Dire Dawa Administration Health Bureau

Dire Dawa Administration Health Bureau Government Organization

ለ1ሺ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክትየድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ፅጌሬዳ ክፍሌ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ...
24/08/2026

ለ1ሺ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ፅጌሬዳ ክፍሌ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት (መውሊድ) በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ብለዋል ፡፡

በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የመደጋገፍና የአብሮነት በዓል በመሆኑ ይሄንን በተግባር የምናሳይበትና ያለው ለሌለው በማካፈልና የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ በዓሉ ልናሳልፍ እንደሚገባ በመልእክታቸው ገልፀዋል።።

እንደ ኃላፊዋ መልዕክት የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመልካምነት፣ የሰላምና የመተሳሰብ አስተምህሮች ዛሬም ለማኅበረሰቡ ትልቅ እሴት ያላቸው በመሆኑ በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት፤ የታመሙ ወገኖቻችን በመጠየቅ የጀመርነውን የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎችን አጠናክረን በመሥራት ልናሳልፈው እንደሚገባ አሳስበዋል።

ዶ/ር ፅጌሬዳ በመጨረሻም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በድጋሚ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የመደጋገፍና የአንድነት እንዲሁም የበረከት እንዲሆንልን ከልብ ተመኝተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
18/12/2018 ዓ.ም

24/08/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም መድረክ 👇👇

በአስተዳደሩ የሚገኙ 142 የመንግስትና የግል የችርቻሮ መድሃኒት መሸጫዎች/ ፋርማሲዎች ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን  መተግበሪያ መጠቀም መቻላቸው ተገለፀ።በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤናና ...
23/08/2026

በአስተዳደሩ የሚገኙ 142 የመንግስትና የግል የችርቻሮ መድሃኒት መሸጫዎች/ ፋርማሲዎች ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን መተግበሪያ መጠቀም መቻላቸው ተገለፀ።

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር የሥራ ሂደት የጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን አተገባበር አስመልክቶ የተሠሩ ሥራዎችን ገምግሟል።

በግምገማ መድረኩ መልእክት ያስተላለፉት የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር የሥራ ሂደት ተወካይ አቶ ወንድሙ ተስፋዬ እንደገለፁት በአስተዳደሩ የመድኃኒት ቁጥጥር እና የመድሃኒት አቅርቦት አሰራርን ለማሻሻል በሀገር ደረጃ እየተተገበረ ያለውን የዲጂታል ጤንነቴ ሞባይል አፕልኬሽን ተጠቅመን በሁሉም ፋርማሲ ያሉ መድሃኒቶችን በመመዝገብ የመድሃኒት አቅርቦት፤ የመድሃኒት አያያዝን፤ ለመድሃኒት ተጠቃሚዎች በአቅራቢያቸው የሚገኝ መድሃኒት ለማወቅና የፈርማሲዎች አድራሻ እንዲሁም የመድሃኒት ዋጋ አማራጮችን ባሉበት ሆነው በሞባይላቸው የሚያዩበት የመተገበሪያ አፕሊኬሽን ቢሮው በአጭር ግዜ ሥራዎች ተሰርተው ተግባራዊ መደረጉን ገልፀዋል።

የቁጥጥር ባለሞያና የጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን አሰተባባሪ አቶ አስፋው አክሊሉ እንዳብራሩት በአስተዳደሩ የሚገኙ የችርቻሮ መድሃኒት መሸጫዎች/ፋርማሲዎች ጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን እንዲተገብሩ በተሰጠው አቅጣጫ በአጭር ግዜ 142 የመንግስት እና የግል ፋርማሲዎች ተግባራዊ ማድረጋቸው የሚበረታታ መሆኑ ገልፀው በቀጣይ ተመዝግበው ነገር ግን ወደ ትግበራው ያልገቡ የመድሃኒት ዓይነቶችን በአጭር ግዜ እንዲያስገቡና ህብረተሰቡ የጤንነቴ ሞባይል አፕሊኬሽን ከplay store ወይም ከቴሌ ብር በማውረድ በሞባይላቸው በመጫን የሚፈልጉትን መድሃኒት የት የችርቻሮ መድሃኒት መሸጫዎች/ፋርማሲዎች እንደሚገኝ እና ዋጋውንም አወዳድረው መግዛት እንደሚችሉ አቶ አስፋው ገልፀዋል።

በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ግብዓት ጥራት ቁጥጥር የሥራ ሂደት የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ 6 ወራት ዕቅድ
ወደ ግለሰብ ካስኬድ በማድረግ በጀት የማጣጣም እና በሥራ ሂደቱ የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በቀጣይ የሚፈቱበት መንገድ ላይ ተወያይተው በዕቅዳቸው እንዲካተቱ ተደርጓል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
17/12/2018 ዓ.ም

የሐዘን መግለጫየኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ደረጀ አበበ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው የተሰማንን ጥልቅ ሐ...
22/08/2026

የሐዘን መግለጫ
የኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ደረጀ አበበ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እንገልጻለን።

አቶ ደረጀ አበበ የጤና መድህን አገልግሎት ሽፋን ለማሳደግ በቅንነት እና በትጋት ያገለገሉ አመራር ነበሩ።

ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

የድሬደዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ

የ2018 በጀት ዓመት የጤና ዘርፍ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና ዓመታዊ የጤና ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ።​የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመት የጤና...
22/08/2026

የ2018 በጀት ዓመት የጤና ዘርፍ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና ዓመታዊ የጤና ጉባኤ በስኬት ተጠናቀቀ።

​የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የ2018 በጀት ዓመት የጤና ዘርፍ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና ዓመታዊ የጤና ጉባኤ የቀጣይ ዓመት የሥራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥና የእውቅና ፕሮግራም በማካሄድ ተጠናቋል።

​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በእናቶችና ሕፃናት ጤና አጠባበቅ ላይ በትኩረት በመሥራት የሚከሰቱ ሞቶችን መቀነስ፣ ወረርሽኞችን ቀድሞ መከላከል እንዲሁም የጤና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት ማረጋገጥ የቀጣይ ጊዜያት ዋና ትኩረት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል። ምክትል ከንቲባ ሀርቢ አክለውም አስተዳደሩ ከአጎራባች ክልሎች ጋር ያለውን የተቀናጀ አሠራርና የርስ በርስ መደጋገፍ ማጠናከር እንደሚገባ ገለፀዋል።

​የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌሬዳ ክፍሌ በመድረኩ እንደገለፁት የሁለተኛው የጤና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በተተገበረበት በዚህ ወቅት በርካታ መሻሻሎች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፣ በቀጣይም ዲጂታል አሠራርን ማጠናከር፣ የዳታ ጥራትን ማሳደግ፣ የታዩ ክፍተቶችን ማረም እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በምርምርና በጤና አገልግሎት የተቀናጀ ሥራ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

​በጉባኤው የተገኙት የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ተወካይ እና ልዩ አማካሪ አቶ ዮናስ ጥግነህ በበኩላቸው፤ በጤና ዘርፉ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት ውስን የሆነውን ሀብት በአግባቡና በተቀናጀ መንገድ መጠቀም እንዲሁም ተቋማት በቅንጅትና በትብብር መሥራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ጫልቱ ሁሴን በበኩላቸው የጤና ተቋማት አፈጻጸምን ለመመዘን ግልጽ መለኪያዎችን በመጠቀም ዝቅተኛ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ተቋማት ራሣቸውን ማሻሻል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

​በመድረኩ የዕቅድና ፕላን ፕሮግራም ዳሪክቶሬት ዳሪክተር በሆነት በአቶ አለማየሁ ግርማ የዓመቱን አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረበ ሲሆን በመድረኩ የተለያዩ ጥናቶችና ምርምሮች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

