05/09/2026
የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላለፈ
ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።
1ኛ፦ ካቢኔው በመሬት እና መሬት ነክ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።
መሬትን በፕላንና በሕግ አግባብ ማስተዳደር የከተማዋን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ያፋጥናል። ይህም መሬት ለታለመላቸው የኢንቨስትመንት፣ የኢንዱስትሪ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ብቻ እንዲውል በማስቻል ረገድ ሚናው የጎላ ነው። አሠራሩ ኅብረተሰቡ ከመሬት ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ፣ በግልጽነትና ከብልሹ አሠራር በጸዳ መልኩ ማግኘት እንዲችል በማድረግ ረገድም ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
2ኛ፦ ካቢኔው በአስተዳደሩ የልማት ሥራዎች እና መልካም አስተዳደርን በማስፈን የሕዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚቻልባቸው ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በሰፊው ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ!