Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Dire Dawa
  • Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን

Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን News

ዜና | የአምስቱ ተጎራባች ክልሎች የወጣቶች የምክክር መድረክ በመጪው ረቡዕ በድሬዳዋ መካሄድ ይጀምራል ::  | ነሐሴ 22 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋየአምስቱ ተጎራባች ክልሎች ማለትም የድሬ...
28/08/2026

ዜና | የአምስቱ ተጎራባች ክልሎች የወጣቶች የምክክር መድረክ በመጪው ረቡዕ በድሬዳዋ መካሄድ ይጀምራል ::

| ነሐሴ 22 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የአምስቱ ተጎራባች ክልሎች ማለትም የድሬዳዋ አስተዳደር፣ የሐረሪ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የኦሮሚያ ክልል ወጣቶች የምክክር መድረክ በመጪው ረቡዕ በድሬዳዋ ከተማ መካሄድ እንደሚጀምር ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው መድረኩን በስኬት ለማጠናቀቅ በተደረገ የመጨረሻው ምዕራፍ ዝግጅትና መርሃ-ግብር አፈጻጸም ዙሪያ በተካሄደ ውይይት ላይ ነው።

የድሬዳዋ አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኻሊድ መሐመድ እንደገለጹት፤ የምክክር መድረኩ ወጣቶችን በሁለንተናዊ መልካም ተግባቦት በማስተሳሰር ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ለቀጠናው ሰላምና አብሮነት አያሌ ጠቀሜታዎችን ያበረክታል።

ወጣቶቹ በድሬዳዋ በሚኖራቸው ቆይታ ከምክክር መድረኩ በተጨማሪ፡
የችግኝ ተከላ እና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ይሳተፋሉ፤
በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን ይጎበኛሉ።

በመጨረሻም የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሻኪር አህመድ፤ ለተጋባዥ ወጣቶች ከሚደረገው አቀባበል ጀምሮ በድሬዳዋ በሚኖራቸው አጠቃላይ ቆይታ ዙሪያ ለተዋቀረው አስተባባሪ ኮሚቴ አስፈላጊውን አቅጣጫ ሰጥተዋል።

ዜና የ2019 በጀት ዓመት መደበኛ እቅድ አፈፃፀም የውል ስምምነት ተፈረመ ።DYSC 21/12/2018የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሺን የ2019 በጀት ዓመት መደበኛ እቅድ አፈፃፀም...
27/08/2026

ዜና የ2019 በጀት ዓመት መደበኛ እቅድ አፈፃፀም የውል ስምምነት ተፈረመ ።

DYSC 21/12/2018

የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሺን የ2019 በጀት ዓመት መደበኛ እቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ በኮሚሽኑ ዳይሬክተሮች እና ለኮሚሽነር ተጠሪ በሆኑ ደጋፊ ዳይሬክተሮች መካከል የውል ስምምነት የፊርማ ስነ-ስርዓት አካሄደ።

ይህ የስምምነት ሰነድ በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ ስትራቴጂካዊ ግቦችን፣ የሥራ አፈፃፀም ጠቋሚዎችን እና ዋና ዋና ተግባራትን በተያዘላቸው ጊዜ እና ጥራት ለማከናወን ያለመ ነው።

በስነ-ስርዓቱ ወቅት ኮሚሽነር ኻሊድ መሀመድ እንደገለፁት፤ የስምምነት ሰነዱ መፈረም፡

ተጠያቂነትንና ግልፅነትን ለማስፈን፣ የስራ አፈፃፀም ውጤታማነትን ለማሳደግ፣

ለድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሺን የሚሰጡ አገልግሎቶችን ደረጃ ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።

የኮሚሽኑ አመራሮች እና ለከፍተኛ ባለሞያዎች በተሰጣቸው ኃላፊነት መሰረት የታቀዱትን የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች በቁርጠኝነት ለማሳካትና የታቀደውን ግብ ለማሳካት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

#ድሬዳዋ #ወጣቶችናስፖርት ኮሚሺን
#የ2019እቅድ #ውጤታማነት #አገልግሎት

 #ስፖርት| በአገር አቀፍ የሰውነት ግንባታ ውድድር አሸናፊ ለሆነው አትሌት ሳምራን ሃሩን በድሬዳዋ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት  | ነሐሴ 20 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋበአገር አቀፍ የሰውነ...
26/08/2026

