Dire Dawa Administration Health Bureau

Dire Dawa Administration Health Bureau Government Organization

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከ JSI ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በ2018 ዓ.ም በተመረጡ ጤና ተቋማት የተጀመሩ የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክቶች (Quality Improvement Projects) ያ...
30/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከ JSI ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በ2018 ዓ.ም በተመረጡ ጤና ተቋማት የተጀመሩ የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክቶች (Quality Improvement Projects) ያሉበትን የአፈፃፀም ግምገማና የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሂዷል።

መድረኩ በጤና ተቋማት የመረጃ ጥራት፣ የሪፖርት ተመጣጣኝነት፣ የአገልግሎት ክትትልና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችን ለማሻሻል እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በጋራ ለመገምገምና ቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን ተገልጿል።

በአስተዳደሩ ጤና ቢሮ በዕቅድ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት የጤና መረጃ አስተዳደር ስርዓት አስተባባሪ አቶ ነጋ ጌትነት እንደገለፁት በአስተዳደሩ የሚታዩ የዝቅተኛ አፈፃፀም ጠቋሚዎች(low performing indicators) ለመቀየር የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክቶች ትልቅ ሚና እንዳላቸው በመግለፅ በተለይም በመረጃ ጥራት፣ በሪፖርት ተመጣጣኝነት፣ በመድሐኒት አቅርቦትና በአገልግሎት ክትትል ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ መፍትሄዎችን መተግበር አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

አቶ ነጋ አክለውም የጤና መረጃ ለትክክለኛ ውሳኔ መሰረት በመሆኑ በጤና ተቋማት የሚመነጩ መረጃዎች ትክክለኛ፣ ወቅታዊና ተመጣጣኝ መሆን እንዳለባቸው ገልፀው፣ በተለይም በጤና ተቋማት ደረጃ የሚታዩ የመረጃ ልዩነቶችና የሪፖርት አለመጣጣሞች በአገልግሎት እቅድ፣ በመድሐኒት ስርጭትና በሀብት አጠቃቀም ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንደሚያሳድሩ አብራርተዋል።

በመድረኩም ሁለት ዋና ዋና የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክቶች የቀረቡ ሲሆን፤ የመጀመሪያው “In-depth Data Quality Analysis (Triangulation) of Family Planning Program Vs Supply Reports” የተሰኘ የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክት ሲሆን ይህም በቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር እና በመድሐኒት አቅርቦት ሪፖርቶች መካከል ያለውን የመረጃ ልዩነት በመተንተን ተመጣጣኝና ታማኝ መረጃ እንዲኖር ለማስቻል የተዘጋጀ መሆኑ በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የእናቶች ጤና አገልግሎትና ቤተሰብ ዕቅድ ባለሙያ የሆኑት አቶ ደጉ ኩኖ ገልፀዋል።

ፕሮጀክቱ ለተጠቃሚዎች ወቅታዊና ቀጣይ የቤተሰብ ዕቅድ የመድሐኒት አቅርቦት እንዲኖር እንዲሁም በጤና ተቋማት የሚከሰተውን የመድሐኒት ብክነትና የአገልግሎት መሰጫ መሳሪያ እጥረት ለመቀነስ እንደሚያግዝና በተለይም ትክክለኛ መረጃ መኖሩ ለትክክለኛ የመድሐኒት ትንበያና አቅርቦት ውሳኔ ለመስጠት እንደሚያስችልም ተጠቅሷል።

ሁለተኛው “Scaling-up Report Consistency of Under Five Children Diarrhea Disease versus service report” የተሰኘ የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በሪፖርቶች ላይ የሚታዩ የመረጃ አለመጣጣሞችን ለመቀነስ ያለመና ፕሮጀክቱ መጀመሪያ በተመረጡ ጤና ተቋማት በሙከራ ደረጃ ተተግብሮ በአፈፃፀሙም የሪፖርት ተመጣጣኝነትና የመረጃ ጥራት ላይ አበረታች ለውጥ መታየቱ ተገልጿል።

የጤና ተቋማት የጥራት አስተባባሪዎችና ባለሞያዎች፣ የጤና መረጃ ባለሙያዎች፣ የፕሮግራም አስተባባሪዎች፣ እንዲሁም የሚመለከታቸው አጋር አካላት በመድረኩ ተሳትፈዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
22/09/2018 ዓ.ም

የድሬደዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄደ።​የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሂዷል።በመድረኩ...
28/05/2026

የድሬደዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄደ።

​የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የቢሮው ከፍተኛ አመራሮች፤ የጤና ተቋማት ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት በጤናው ዘርፍ በተቀመጡ አመላካቾች የተመዘገቡ ውጤቶችና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

