Dire dawa Administration Council P

Dire dawa Administration Council P Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dire dawa Administration Council P, Government Organization, Dire Dawa.

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር የኢድ አል አደሀ (አረፋ) በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት  የተከበራችሁ የአስተዳደራችን ነዋሪዎች እና መላው የእስ...
26/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር የኢድ አል አደሀ (አረፋ) በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት

የተከበራችሁ የአስተዳደራችን ነዋሪዎች እና መላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በአል በሰላም አደረሳችሁ

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የሁላችንም የጋራ መኖሪያችን የሆነችውን ድሬዳዋን በማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ የህግ ማውጣትና የክትትልና ቁጥጥር ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ በምክር ቤቱ በተቋቋሙ ቋሚ ኮሚቴዎች አማካኝነት የአስተዳደሩን አስፈጻሚ አካላት የስራ እንቅስቃሴ በመከታተል የድጋፍና ክትትል ስራዎችን በማከናወን እንዲሁም በህዝብ ውክልና የውይይት መድረኮች የሚነሱ የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ እና የተቋማቱን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ቅንጅታዊ ስራዎችን አጠናክሮ ሲሰራ ቆይቷል፡፡
የአስተዳደሩ ነዋሪም ለአስተዳደሩ ሰላምና ዲሞክራሲያዊ ስረአት መረጋገጥ ዋነኛ መሳሪያ በሆነው የሀገራዊ ምርጫ ንቁ ተሳታፊ በመሆን በአስተዳደሩ ዲሞክራሲያዊ የህዝብ አስተዳደር እንዲሁም የተጀመሩ የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ እንዲሁም በአሉን በምናከብርበት ወቅት በአካባቢያችን ለሚገኙ አቅመ ደካማ ወገኖቻችንን በእስልምና አስተምህሮ በሚያዘው መሰረት ያለንን በማካፈል በአሉን በደስታ እና በፍቅር እንዲያከብሩ እንድናደርግ ጥሪዬን እያቀረብኩ በአሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡
የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ

ለድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት ስልጠና ተሰጠበዛሬው እለት በፌዴራሊዝም እና ኘሮጀክት ሞኒተሪንግ ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና ለድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባ...
23/05/2026

ለድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት ስልጠና ተሰጠ

በዛሬው እለት በፌዴራሊዝም እና ኘሮጀክት ሞኒተሪንግ ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና ለድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ለም/ቤቱ ጽ/ቤት አመራሮች እንዲሁም ለቋሚ ኮሚቴ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሰጥቷል።

በስልጠናው ላይም የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር እና ም/አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ ተገኝተዋል።

የስልጠናውን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ም/ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አባላትን አቅም ለማጎልበት የተለያዩ ርእሶች ላይ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱን ገልጸው በዛሬው ስልጠናም ቋሚ ኮሚቴዎች በሚያካሂዱት የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች ውስጥ አንዱ የኘሮጀክቶች አፈጻጸም ክትትል በመሆኑ ስልጠናው ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርና የመንግስት ኘሮጀክቶች ከጅማሬ እስከ ፍጻሜ ድረስ የሚያልፉበትን ሂደት ለመከታተል እና ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ እንዲሁም ከህግ አወጣጥ እና የፌዴራሊዝም ስረአት ጋር ተያይዞ ለቋሚ ኮሚቴ አባላት ስልጠናው ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
በመቀጠልም በኘሮጀክት ሞኒተሪንግ ኤንድ ኢቫሉዬሽን ርእስ በወ/ሮ ብርሀኔ ውብሸት እንዲሁም በፌዴራሊዝም እና ዲሞክራሲ ዙሪያ የተዘጋጀ የስልጠና ሰነድ በአቶ ናኒ ደበሌ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተካሂዶበታል።

በአዲሱ ካሳ
ፎቶ በእንድሪያስ ደሱ

#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!

ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et

ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d

ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/?si=TB3KelHlFoN6FhsP

ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1

ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤

ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን

የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ከፍተኛ አመራሮች የድንገተኛ መስክ ምልከታ በዛሬው እለትም ቀጥሏልበሁለተኛው ቀን በዋለዉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ እና የቋሚ...
13/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ከፍተኛ አመራሮች የድንገተኛ መስክ ምልከታ በዛሬው እለትም ቀጥሏል

በሁለተኛው ቀን በዋለዉ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ እና የቋሚ ኮሚቴ አባላት ድንገተኛ የመስክ ምልከታ በተለያዩ የመንግስት ተቋማትና የልማት ድርጅቶች ላይ ተከናውኗል።

ለሁለተኛ ቀን በቀጠለው የድንገተኛ የመስክ ምልከታ የመልካ ጤና ማዕከል ለማህበረሰቡ የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት ጎብኝቷል።

የአሳሊሶ ክላስተር እና የዲስትሪክት 01' የስራ አስፈፃሚ ቢሮን እንዲሁ ምልከታ የተደረ ሲሆን የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ስራ ሂደት ምን እንደሚመስል ተገምግሟል ።

የድሬዳዋ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የምልከታዉ አካል ሲሆን አገልግሎቱን ከማዘመንና ከማቀላጠፍ አንፃር እንዲሁም የህብረተሰቡን ጥያቄ በተገቢዉ መንገድ ከማስተናገድ አንፃር የተሰሩ ስራዎችን ተመልክተዋል ።

በጉብኝቱ ወቅት የተሰሩ አበረታች ስራዎች እንዲቀጥሉ እና በዉስንነት የሚታዩ ችገሮች ለቀጣይ በሚስተካከልበት አግባብ ስራዎች እንዲሰሩ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ከፍተኛ አመራሮች በተመረጡ የመንግስት ተቋማት ድንገተኛ የመስክ ምልከታ አካሄዱ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ እና የቋሚ ኮሚቴ አ...
12/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ከፍተኛ አመራሮች በተመረጡ የመንግስት ተቋማት ድንገተኛ የመስክ ምልከታ አካሄዱ

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ እና የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተለያዩ የመንግስት ተቋማትና የልማት ድርጅቶች ላይ ድንገተኛ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።

ድንገተኛ የመስክ ምልታው ከአሁን በፊት የተቋማቱን አገልግሎት አሰጣጥ አስመልክቶ ይነሱ ለነበሩ የህዝብ ጥያቄዎች እና በም/ቤቱ ለተሰጡ አቅጣጫዎች በተቋማቱ የተሰጡ ምላሾች የሚገኙበትን ደረጃ ለመገምገም ያለመ ነው።

በመሆኑም በሽኒሌ እና በማርያም ሰፈር የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚገኙ የሴፍቲ ታንከሮች አሁናዊ ሁኔታ : የሳቢያን አጠቃላይ ሆስፒታል እንዲሁም በግብርና እና እንስሳት ሀብት ዳይሬክቶሬት በመገኘት፣ የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ የሚገኝበት ደረጃ ምልከታ ተደርጎባቸዋል ። በተጨማሪም በግብርና ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ያለውን የንብረት አያያዝ እንዲሁም በድሬ ሁለገብ የገበሬዎች ማህበር የዶሮ መኖ ዝግጅትና የእርባታ አያያዝን ተመልክተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አብዲ ሙክታር በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ተቋማት ከሕዝብ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዕቅዳቸው መሠረት እየፈቱ መሆኑን ማረጋገጥ የምክር ቤቱ ዋነኛ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ መሆኑን ገልጸው በምልከታውም በተወሰኑ ዘርፎች የተሻሉ ለውጦች መኖራቸውን እና ተቋማቱ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በጊዜ አጠቃቀም እና በንብረት አያያዝ ላይ በከፍተኛ ትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አቅጣጫ ሰጥተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመየድሬዳዋ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ  እና የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት የእቅድ ...
07/05/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ

