2026

🖊️ 🖊️ Gobolka Soomaalida Itoobiya, Degmada Deka-Sufto; Dr. Run Axmed, oo ka mid ah musharixiinta haweenka ah ee ka soo jeeda bariga dalkeenna ee Xisbiga Xorriyadda iyo Sinnaanta, ayaa waxaa soo dhaweeyay bulshada Degmada oo ay ku tartamaysay doorashadii 7aad ee qaran.
🖊️ Kani waa Xisbiga Xorriyadda iyo Sinnaanta.
Waxaad noqotay
🖊️ 🖋️ doorashadayada! 🖊️ 🖊️

Address

መጋላ ኮኔል
Dire Dawa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Freedom and equality party -Dire Dawa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share