​በአስተዳደሩ ጤና ቢሮ የልማት፣ እቅድና በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ግርማ በመድረኩ ላይ እንዳሉት የግምገማ መድረኩ ዋና ዓላማ ባለፈው የ6 ወራት ግምገማ ወቅት የተሰጡ ተልዕኮዎችንና ግብረ-መልሶችን አፈፃፀም ምን እንዳሳካን የምንገመገምበትና “በ9 ወራቱ የተቀመጡ ቁልፍ የጤና አመላካቾችን በዝርዝር የሚገመገሙበት ነው ብለዋል።

አቶ አለማየሁ አያይዘውም ባለፉት 9 ወራት ያስመዘገብናቸውን ጠንካራ ውጤቶች ይበልጥ በማስቀጠል ዝቅተኛ አፈፃፀም የታየባቸውን ዘርፎች በመለየት በቀሪዎቹ ወራት አፈፃፀማችንን ከፍ ለማድረግ በምን መልኩ መሥራት እንዳለብን አቅጣጫ አመላካቾች የሚቀመጡበት መድረክ ነው ብለዋል።

​የግምገማ መድረኩን የመሩት የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ በበኩላቸው በአስተዳደር ደረጃ በጤናው ዘርፍ በበርካታ ቁልፍ አመላካቾች ላይ አመርቂና አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው በተወሰኑ ዘርፎች ላይ የሚታዩ ዝቅተኛ አፈፃፀሞችን በፍጥነት ለማሻሻልና ውጤታማነቱን ሙሉ ለማድረግ የሁሉም አካላት የተቀናጀ ሥራ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

​ዶ/ር ፅጌረዳ አያይዘውም ጥራት ያለውና ፍትሀዊ የጤና አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለማድረስ መረጃዎችን በጥራት ማየትና መተንተን መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰው የጤና ተቋማት ኃላፊዎች ለዚህ ሥራ ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል። በተለይም በገጠር አካባቢ የሚገኙ የጤና ተቋማት ያሉባቸውን የአፈፃፀም ክፍተቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመሙላትና ውጤታቸውን ለማሳደግ በ ጊዜ የለኝም መንፈስ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባቸው ዶክተር ፅጌረዳ ጥብቅ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
20/09/2018 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች የሥራ ባልደረባችን በሆኑት በአቶ ኤፍሬም ስዩም ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን መሪር ሃዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ  መ...
28/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች የሥራ ባልደረባችን በሆኑት በአቶ ኤፍሬም ስዩም ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን መሪር ሃዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።

ግንቦት 20/2018 ዓ.ም

27/05/2026
የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ እንኳን ለ1447ኛው ዓመት ሒጅራ የዒድ አል- አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የስኬት እንዲሆንልን መል...
26/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ እንኳን ለ1447ኛው ዓመት ሒጅራ የዒድ አል- አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የስኬት እንዲሆንልን መልካም ምኞቱን ይገልፃል፤

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ

የሰቆጣ ቃል ኪዳን ማስፋፋት ምዕራፍ ስልጠና ተሰጠ።የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር እና ከማክስ ፋዉንዴሽን ኢትዮዽያ ጋር በመተባበር የሰቆጣ ቃል ኪዳን ማስፋፋት ምዕራፍ / SD ...
25/05/2026

የሰቆጣ ቃል ኪዳን ማስፋፋት ምዕራፍ ስልጠና ተሰጠ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር እና ከማክስ ፋዉንዴሽን ኢትዮዽያ ጋር በመተባበር የሰቆጣ ቃል ኪዳን ማስፋፋት ምዕራፍ / SD Scaling with Quality/ ስልጠና ሰጠ።

በስልጠናው መክፈቻ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤና ማበልፀግ ኬዝ ቲም አስተባባሪ አቶ ታሪኩ አበበ ተሳታፊዎች በስልጠናው ሂደት ተሞክሮዋቸውን በመለዋወጥና በመቀመር እንዲሁም ለማስፋት የሚረዱ ዕቅዶችን በማውጣት በቀጣይ ለፕሮግራሙ አፈፃፀም ውጤታማነት የድርሻችሁን ኃላፊነት ልትወጡ ይገባል ብለዋል።

በድሬዳዋ አስተዳደር የዘርፈ ብዙ ቅንጅት የምግብ ስርዓትና ኒዩትሪሽን አማካሪ አቶ መልካሙ ከፍያለው በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ከፍተኛ ተፅዕኖ ያላቸውን በማስረጃ የተደገፉና በተግባር የተሳኩ የምግብና የስርዓተ ምግብ ትግበራዎች በጥራት እንዲሰፉ ለመንደፍ፣ ለማቀናጀትና ለመተግበር ታልም የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