የድሬዳዋ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ እና የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ፣ ም/አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ ፣ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች እንዲሁም የፍርድ ቤቶቹ ፕሬዚዳንቶች እና ባለሙያዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡
የተቋማቱ ሪፖርትም በዝርዝር ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በመጨረሻም የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር በሰጡት አቅጣጫም የ ፍርድፍ ቤቶቹሪፖርት መቅረቡ እና የታየው አፈጻጸም ጥሩ መሆኑን ገልጸው የተቋማት ዋነኛ ግብ የሆነው የተገልጋይ እርካታን ማሳደግ እንደመሆኑ ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሰራት ላይ ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ የዳሰሳ ጥናት ተጠናቆ ወደ ስራ እንዲገባ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የፍርድ ቤቶችን ስራዎች ይበልጥ ውጤታማ ሊያደርግ የሚችለው የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ውጤታማ ስራዎችን መስራት እንዲችል አስፈላጊው ጥረት ሊደረግ እንደሚገባ እንዲሁም በተቋማቱ የሚስተዋሉ ጥሩ አፈጻጸሞችን ይበልጥ ለማሻል ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

በአዲሱ ካሳ
ፎቶ፡- በእንድሪያስ ደሱ

#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!

ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et

ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d

ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/?si=TB3KelHlFoN6FhsP

ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1

ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤

ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን

የጀግኖች  አርበኞች  ቀንን አስመልክቶ  የተከበሩ  አቶ  አብዲ  ሙክታር  ያስተላቸፉት  እንኳን  አደረሳችሁ  መልእክት    የተከበራችው  የአስተዳደራችን  ነዋሪዎች  እና  መላው  ኢትዮጲ...
05/05/2026

የጀግኖች አርበኞች ቀንን አስመልክቶ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ያስተላቸፉት እንኳን አደረሳችሁ መልእክት

የተከበራችው የአስተዳደራችን ነዋሪዎች እና መላው ኢትዮጲያውያን አንኳን ለ85ተኛው የጀግኖች አርበኞች በአል በሰላም አደረሳችሁ ፡፡

በየአመቱ ሚያዚያ 27ቀን የምናከብረው የጀግኖች አርበኞች በአል ጀግኖች አናትና አባቶቻችን ድንበር ተሻግረው የሀገራችንን ሉአላዊነት ለመድፈር የተከፈተብንን የፋሽሽት ወራሪ ሀይል በተባበረ ኢትዮጲያዊ ክንዳቸው ድል አድርገው ለመላው ጥቁር ህዝብ ተምሳሌትነታቸውን የሳዩበት ታላቅ በአል ነው ፡፡

በወቅቱ የነበሩ ኢትዮጲያውያን ከግል ጥቅማቸው ይልቅ የሐገርን ጥቅም በማስቀደም የሀገር ፍቅር
ማለት ምን ማለት እንደሆነ በሂይወት መሰዋትነት ለቀሪው ትውልድ አስተምረው አልፈዋል ፡፡

የሀገር ፍቅር የሚገለፅባቸው መንገዶች አንዱ የሆነው በጦር ሜዳ የሚደረግ ጦርነት ኢትዮጲያውያን ያላቸውን ቆራጥነትና ጀግንነት በተግባር አሳይተዋል ፡፡
በመሆኑም ከዚህ ታሪካዊ የድል በአል የተነሳ የጦር ጀግንነታችንንም በልማቱም በመድገም ታላቅ አደራ ተጥሎ ብናል ስለዚህም መላው ኢትዮጲያውያን አገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ ለማስቀጠል እያንዳዳችን በተሰማራንባቸው የስራ መስክ በታማኝነት በታታሪነት አና በሐገር ፍቅር ስሜት ጠንክረን በመስራት ሀገራዊ ዜግነት ሐላፊነታችንን እንድንወጣ መልእክቴን አስተላልፋለሁ ፡፡

በድጋሚ ለጀግኖች አርበኞች በአል ቀን አንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ፡፡

ኢትዮጲያ በጀግኖች ልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር !!
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አብዲ ሙክታር

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ተጠሪ ተቋማት የ9ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ተገመገመ።የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ተጠሪ የተቋማት የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት...
28/04/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ተጠሪ ተቋማት የ9ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ተገመገመ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ተጠሪ የተቋማት የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ እንዲሁም የተጠሪ ተቋማቱ ሀላፊዎች እና ከፍተኛ ባለ ሞያዎች በተገኙበት ተገምግሟል።

በግምገማውም ላይ የዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ፣ ብዙሀን መገናኛ ድርጅት እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ፅህፈት ቤት የ9 ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱ ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዳል ።

