13/08/2026
የዱብቲ ወረዳ የብልፅግና የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን በወረዳ ስር ከሚገኙ ቀበሌዎች እና የመንግስት ሰራተኛች የብልፅግና ሕብረት የኮሚሽን አባላት ጋር የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ አካሄደ።
በመድረኩም በአራቱ የትኩረት መስኮች ማለትም "በፓርቲ ፖለቲካዊ ጤንነት አጠባበቅ"፣ "በፓርቲ አባላት መብት አከበባር"፣ "በፓርቲ ሀብት አጠባበቅ" እና "በኮሚሽን ተቋማዊ አቅም ግንባታ" ስር የተካተቱ ግቦችና ዝርዝር ተግባራትንና የአፈፃፀም አቅጣጫዎች እንዲሁም የግምገማና የሪፖርት ስርአቶች ላይ ገለፃ ቀርቦ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
በመጨረሻም የዱብቲ ወረዳ የብልፅግና የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ሰብሳቢ አቶ ሀሰን መሀመድ አይዳሂስ እንደተናገሩት በቀረበው ዓመታዊ ዕቅድ ግቦችና ተግባራት ዙሪያ ከኮሚሽንና ከፖርቲ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት የኮሚሽን ተቋማዊ አቅምን በሚገነባና የአንድ አቅድ፣ አንድ ሪፖርትና አንድ ምዘና መርህን በመከተል የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ለመፈፀም መረባረበብ እንደሚገባ በማስገንዘብ ከቀበሌ ኮሚሽን ጋር የእቅድ ስምምነት ፊርማ በመከነወን የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።
!!
Dubte Daqaarak Leeda Partik Inispekshin kee meqem kaban Koomishin