የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Durame
  • የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት, Government Organization, Adilo, Durame.

በአዲሎ ከተማ የኮሪደር ልማት የወሰን ማስከበር ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ‎‎አዲሎ፣ ነሐሴ 29/2018/መንግስት ኮሙኒኬሽን/‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አዲሎ ከተማ የኮሪደር ልማት የወሰን ማስከ...
04/09/2026

በአዲሎ ከተማ የኮሪደር ልማት የወሰን ማስከበር ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ

‎አዲሎ፣ ነሐሴ 29/2018/መንግስት ኮሙኒኬሽን/
‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አዲሎ ከተማ የኮሪደር ልማት የወሰን ማስከበር ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።

‎በሥፍራው የተገኙት የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ብርሃኑ አበጌ እና የአዲሎ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ደግነት አብርሃም እንደገለጹት በከተማው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቱን በተሳካ ሁኔታ ለማስቀጠል በፕላኑ መሠረት ተለክቶ በኮሪደሩ ወሰን ውስጥ የገቡ አጥሮችን፣ ቤቶችንና የተለያዩ እንጨቶችን በቀለም የመለየት ተግባር እየተከናወነ ይገኛል።

‎በተጀመረው የመንገድ ዳር ወሰን ልየታ ስራው በቀለም ምልክት የተደረገባቸውን ንብረቶች ባለቤቶቹ እያነሱት እንደሚገኙ የጠቀሱት ኃላፊዎች ህብረተሰቡ ለልማቱ እያደረገ ላለው በጎ ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

‎የተጀመረው ልማት በተያዘለት ፍጥነት እንዲከናወን በኮሪደር ወሰን ውስጥ የሚገኙ ንብረቶችን ህብረተሰቡ በፍጥነት እንዲያነሳም ጥሪ አቅርበዋል።

‎ከነዋሪዎችም መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት የወሰን ልየታ የተጀመረባቸዉ ቦታዎች የመንገዱ ስፋት ለከተማው ከአሁኑ ተጨማሪ ውበት እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዉ የተጀመረዉ ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

‎የወረዳው ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ባለሀብትን በማስተባበር ለ20 ለሚሆኑ ለአቅም ደከማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።‎   ‎‎አዲሎ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም(መ ኮ ...
04/09/2026

‎የወረዳው ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ባለሀብትን በማስተባበር ለ20 ለሚሆኑ ለአቅም ደከማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።


‎አዲሎ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም(መ ኮ ጉ)
‎የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት አንድ ለበጎ ሥራ ቅን ልቦና ያለውን ባለሀብትን በማስተባበር ለ20 ለሚሆኑ ለአቅም ደከማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።


‎በመርሐ ግብሩ ላይ የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ባይዳ ጀታኖ እንደገለጹት ድጋፉ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመንን የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ሳይገጥማቸው እንዲጀምሩ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

‎ በቀጣይም የመማሪያ ቁሳቁስ ማሰባሰቡና የበጎ ፈቃድ ተሳትፎው እንደሚጠናከር ያስታወቁት ኃላፊው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው በትምህርት ዘመኑ እድሜው ለትምህርት የደረሰ ህጻን በመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታ እንዳይለይ ባለሀብቶችና መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፋቸውን አጠናክረው እንድቀጥሉ መልእክት አስተላልፈዋል



‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አጠቃላይ በወቅታዊ ንቅናቄ ስራዎች አፈጻጸም ዙሪያ ግምገማ ተካሄደ ‎‎አዲሎ፣ ነሃሴ 29/2018(መ ኮ ጉ)‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አጠቃላይ በወቅታዊ ንቅናቄ ስራዎች አፈጻ...
04/09/2026

‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አጠቃላይ በወቅታዊ ንቅናቄ ስራዎች አፈጻጸም ዙሪያ ግምገማ ተካሄደ

‎አዲሎ፣ ነሃሴ 29/2018(መ ኮ ጉ)
‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አጠቃላይ በወቅታዊ ንቅናቄ ስራዎች አፈጻጸም ዙሪያ ግምገማ መድረክ በአዲሎ ከተማ ተካሂዷል።

‎የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ወቅታዊ መንግስታዊ እና ፖለቲካዊ ስራዎች አፈጻጸም መድረኩን የከምባታ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ሞላልኝ አብርሃም እና የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ታደገ ደስታ ጋር በመሆን በጋራ መርተዋል፡፡