በግምገማወ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር እንዳሉት የተጠሪ ተቋማቱ የ9 ወር እቅድ አፈፃፀም ያከናወናቸው ተግባሮች በተጨማሪም ከእቅድ ዉጪ የተሰሩ ስራዎችን በጋራ የምንገመግምበት እንዲሁም በቀጣይ የቀሩትን የሶስት ወራት ጊዜያት ደግሞ የ2018 እቅድ አፈፃፀምና ባለፉት አምስት አመታት ስንሰራ የነበርናቸውን ስራዎች ደግሞ እንደ ምክር ቤት የምናጠናቅቅበት አመት እንደመሆኑ መጠን ሁላችንም በምንሰራበት ቦታና ተቋም ስራችንን በአግባቡ ማከናወን ይገባል ብለዋል አፈ ጉባኤው አክለውም ባለን አቅም ባለን ባጀት እና ባለን ውስን የሰው ሀብት የአገልግሎት አሰጣጣችንን ከበፊቱ በተለየ መልኩ በማዘመን ስራዎችን መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል።

በመጨረሻም የስራ አቅጣጫ የሰጡት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ የተከበሩ ወይዘሮ ከሪማ አሊ ተጠሪ ተቋማቱ በላፉት ወራቶች ባከናወናቸው ስራዎች ተገልጋዮችን በማርካት በኩል አበረታች ስራዎችን ማከናወናቸውን አስታወቀው በበጀት አመቱ ማጠቃለያ እና የ አምስት አመቱ መጠናቀቂያ እንደመሆኑ መጠን በቀጣዮቹ 3 ወራቶች የተሰጡ ግብረ መልሶችን በአግባቡ በመጠቀም ለበለጠ ወጤት መስራት እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

ዜና ናትናይል ነጋሽ
ምስል እንድርያስ ደሱ

#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!

ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et

ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d

ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/?si=TB3KelHlFoN6FhsP

ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1

ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤

ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን

የቋሚ ኮሚቴዎች የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ተገመገየድሬዳዋ አስተዳደር ምክር  ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የምክር ቤቱ አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ...
24/04/2026

የቋሚ ኮሚቴዎች የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ተገመገ
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የ2018 በጀት አመት የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የምክር ቤቱ አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር እና ም/አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ በተገኙበት ተገምግሟል ፡፡
በመድረኩም የቋሚ ኮሚቴዎቹ የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በውይይቱ ማጠቃለያም የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር የአንድ ሀገርም ሆነ ተቋም ውጤታማነት ሊለካ የሚችለው የተቋሙን ራእይ ለማሳካት የሚታቀዱ እቅዶች በተያዘላቸው ጊዜና መለኪያ መሰረት ተፈጻሚነታቸው ሲረጋገጥ መሆኑን በመግለጽ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም ያቀዱትን የ9 ወራት እቅድ ወደተግባር ለመቀየር የሰሩት ስራ የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ የተከበሩ አፈጉባኤው አክለውም በቀሪ ጊዜያትም በኑሮ ውድነት እና በነዳጅ ስርጭት ዙሪያ በሚታዩ ጉዳዮች ላይ በቅንጅት መስራት እንዲሁም የተዋረድ ምክር ቤቶችን የመደገፍ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

በአዲሱ ካሳ
ፎቶ ፤- እንድሪያስ ደሱ

#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!

ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et

ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d

ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/?si=TB3KelHlFoN6FhsP

ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1

ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤

ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን

የወረዳ ም/ቤቶች የ9 ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ።የድሬዳዋ አስተዳደር  ምክር ቤት የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶችን የ2018 ዓ.ም የ 9 ወር  የእቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።በግምገማ መድ...
23/04/2026

የወረዳ ም/ቤቶች የ9 ወር እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶችን የ2018 ዓ.ም የ 9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።

በግምገማ መድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ፀሀፊ የተከበሩ አቶ ማርቆስ ባዩህ የወረዳ ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች ተገኝተዋል።
የወረዳዎቹ ሪፖርትም በዝርዝር ቀርቦ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል።

በመጨረሻም የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት ፀሀፊ የተከበሩ አቶ ማርቆስ ባዩ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት የቀረቡት ሪፖርቶች ጥሩ መሆናቸውን እና የወረዳ ምክር ቤቶች አፈጻጸም ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎችን እያሳየ መምጣቱን በመግለፅ በየ ወረዳው እየተሰሩ ያሉትን የከተማ ማደስ እና ማስዋብ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው፣ የወረዳ ምክር ቤቶች ቋሚ ኮሚቴዎችን በስራዎች ላይ ማሳተፍ እንደሚያስፈልግ እና ከመንግስት የሚሰጡ አቅጣጫዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል።

ዜና፦ ናትናኤል ነጋሽ
ፎቶ ፦ እንደሪያስ ደሱ

#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!

ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et

ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d

ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/?si=TB3KelHlFoN6FhsP

ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1

ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤

ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የግብርና ተፈጥሮ ሐብትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ  ኮሚቴ ድንገተኛ  የመስክ ምልከታ አካሄደ ።የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የግብርና ተፈጥሮ ሐብትና የአ...
16/04/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የግብርና ተፈጥሮ ሐብትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ድንገተኛ የመስክ ምልከታ አካሄደ ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የግብርና ተፈጥሮ ሐብትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ድሬ ሁለገብ የገበሬዎች ሀላፊነቱ የተወሰነ ህብረት ስራ ማህበራት ዩኒየን እና የግብርና ማአድንና ኢነርጂ ቢሮ ስር የሚገኘውን የእንሰሳት ሀብት ልማት ዳሬክቶሬት ዳሬክተርን የመስክ ምልከታ አካሂዷል።

በመሰክ ምልከተዉም የእንሰሳት ሀብት ልማት ዳሬክቶሬቱን የክሊኒክ፣ የንብረት ክፍሉን የካይዘን አተገባበር ስራዎችን አና የስራ አካባቢን ምቹ ከማድረግ አንፃር የተሰሩ ስራዎችን የተመለከተ ሲሆን በመቀጠልም የዮኒየኑን የመኖ ማቀነባበሪያ እና የእንቁላል ማስፈልፈያ(ኢንኩቤተር) ማሽኑን ቋሚ ኮሚቴው ምልከታ አድርጓል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የግብርና ተፈጥሮ ሐብትና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አህመድ አብዶ በሰጡት ሀሳብ የእንሰሳት ሀብት ልማት ቢሮ ዳሬክቶሬቱ ሰፊ የለውጥ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን እና በባለፋት ጊዜያት ከቋሚ ኮሚቴ የተሰጡ ግብረ መልሶችን ትኩረት በመስጠት እየሰሩ መሆናቸውንና በተለይ የካይዘን አተገባበር በተመለከተ ንብረት ክፉሉ ላይ የተሰሩ ስራውች ሚበረታቱ እና ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ እንዲሁም የስራቦታን ምቹ ከማድረግ አንፃር አካባቢን ግሪነሪ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ ገልፀዋል።
በመቀጠልም በዩኒየኑ የሚገኙትን የእንቁላል ማስፈልፈያ ማሽኖች ወደስራ መግባታቸውን እና እነዚህም ማሽኖች በሳምንት እሰከ 3500 እንቁላሎችን ማስፈልፈል መቻላቸውን በመግለፅ ይሄም ጥሩ ጅማሮ መሆኑን እና እነዚህንም ጅማሮዎች በቀጣይ ጊዜያት
አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል። ሰብሳቢው አክለውም የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኑ ጋር በተያያዘ በብልሽት ምክንያት ስራ ላይ አለመሆኑን እና ይሄንንም ማሽን ወደ ስራ ለማስገባት በትኩረት መስራት እንደሚገባም ገልፀዋል።

ዜና፦ ናትናኤል ነጋሽ
ፎቶ ፦ እንደሪያስ ደሱ

#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!

ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et

ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d

ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/?si=TB3KelHlFoN6FhsP

ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1

ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤

ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን

Address

Dire Dawa

Opening Hours

Monday 01:30 - 17:30
Tuesday 01:30 - 17:30
Wednesday 01:30 - 17:30
Thursday 01:30 - 17:30
Friday 01:30 - 17:30

Telephone

+251914994672

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire dawa Administration Council P posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dire dawa Administration Council P:

Share