#ስፖርት| በአገር አቀፍ የሰውነት ግንባታ ውድድር አሸናፊ ለሆነው አትሌት ሳምራን ሃሩን በድሬዳዋ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት

| ነሐሴ 20 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በአገር አቀፍ የሰውነት ግንባታ ውድድር ድሬዳዋን በመወከል አሸናፊ በመሆን ላጠናቀቀው አትሌት ሳምራን ሃሩን ወደ ድሬዳዋ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

አትሌቱ ድሬዳዋ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የድሬዳዋ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ፣ የአስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ስፖርትን የማልማትና የማስፋፋት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኢብሳ ዱሪ እንዲሁም የድሬዳዋ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ዮናስ በትሩ በተገኙበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

የኢትዮጵያ የአካል ብቃትና የሰውነት ግንባታ ፌዴሬሽን ባዘጋጀው በዚህ አገር አቀፍ ውድድር ላይ አትሌት ሳምራን ሀሩን ድሬዳዋን በመወከል ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡ ይታወሳል።

ወጣት ሳምራን ሀሩን ድሬዳዋን በመወከል የኢትዮጵያ ፊትነስና ሰውነት መገንባት ፌዴሬሽን ባዘጋጀው አገር አቀፍ ውድድር (YBBS) ላይ ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ በጥሩ ደረጃ ውድድሩን አጠናቋል...
24/08/2026

ወጣት ሳምራን ሀሩን ድሬዳዋን በመወከል የኢትዮጵያ ፊትነስና ሰውነት መገንባት ፌዴሬሽን ባዘጋጀው አገር አቀፍ ውድድር (YBBS) ላይ ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ በጥሩ ደረጃ ውድድሩን አጠናቋል።

ስለሆነም በድሬዳዋ አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ስም ለሳምራን ሀሩን እንኳን ደስ አለህ እንላለን! 👏

Dargaggeessi Samran Haaruun, Dirree Dhawaa bakka bu’uun, dorgommii biyyaalessaa (YBBS) Federeeshiniin Fiitnasii fi Ijaarsa Qaamaa Itoophiyaa qopheesse irratti qabxii olaanaa galmeessuun, sadarkaa gaariin dorgommicha xumureeti jira.

Maqaa Komishinii Dargaggootaa fi Ispoortii Bulchiinsa Dirree Dhawaatiin, Samran Haaruuniif baga gammadde jechuun barbaada! 👏

 #ዜና | የድሬዳዋው በርዋቆ እግር ኳስ ክለብ ከጅቡቲ ቴሌኮም ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸነፈ  | ነሐሴ 16 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋየድሬዳዋ አስተዳደር ዕ...
22/08/2026

#ዜና | የድሬዳዋው በርዋቆ እግር ኳስ ክለብ ከጅቡቲ ቴሌኮም ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸነፈ

| ነሐሴ 16 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ዕውቅና የሰጠውና የሁለቱን ታሪካዊ ከተሞች የስፖርት ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር የተዘጋጀው የወዳጅነት ጨዋታ በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ተካሂዷል።

በጨዋታው ላይ የጅቡቲ ቴሌኮም የተሻለ የጨዋታ የበላይነት በማሳየት በርዋቆን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

በዓመቱ መጀመሪያ ላይ በሚከናወነው የድሬዳዋ ከተማ ዋንጫ ላይ የጅቡቲ ክለቦች መሳተፋቸው የከተሞቹን የንግድ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ባለፈ በእግር ኳሱም ያለውን አጋርነት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።

በዚሁ የወዳጅነት ጨዋታ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኻሊድ መሐመድን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር በአስተዳደሩ የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን በንቃት እየሰራ የሚገኝ ማህበር መሆኑ ተገለፀ። | ነሐሴ 14/2018በድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር አዘጋጅነት በ...
20/08/2026

የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር በአስተዳደሩ የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን በንቃት እየሰራ የሚገኝ ማህበር መሆኑ ተገለፀ።

| ነሐሴ 14/2018
በድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር አዘጋጅነት በቢዮአዋሌ ክላስተር ኢጃነኒ ገጠር ቀበሌ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር በዛሬው እለት ተካሂዷል።

የድሬዳዋ አስተዳደር የለሊት ታክሲ ማህበር ለነዋሪው ህብረተሰብ ከሚሰጣቸው የትራንስፖርት አገልግሎቶች በተጨማሪ በተለያዩ የማህበራዊ አገልግሎቶች ላይም በንቃት እየተሳተፈ የሚገኝ ማህበር መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ተናግረው በተለይም የምግብ ዋስትናን ሊያረጋግጡ የሚችሉ እንዲሁም ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞችን በዛሬው ዕለት መትከላቸውንም ነው አቶ ኢብራሂም ያስታወቁት።

የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር በራሳቸው ተነሳሽነት የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አንድ አካል የሆነውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር ማካሄዳቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ካሊድ መሀመድ ተናግረው በተለያዩ አካባቢዎች በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ የሚተከሉ ችግኞችን መንከባከብ እንደሚገባም ገልፀዋል።

የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር ከሚሰራቸው የማህበራዊ አገልግሎቶች አንዱ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር መሆኑን የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር ሊቀመንበር የሆነው ወጣት ቃልኪዳን ፀሀይ ተናግረው ማህበሩ ከአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር በተጨማሪ የፅዳት እና የደብተር ልገሳዎችን ማካሄዳቸውንም ነው የማህበሩ ሊቀመንበር ወጣት ቃልኪዳን በእለቱ ያስታወቁት።

 #ዜና /የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ዜጎች ከግል ጥቅማቸው ባሻገር ለሌሎች ወገኖቻቸው ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ በማህበረሰቡ ውስጥ የመረዳዳት ባህልን እንዲያጎለብቱና የጋራ ችግሮችን በጋራ ...
15/08/2026

#ዜና /የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ዜጎች ከግል ጥቅማቸው ባሻገር ለሌሎች ወገኖቻቸው ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ በማህበረሰቡ ውስጥ የመረዳዳት ባህልን እንዲያጎለብቱና የጋራ ችግሮችን በጋራ እንዲፈቱ የሚያበረታታ መሆኑ ተገለጸ

DYSC ነሐሴ 9/2018

​“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የክረምት የበጎ ፈቃድ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት እና በተጠሪ ተቋማት አስተባባሪነት ተካሂዷል።

​መርሃ ግብሩ በድሬዳዋ አስተዳደር የክረምት የበጎ ፈቃድ ተግባራትን በማጠናከር፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍና የወገንነት ባህልን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፤ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸውና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ የበጎነትን መርህ ማሳየት ዋና ዓላማው ነው።

​በመርሃ ግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የተጠሪ ተቋማት ተወካዮች፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጪዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

​የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በርካታ ማህበረሰብ ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። የማዕድ ማጋራት ተግባሩም የምግብ ድጋፍን ብቻ ሳይሆን በማህበረሰቡ ውስጥ የመተሳሰብና የመደጋገፍ እሴቶችን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።

​የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ከሪማ አሊ በበኩላቸው፤ የበጎ ፈቃድ ተግባራት ሲጠናከሩ በማህበረሰቡ ውስጥ መተሳሰብና መተባበር እንደሚጎለብት ጠቁመው፣ ይህም ለማህበራዊ መረጋጋትና ለሀገራዊ አንድነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

​ምክር ቤቱ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የማዕድ ማጋራት ድጋፍ ለ250 ወገኖች ያደረገ ሲሆን፤ በተጨማሪም ለ600 ተማሪዎች የሚሆል የትምህርት ቁሳቁስ ለአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮና ለተማሪዎቹ አስረክቧል።

​በመጨረሻም የተካሄደው የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብር የምግብ ድጋፍን ከማቅረብ ባሻገር የወገንነት፣ የመተሳሰብና የመደጋገፍ መልዕክትን ያስተላለፈ ተግባር መሆኑ ተገልጿል።

ዘጋቢ ፉአድ አሊ
ፎቶ ሰላም አበበ

⚽️ ዜና ለወረዳ 05 እና ለአካባቢው ወጣቶች ታላቅ የምስራች! በተስፋዬ ሜዳ የተገነባው ዘመናዊ የአርቲፊሻል እግር ኳስ (ፉትሳል) ሜዳ በክቡር ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር ተመርቆ በይፋ አገልግ...
15/08/2026

⚽️ ዜና ለወረዳ 05 እና ለአካባቢው ወጣቶች ታላቅ የምስራች!