‎የግምገማ መድረኩ በዋናነት ያተኮረው በመደበኛና በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አፈፃፀም ፣በከተማና በገጠር እየተሰሩ ያሉ ኮርደር ልማት ሥራዎች አፈጻጸም ፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሻገር በሚሰሩ ሥራዎች ፈንድ አሰባሰብ ፣ በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ፣ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ፣ በስራ ዕድል ፈጠራ ፣ የተማሪዎች ምዝገባ እንዲሁም ሌሎች ወቅታዊ መንግስታዊ እና ፖለቲካዊ ስራዎች አፈጻጸም ከማሳካት አንፃር ጠቅለል ያለ ሪፖርት በንቅናቄው ተቋማት ኃላፊዎች እና በቀበሌ ደጋፊ አመራሮች በኩል ቀርቦ በተነሱ ነጥቦች ግምገማ ተደርጎ በውስንነት የተለዩ ነጥቦችን ለማሻሻል ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።

‎ብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት ለአቅመ ደካሞች የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ‎‎አዲሎ፣ ነሐሴ 29/2018/መንግስት ኮሙኒኬሽን/‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ብርሃን በጎ አድራጎት ድር...
04/09/2026

‎ብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት ለአቅመ ደካሞች የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

‎አዲሎ፣ ነሐሴ 29/2018/መንግስት ኮሙኒኬሽን/
‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት ለአቅመ ደካሞች የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

‎በወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት አዘጋጅነት ብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት የኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ከ80 ለሚበልጡ ማህበረሰብ ክፍሎች የትምህርት ቁሳቁስና የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል።

‎የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ተወካይ አቶ ሀብታሙ ታደሰ ብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት በወረዳው ከሚገኙ ቀበሌያት ለተወጣጡ 75 ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ተማሪዎች ቲሸርት እና የትምህርት ቁሳቁስ እንዲሁም ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው 10 አረጋውያን ደግሞ የብርድ ልብስ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል።

‎የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅሕፈት ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ታደገ ደስታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በወረዳው ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር በ16 ዘርፎች በጎ አገልግሎት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረው የአቅም ውስንነት ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች የመደገፍ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎ይህንን በጎ ተግባር ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ በማድረግ ሚናውን የተወጣው ብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅትን በወረዳው መንግስትና ፓርቲ ስም አመስግነዋል።

‎የብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት መሥራች ፖስተር አለማየሁ አሹሮ በበኩላቸው የታረዙትን በማልበስ እና በትምህርት ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዳይርቁ ቀዳሚ ተግባር አድርገው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

‎በጎ ሥራ ለመስራት ቅን ልቦናና መልካም አስተሳሰብ ያስፈልጋል ያሉት ፓስተር አለማየሁ በጎ ተግባራት አንዳችን ለአንዳችን በማድረግ ተግባሩን ሁላችንም ባህል ልናደርገው ይገባል ብለዋል።

‎በመርሃ ግብሩ ላይ የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅሕፈት ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ታደገ ደስታን ጨምሮ የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ተወካይ እና ባለሙያዎች፣ የብርሃን በጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ባለራዕይ መጋቢ አለማየሁ አሹሮ፣ የድርጅቱ ዋና አስተባባሪ አቶ ታምሬ ዮሐንስ እንዲሁም ሌሎችም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢፌዴሪ ባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች በ2019 ዓ/ም የከምባታ ብሔር የዘመን መለወጫ 'መሳላ' በዓል ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ተደረገ፣ከከምባታ ዞን አስተዳደር የተወከሉ አካላት መስከ...
04/09/2026

የኢፌዴሪ ባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች በ2019 ዓ/ም የከምባታ ብሔር የዘመን መለወጫ 'መሳላ' በዓል ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ተደረገ፣

ከከምባታ ዞን አስተዳደር የተወከሉ አካላት መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ/ም በተለያዩ ዝግጅቶች በአደባባይ በሚከበረው የመሳላ ክብረ በዓል ላይ በኢፌዴሪ ባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የሚመራ የሚኒስቴር መ/ቤቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲታደሙ ጥሪ አድርሰዋል።

የጥሪ መልዕክቱን ሚኒስቴር መ/ቤቱን በመወከል በኢፌዴሪ የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር የባሕል፣ እሴትና ሀገር በቀል እውቀት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እስከዳር ግሩም ተቀብለዋል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ ዘላቂ የትምህር...
04/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ

ዘላቂ የትምህርት ጥራት ለላቀ የመማር ውጤት እና ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በኤግዚቢሽኑ ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎች ቀርበው ለእይታ ክፍት የተደረጉ ሲሆን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በ2018 በጀት አመት ያከናወናቸውን ስራዎች የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ ርዕይ ቀርቧል።

03/09/2026
በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ወረዳዊ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ‎‎አዲሎ፣ ነሐሴ 27/2018/መ ኮ ጉ/‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ እና በስራ ዕድል ፈጠራና...
02/09/2026

በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ወረዳዊ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ

‎አዲሎ፣ ነሐሴ 27/2018/መ ኮ ጉ/
‎በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ እና በስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽህፈት ቤቶች አማካይነት የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ወረዳዊ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

‎በመድረኩ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለውም በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የንቅናቄ ሰነድ በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ባለሙያ በአቶ ሀብታሙ ታደሰ ቀርቦ ምክክር ተደርጓል።

‎የውጭ ሀገር ስራ ስምርት ዋና አላማ ህገወጥ ዝውውርን በመከላከል ዜጎች ህጋዊና ብቁ ስልጠና ወስደው በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻል እንደሆነም ተብራርቷል።

‎በመድረኩ የተገኙት የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አዲሴ መኮሬ እንደገለጹት የውጭ ሀገር የስራ ስምርት ዜጎች ተገቢውን የሥራ ስምሪት አግኝተው ኢኮኖሚያቸውን እንዲያሻሽሉ ለማስቻል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ትኩረት ያስፈልገል ብለዋል።

‎ህገወጥ የውጭ ሀገር ጉዞ በሀገር ኢኮኖሚ የሚያደርሰውን ከፍተኛ ጫና ለማስቀረት
‎ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሠራት እንዳለበትም አቶ አዲሴ አሳስበዋል።

‎የወረዳው ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽህፈት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ወሽመጦ በበኩላቸው
‎ህገወጥ ዝውውር በዜጎች አካላዊ እና ስነልቦናዊ ጫና የሚያስከትል መሆኑን አስገንዝበው በጋራ መታገል ይገባልም ብለዋል።

‎የመድረኩ ተሳታፊዎችም በአስተያየታቸው ህገ ወጥ ደላሎችን በመከላከል፣ የዜጎች ደህንነት በመጠበቅ፣ ህጋዊ የስራ ስምሪት መስመሮችን ለማጠናከር እና በወጣቶች ላይ የሚስተዋሉ እንግልቶችን ለመቅረፍ በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

‎በመድረኩ የወረዳው ደጋፊ አመራሮች፣ ባለድርሻ ተቋማት፣ የቀበሌ አመራሮች፣ የጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ በጎ መልዕክተኞች እና ሌሎችም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቴክኒክ ቡድን የመስክ ምልከታ ግምገማ አካሄደ‎‎አዲሎ፣ ነሐሴ 26/2018/መ ኮ ጉ/‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመ...
01/09/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቴክኒክ ቡድን የመስክ ምልከታ ግምገማ አካሄደ

‎አዲሎ፣ ነሐሴ 26/2018/መ ኮ ጉ/
‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቴክኒክ ቡድን በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የአደጋ ስጋት ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ አካሂዷል።

‎የምልከታ ቡድኑ በወረዳው ለአደጋ ስጋት ምላሽ ለመስጠት የተከናውኑ ተግባራት ተዘዋውሮ የተመለለከተ ሲሆን ከመስክ በኋላ ለወረዳው ግብረ-መልስ በመስጠት የታዩ ጥንካሬዎችንና ቀሪ ሥራዎችን በማመላከት ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

‎የተለያዩ የድጋፍ ኪቶች አሰባሰብ፣ የእህል ማከማቻ መጋዘን ዝግጅት፣ የሀብት አሰባሰብ እንዲሁም የመረጃ አያያዝ ስራዎች በጥሩ ደረጃ መከናቸውን ያነሰው የምልከታ ቡድኑ በጀመረው ግለት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስቧል።

በቴክኖሎጂ እና በእውቀት የሚጻፍ አዲስ ታሪክ፡ የባሕር በር አጀንዳችን እና የዲጂታሉ ትውልድ አሸናፊነት ***********************ለዘመናት ሀገራዊ ፈተናዎችን የመጋፈጥ እና የመሸጋ...
31/08/2026

በቴክኖሎጂ እና በእውቀት የሚጻፍ አዲስ ታሪክ፡ የባሕር በር አጀንዳችን እና የዲጂታሉ ትውልድ አሸናፊነት
***********************