​በውይይቱም የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት መሻሻል፣ የበሽታ መከላከልና ቁጥጥር ሥራዎች ውጤታማነት፣የውሃ፣ ሃይጂንና ሳኒቴሽን አቅርቦት፣ የቆሻሻ አወጋገድ፣ የላብራቶሪ መሠረተ ልማት፣ የበጀትና የቦታ እጥረት፣ የሰው ኃይልና የቅንጅታዊ አሠራር ውስንነቶች ላይ በትኩረት ውይይት ተካሂዶባቸው ምላሽና አቅጣጫዎች ተመላክተውበታል።

​በመድረኩ የ2019 በጀት ዓመት ግቦችን ለማሳካት ዲጂታላይዜሽንን ማስፋፋት፣ የእናቶችና ሕፃናት ሞትን መቀነስ እና የተቋማት አቅምን መገንባት በትኩረት መሠራት እንደሚገባው ተመላክቷል።

​መድረኩ የ2019 በጀት ዓመት የሥራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ እና ለጤናው ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ለጤና ባለሙያዎችና ለአጋር ድርጅቶች የእውቅና ሰርተፊኬት እና ምስጋና በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
16/12/2018 ዓ.ም

በአስተዳደሩ በክረምት ወራት የሚከናወኑ የበጎ ፍቃድ የጤና አገልግሎቶች ከዘመቻነት አልፈው የህብረተሰቡ ዘላቂ ማህበራዊ ባህል እንዲሆኑ የማድረግ እና የማጠናከር ስራ እየተሰራ መሆኑን  የብልፅ...
20/08/2026

በአስተዳደሩ በክረምት ወራት የሚከናወኑ የበጎ ፍቃድ የጤና አገልግሎቶች ከዘመቻነት አልፈው የህብረተሰቡ ዘላቂ ማህበራዊ ባህል እንዲሆኑ የማድረግ እና የማጠናከር ስራ እየተሰራ መሆኑን የብልፅግና ፓርቲ ድሬደዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ገለጹ።

የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ እና የቀዶ ጥገና እስፔሻሊስት ሀኪሞች መካከል በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የቀዶ ህክምና ወረፋ የሚጠብቁ ታካሚዎች /Sergical Backlog/ ለመቀነስ የተዘጋጀ የውይይትና የማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የብልፅግና ፖርቲ ድሬደዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ ​አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበጎ ፍቃድ የቀዶ ህክምና ዘመቻ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት የመንግስት እና የግል የጤና ተቋማት ባለሙያዎች በተቀናጀ መንገድ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኝ ጠቁመው በክረምት ወራት የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በአስተዳደሩ የቀዶ ጥገና ወረፋ ለሚጠብቁ ታካሚዎች ህክምና ፍለጋ ወደ አዲስ አበባ እና ወደ ሌሎች ሩቅ ቦታዎች በመሄድ የሚደርስባቸውን እንግልት፣ የቤተሰብ መበተን እና ከፍተኛ ወጪ ለማስቀረት አገልግሎቱ እዚሁ ድሬዳዋ ውስጥ እንዲያገኙ መደረጉ ትልቅ የሠብአዊነት ሥራ መሆኑን ገልፀዋል።

​አቶ ኢብራሂም አያይዘውም ድሬዳዋን የአካባቢው ክልሎች እና የጎረቤት ሀገራት የሚገለገሉበት የህክምና ማዕከል ለማድረግ ከግል የጤና ተቋማት ጋር የሚደረገው አጋርነት (Public-Private Partnership) ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለበጎ ፍቃደኛ ሀኪሞች እና ለህክምና ተቋማት በአስተዳደሩ ስም ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን አስተዳደሩም ለሚሠሩት በጎ ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እና አጋርነት ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።

​በመድረኩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፅጌረዳ ክፍሌ በበኩላቸው በክረምት በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ ከመንግስት እና ከግል ጤና ተቋማት ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት በርካታ ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሆኑባቸው ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ጠቁመው በዚህም የስኳር እና የደም ግፊት ህመምተኞችን የመለየት ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ ከ40 ዓመት በላይ ለሆኑ የጤና ሴክተር ሴት ሰራተኞች ነፃ የጡት ካንሠር (Mammography) ምርመራ እየተካሄደ መሆኑንና የሄፓታይቲስ 'ቢ' እና 'ሲ' ምርመራ ተካሂዶ አዎንታዊ ለሆኑ ታካሚዎች አስፈላጊው የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ገልፀዋል።

​በተመሳሳይ ከ1,200 በላይ በ3 የመንግስት ትምህርት ቤቶች የልብ ምርመራ መደረጉን እና ከ52 በላይ ህጻናት ላይ የልብ ህመም ችግር በመገኘቱ አስፈላጊው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል።

ዶክተር ፅጌረዳ አክለውም በአስተዳደሩ የቀዶ ህክምና ወረፋ ላይ ያሉ 270 ያህል ታካሚዎችን ችግር ለመፍታት ከቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ሀኪሞች ጋር በመቀናጀት ስራው በይፋ መጀመሩን ጠቅሠው ከእነዚህ መካከል 135 ያህሉ የጆሮ፤ አፍንጫ እና ጎሮሮ (ENT) ህክምና የሚሹ በመሆናቸው አስፈላጊው ግብአት እና የህክምና መሳሪያዎች ከተሟሉ በኋላ 75 ያህሉን በአንድ ሳምንት ውስጥ ለማከም እቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱንና በዛሬው ዕለትም የሁለት ሰዎች ኦፕሬሽን ተጀምሮ ሥራው በይፋ መጀመሩን ገልፀዋል።

በመድረኩ የተገኙ በጎ ፍቃደኛ ሀኪሞች በበኩላቸው የጊዜ ሠሌዳቸውን በመከፋፈል የበጎ ፍቃድ ስራውን ለመከወን ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በመድረኩ የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ዩሱፍ ሠኢድን ጨምሮ የማኔጅመንት አባላት ተሣትፈዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
14/12/2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ የጤና መረጃ ጥራትን ለማሻሻልና የመረጃ ሥርዓቱን ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ።​የቅድመ ጥንቃቄና የቅድመ መከላከል ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የጤና ተቋማት የሚመዘግቧቸውን መረጃ...
18/08/2026

በድሬዳዋ የጤና መረጃ ጥራትን ለማሻሻልና የመረጃ ሥርዓቱን ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ።

​የቅድመ ጥንቃቄና የቅድመ መከላከል ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የጤና ተቋማት የሚመዘግቧቸውን መረጃዎች ጥራት ማስጠበቅ እንዳለባቸው ተገለጸ።

​የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሁሉም የጤና ተቋማት እና ከገጠር ቀበሌዎች ለተወጣጡ የኅብረተሰብ ጤና ሥጋት ቁጥጥር (PHEM) ፎካሎች እና የጤና መረጃ ባለሙያዎች (HIT) በ PHEM DHIS-2 ሥርዓት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለሁለተኛ ዙር የሰጠ ሲሆን፣ ስልጠናው ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል።

​በኢንስቲትዩቱ የኅብረተሰብ ጤና ቁጥጥር ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳግም አበበ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በጤናው ዘርፍ የሚታዩ የመረጃ አያያዝ ችግሮችን ለመቅረፍ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። አቶ ዳግም አክለውም በተለይም ነባር ባለሙያዎች በሥራ ሂደትና በስልጠና ያገኙትን ዕውቀትና ልምድ በተቋሞቻቸው ለሚገኙ አዳዲስ ባለሙያዎች ማካፈል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
12/12/3018 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር የማናጅመንት አባላት በክረምት በጎ ፍቃድ የተሠሩና እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን ገመገሙ።የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የማናጅመንት አባላት የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌና ...
17/08/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር የማናጅመንት አባላት በክረምት በጎ ፍቃድ የተሠሩና እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን ገመገሙ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የማናጅመንት አባላት የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌና ምክትል የቢሮ ኃላፊ አቶ ዩሱፍ ሰኢድ በተገኙበት በክረምት በጎ ፈቃድ የተያዙ የተለያዩ ዕቅዶችን የገመገሙ ሲሆን የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎች ሪፖርት ቀረቦ ወይይት ተደርጓል።