በተስፋዬ ሜዳ የተገነባው ዘመናዊ የአርቲፊሻል እግር ኳስ (ፉትሳል) ሜዳ በክቡር ከንቲባ አቶ ከዲር ጁሃር ተመርቆ በይፋ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ ዘመናዊ የስፖርት ማዕከል ወጣት ዮሴፍ ተሻገር ከኮሚሽናችን እና ከወረዳ 05 አስተዳደር ጋር በመተባበር ያስገነባው ሲሆን፣ ለአካባቢው ወጣቶች የስፖርት ክህሎታቸውን የሚያሳድጉበትና ጊዜያቸውን በጥሩ ሁኔታ የሚያሳልፉበት ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
ለስፖርትና ለወጣቶች እድገት አስተዋጽዖ ላደረጉ አካላት በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉

"ብዝሀ የወጣቶች እውቀት ለጋራ ትልም"!በድሬዳዋ አስተዳደር “ብዝሀ የወጣቶች እውቀት ለጋራ ትልም” በሚል መሪ ቃል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለ23ኛ ጊዜ የሚከበ...
13/08/2026

"ብዝሀ የወጣቶች እውቀት ለጋራ ትልም"!

በድሬዳዋ አስተዳደር “ብዝሀ የወጣቶች እውቀት ለጋራ ትልም” በሚል መሪ ቃል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለ23ኛ ጊዜ የሚከበረውን የወጣቶች ቀን አስመልክቶ የተዘጋጀው ማጠቃለያ መድረክ በደማቅ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ከሪማ አሊ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደረጀ ፀጋዬ፣ የካቢኔ አባላት እንዲሁም በአስተዳደሩ የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮችና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች ተገኝተዋል።

በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ በክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የተመራ የከፍተኛ አመራሮች ቡድን ከአስተዳደሩ ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር በጋራ በመሆን የችግኝ ተከላ አከናውኗል።

በኤደን ሳሙኤል
ፎቶ፦ አገኘሁ ሸዋረጋ

 #ዜና /የድሬደዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም የካፍ የ3ኛ ደረጃ ዕውቅና ለማግኘት የሚያስችለው ምርመራ ተደረገበት  ነሀሴ 6/2018​የድሬደዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም አሁን ያለበትን የ2ኛ ደረጃ ዕ...
12/08/2026

#ዜና /የድሬደዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም የካፍ የ3ኛ ደረጃ ዕውቅና ለማግኘት የሚያስችለው ምርመራ ተደረገበት

ነሀሴ 6/2018

​የድሬደዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም አሁን ያለበትን የ2ኛ ደረጃ ዕውቅና ለማሻሻል አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ።

​የድሬደዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ካሊድ መሐመድ እንደገለጹት፤ ስታዲየሙ የተደረገበትን ምርመራ አልፎ የ3ኛ ደረጃ ዕውቅና ካገኘ አሁን ከሚሰጠው አገልግሎት በላይ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።

​በአሁኑ ወቅት ስታዲየሙ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታዎችን ብቻ የማስተናገድ ፈቃድ ያለው ሲሆን፣ የ3ኛ ደረጃ ፈቃድ ሲያገኝ ግን በብሔራዊ ቡድን እንዲሁም በክለቦች ደረጃ የሚካሄዱ ዓለም አቀፍ የነጥብ ጨዋታዎችን ማስተናገድ የሚያስችለው ይሆናል ብለዋል።

​ኮሚሽነር ካሊድ አክለውም፤ ስታዲየሙ በየጊዜው ደረጃውን እያሻሻለ እዚህ ደረጃ እንዲደርስ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

በዳግማዊ ፍቃዱ
ፎቶ፦ሰላም አበበ

Address

Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን:

Shortcuts

Share