ለዘመናት ሀገራዊ ፈተናዎችን የመጋፈጥ እና የመሸጋገር ታሪካችንን ስንቃኝ፣ ትውልዶች ነፃነትን ለማስጠበቅ በጽናት ተዋግተዋል፤ አባቶቻችንም የተበታተነውን ለመገንባት ሌት ተቀን ጥረዋል።

በዚህ ዘመን ግን የሀገሩን ነገ በመቀየር ሂደት ውስጥ የተሰለፈው አዲሱ ትውልድ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂ እና በፈጠራ የተቃኘ አዲስ የትግል ምዕራፍ ከፍቷል።

በአሁኑ ወቅት የሀገራት ድንበር በጦርነትና በኃያላን ጣልቃ ገብነት ሲታመስ፣ የዓለም ፍላጎትና ውድድር በቴክኖሎጂ፣ በኢኮኖሚ እና በፈጠራ በሚገነቡ አዳዲስ መስኮች ላይ ያተኮረ ሆኗል።

የዛሬው ወጣት በኮድ የሚገነባ፣ በፈጠራ የሚያስብ እና በቴክኖሎጂ መፍትሔ የሚፈልግ ሲሆን፣ የባሕር በር ጉዳይም ከምኞትና ከቁጭት ባለፈ በጠንካራ ኢኮኖሚ፣ በልማት፣ በዲፕሎማሲ፣ በእውቀት እና በቴክኖሎጂ በተገነባ አቅም የሚረጋገጥ መሆኑን በጥበብ ተረድቷል።

በየትኛውም መንገድ የውስጥም ሆነ የውጭ ጫናዎች ቢበዙብን፣ የቱንም ያህል ፈተናዎች ቢደቀኑብን ዓይናችን ከባሕር በር አጀንዳችን ፈጽሞ አይነቀልም፤ ይህ ትውልድም የታሪክ እና የጂኦግራፊ ስብራታችንን በጽናት ያሳካዋል።

አንድ መሐንዲስ የወደብ ቴክኖሎጂን ሲያጠና፣ አንድ ተመራማሪ የባሕር ኢኮኖሚን ሲመረምር ወይም አንድ የቴክኖሎጂ ባለሙያ የዘመናዊ ሎጂስቲክስ መፍትሔ ሲያመጣ እየተገነባ ያለው ከአንድ ሙያ በላይ የሆነ ሀገራዊ ህልውና ነው።

የዛሬው ትውልድ ቀድሞ ያልነበሩ የዲጂታል መሳሪያዎች በእጁ የሚገኙ በመሆናቸው፣ በአዲስ አበባ የሚገኝ ወጣት ከዓለም የቴክኖሎጂ ማዕከላት ጋር የመማር፣ የመወዳደር፣ ሀሳቡን ወደ ሶፍትዌር እና ፈጠራውን ወደ ንግድ የመቀየር ሙሉ አቅም አለው።

በቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ በእውቀት የታጠቀ እና በራዕይ የተመራ ትውልድ ሀገሩን አይቻልም ወደሚባለው ህልም የማድረስ ችሎታ ያለው ሲሆን፣ በወጣቶች እጅ ያለው ስልክ የመዝናኛ ብቻ ሳይሆን የመማሪያ፣ የፈጠራ እና የዓለም ግንኙነት መስኮት ሆኗል።

ዛሬ የሚጻፈው ኮድ የነገን ኢኮኖሚ ይገነባል፤ ዛሬ የሚደረገው ምርምርም የሀገርን የዲፕሎማሲና የባሕር በር አቅም ያጠናክራል።

ምናልባትም የባሕር በርን የሚያስመልሰው ትውልድ በባሕር ዳርቻ ላይ ቆሞ የሚያልም ሳይሆን በዩኒቨርሲቲዎች እየተማረ፣ በላቦራቶሪዎች እየተመራመረ፣ በኮምፒዩተር ኮድ እየጻፈ እና አዳዲስ ሀሳቦችን ወደ እውነታ እየቀየረ ያለው ትውልድ ነው።

ይህ ትውልድ ታሪክን በቁጭት ብቻ የሚያስታውስ ሳይሆን ታሪክን በአዲስ መልክ የሚሰራ፣ የባሕር በር መብታችንን በእውቀት፣ በፈጠራ፣ በጠንካራ ሀገራዊ አቅም እና በሰለጠነ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ በተግባር የሚያሳካ የጽናት ትውልድ ነው።

በልዩ እሸቱ

Address

Adilo
Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share