በስልጠና መድረኩ በአስተዳደሩ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ወረዳ/ክላሰተር የስርዓተ ምግብ እና ኒውትሪሽን ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት፤ ከተለያዩ ሴክተር -ከጤና፥ ትምህርት፥ የግብርና፤ ሴቶች፤ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ፤ መንግስት ኮሚኒኬሽን፤ ፋይናንስ እና ንግድ የተውጣጡ መሆናቸውን አቶ መልካሙ አክለው ተናግረዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽ
17/09/2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤና መረጃ አስተዳደር ስርዓት ኬዝ ቲም የተቀናጀ የጤና መረጃ ስርዓት (Integrated HIS) ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጠ።በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የዕቅድ...
24/05/2026

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤና መረጃ አስተዳደር ስርዓት ኬዝ ቲም የተቀናጀ የጤና መረጃ ስርዓት (Integrated HIS) ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጠ።

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የዕቅድ ክትትል እና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ግርማ እንደገለጹት የጤና መረጃ የእያንዳንዱ ተገልጋይና ታካሚ ሕይወት መሆኑን ተናግረው መረጃው በጤና ተቋማት በጥንቃቄ መሰብሰብ፤ በመደበኛነት መከታተል እና ከምንጭ ሰነድ እስከ ሪፖርት ድረስ የተጣጣመ ሆኖ መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

አቶ አለማየሁ አክለውም የጤና መረጃ የጤና አገልግሎት ወሳኔን ለመወሰን እና ወሳኔውን መሰረት በማድረግ አገልግሎት ለመስጠት ጉልህ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል።

በአስተዳደሩ ጤና ቢሮ የጤና የዕቅድ ክትትል እና ግምገማ ዳይሬክቶሬት መረጃ አስተዳደር ስርዓት አስተባባሪ አቶ ነጋ ጌትነት እንደገለጹት ከስልጠናው በኋላም የጤና መረጃ ቴክኒሻኖች (HITs) የየራሳቸውን እንዲሁም በእነሱ ስር በሚገኙ ጤና ተቋማቶች ላይ የወስዱትን ስልጠና ተግባራዊ እንዲያደርጉ ይጠበቃል ብለዋል።

በስልጠናው የጤና መረጃ ድጋፍዊ ጉብኝት (HMIS Mentorship)፤ የጤና መረጃ አብዮት አመዛዘን ( Information Revolution Assessment) ፤ማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መረጃ ስርዓት (community Health information system) እና የተቀናጁ የጤና መረጃ የባህርይ የመፍትሄ ሃሳቦች (Integrated Behavioural Solution) ያካተቱ ፅሁፎች ቀርበዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
16/09/2018 ዓ.ም

"የክትባቶችን ጠቀሜታ በማስገንዘብ የህብረተሰባችንን ጤና ልንጠብቅ ይገባል"                       አቶ ታሪኩ አበበ በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤና ማበልፀግ ኬዝ ቲም አስተባ...
23/05/2026

"የክትባቶችን ጠቀሜታ በማስገንዘብ የህብረተሰባችንን ጤና ልንጠብቅ ይገባል"

አቶ ታሪኩ አበበ
በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤና ማበልፀግ ኬዝ ቲም አስተባባሪ

ሁለተኛው ዙር የማህፀን በር ካንሰርንና የክትባት ፕሮግራሞችን ጨምሮ ሌሎች የጤና ፕሮግራሞችን ውጤታማ ለማድረግ የሚረዳ ስልጠና ከየወረዳው ለተውጣጡ የብሎክ አደረጃጀት መሪዎች እና ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሰጠ።

ስልጠናው የተሰጠው የማህፀን በር ካንሰር ምርመራን በተመለከተና ስለክትባቶች የተሻለ ግንዛቤን በመያዝ ህብረተሰቡን በማንቃት እና የጤና አገልግሎቶችን በሚገባ በመጠቀም የራሱን እና የሌሎችንም ጤና መጠበቅ እንዲችል ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤና ማበልፀግ ኬዝ ቲም አስተባባሪ አቶ ታሪኩ አበበ ተናግረዋል።

አቶ ታሪኩ አክለውም የብሎክ አደረጃጀት መሪዎችና የህብረተሰብ ተወካዮች ለህብረተሰቡ ጤና መጠበቅ ሚናቸው ከፍ ያለ ነው ያሉ ሲሆን የክትባቶችን ጠቀሜታ በማስገንዘብና የማህፀን በር ካንሰርን ለመከላከል ምርመራ ማድረግ ተገቢ መሆኑን በማስተማር የህብረተሰባችንን ጤና ልንጠብቅ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