ለማናጅመንቱ ቀርበው ወይይት ከተደረገባቸው ዕቅዶች እንደ ችግኝ ተከላ፤ የነፃ ህክምና፤ የቀዶ ጥገና ወረፋ የሚጠብቁ ታካሚዎችን በዘመቻ መሥራት፤ የህክምና መሳሪያዎች ጥገና፤ ደም ልገሳ፤ የተለያዩ የቁሳቀስ ድጋፎች እና ሌሎችም ሪፖርት ቀርቦ ወይይት ተደርጎበታል።

በአጠቃላይ እስካሁን በአስተዳደሩ ከ80,000 በላይ ማህበረሰብ ክፍሎች የነፃ ህክምና ደጋፍ እንደተደረገላቸውም በሪፖርቱ ተገልጿል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
11/12/2018 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ዳይሬክቶሬቶች፤  የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ፅ/ቤት  የ 2019 በጀት ዓመት የመደበኛ ሥራዎች ዕቅድን ከቢሮ ኃ...
17/08/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ዳይሬክቶሬቶች፤ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ፅ/ቤት የ 2019 በጀት ዓመት የመደበኛ ሥራዎች ዕቅድን ከቢሮ ኃላፊ ከ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ ጋር ተፈራረሙ።

ከዳይሬክቶሬቶቹ ጋር የመደበኛ ዕቅድ ሥራዎቹን የተፈራረሙት የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ የሥራ ዕቅዶቹ አፈፃፀም የተሳካና ውጤታማ እንዲሆን ሁላችንም የድርሻችንን ኃላፊነት ልንወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
11/12/2018 ዓ.ም

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከል እና ጤና ማበልፀግ ዳይሬክቶሬት የ 2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ክንውን ግምገማ አካሄደ።በመድረኩ የዳይሬክቶሬቱ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ክ...
15/08/2026

በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከል እና ጤና ማበልፀግ ዳይሬክቶሬት የ 2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ክንውን ግምገማ አካሄደ።

በመድረኩ የዳይሬክቶሬቱ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ ክንውን አፈፃፀምና የተለዩ ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም መሻሻል ያለባቸውና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች በአቶ አጀበ ከቤ ቀርበው በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዩሱፍ ሰኢድ የተነሱ የአፈፃፀም ክፍተቶችን በኬዝ ቲም ደረጃ በመለየትና የመፍትሄ ሃሳብ በማፍለቅ ችግሮቹ የሚፈቱበትን ዕቅድ በመንደፍ በ 2019 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ለማምጣት መሥራት አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

በተለይ የከተማ የብሎክ አደረጃጀቶችን እና በገጠር የጎጥ መሪዎችን በማሳተፍ የማህበረሰባችንን ጤና ለመጠበቅ መሥራት አለብን ያሉ ሲሆን የጤና ተቋማትን በተመለከተ እንደቢሮም ሆነ እንደ ዳይሬክቶሬት የተለያዩ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች እየተሠሩ ሲሆን በቀጣይም የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር አስፈላጊው የድጋፍና ክትትል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉና ለዚህም ዳይሬክቶሬቱ የራሱን ድርሻ ይወጣል ብለዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ለምክትል ቢሮ ኃላፊ ለአቶ ዩሱፍ ሰኢድ የዳይሬክቶሬቱ ሠራተኞች የምስጋና ሽልማት ያበረከቱ ሲሆን ከፍተኛ የሥራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ክፍሎች እና ባለሞያዎች እንዲሁም ለባለድርሻ አካላት የዕውቅናና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኮሙዩኒኬሽን
09/12/2018 ዓ.ም

Address

Dire Dawa

Telephone

+251251112330

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Administration Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share