በግንዛቤ መስጫ መድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ ልማትና ህብረተሰብ ተሳትፎ ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ረሂማ አወል የሥራ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

ለተሳታፊዎች በክትባቶች ዙሪያ ያተኮሩ፤ የማህፀን በር ካንሰርን በተመለከተና ሌሎች የጤና ፕሮግራም ፅሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጓባቸዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
15/09/2018 ዓ.ም

ለድሬዳዋ አርሰናል ክለብ ደጋፊዎች በሙሉ የድሬዳዋ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት 2025/2026 የውድድር ዘመን ሻምፒን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እያለ የዋንጫ ፕሮግራሙን ምክኒያ...
22/05/2026

ለድሬዳዋ አርሰናል ክለብ ደጋፊዎች በሙሉ የድሬዳዋ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት 2025/2026 የውድድር ዘመን ሻምፒን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እያለ የዋንጫ ፕሮግራሙን ምክኒያት በማድረግ ግንቦት 15 እና 16 ድሉን እያጣጣምን ደም እንለግስ በማለት ጥሪውን ያቀርባል።

በስኬታችን ድልድይ ሆንን እናገልግል

አድራሻ 👇👇
ከዚራ ፖሊስ ጣቢያ ከፍ ብሎ የድሬዳዋ ደምና ህብረ-ህዋስ ባንክ አገልግሎት

የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመከላከል የተቀናጀ የማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ። የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመከላከል የአጎራባች ክልሎች  መቀናጀትና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ መሥራት ወሳኝ በ...
21/05/2026

የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመከላከል የተቀናጀ የማህበረሰብ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመከላከል የአጎራባች ክልሎች መቀናጀትና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ መሥራት ወሳኝ በመሆኑ የድሬዳዋ አስተዳደር፤ የሐረሪና ጅግጅጋ ክልሎችን ያሳተፈ የምክክር አውደ ጥናት በድሬዳዋ አስተዳደር ተካሄዷል።

በአውደ ጥናቱ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ኬዝቲም አስተባባሪ አቶ ጂሃድ አባነጋሽ ድሬዳዋን ጨምሮ ሁለቱ ክልሎች በተመረጡ ጤና ተቋማት ላይ በሰለጠኑ አቻ ለአቻ ምክር ሰጪ ግለሰቦች አማካኝነት በህክምና ላይ ያሉትን የቲቢ ታማሚዎችን የድጋፍ አገልግሎት ለማጠናከር፤ ግንዛቤ ለማሳደግና የቲቢ ህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ያለሙ ሥራዎችን ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲሰጥ የማስጀመርያና የማስተዋወቅያ መድረክ ነው ብለዋል።

ቤዛ ፖስትሪቲ ልማት ድርጅት የቲቢ ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑት አቶ ታጀበ ጌታቸው በበኩላቸው በቲቢ በሽታ ታመው ህክምናቸውን በአግባቡ የተከታተሉና ከበሽተው የዳኑ ወገኖቻችንን የሚመራና ማህበረሰቡን ያሳተፈ የቲቢ በሽታ መከላከል ሥራ ከጤና ፕሮግራሞች ጋር በማቀናጀት ለመሥራት የታቀደ ፕሮጀክት መሆኑ ጠቅሰው የሥራው ስኬታማነት በቀጣይ ተገምግሞ ለወደፊትም በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልፀዋል።

ይህ ሥራ በጤና ሚኒስቴርና በጉለባል ፈንድ ድጋፍ የሚሠራ ሲሆን ፕሮጀክቱ ድሬዳዋን ጨምሮ በሁለቱም ክልሎች በተመረጡ ሶስት ጤና ተቋማት ማለትም ከየክልሉ አንድ ሆስፒታልና ሁለት ጤና ጣብያ ላይ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

በመድረኩም የሳቢን ጠቅላላ ሆስፒታል፤ የጎሮና የለገሀሬ ጤና ተቋም ኃላፊዎች እንዲሁም ከሶስቱ ተቋማት የተመረጡ የቲቢ ህክምና ተከታትለው በመጨረስ ሙሉ በሙሉ የተፈወሱ ታካሚዎች፤ ከጤና ቢሮ የቲቢ ፕሮግራም ባለሙያዎች፤ የሐረሪና የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ የቲቢ ፕሮግራም አስተባባሪዎችና ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
13/09/2018 ዓ.ም

Address

Dire Dawa

Telephone

+251251112330

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Administration Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share