04/09/2026
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ የ2019 ዋና ዋና ግቦች እና በሚጠበቁ ውጥቶች ላይ ትኩረት ያደረገ የውል ስምምነት ተፈራረመ።
ነሐሴ 29/2018
ስምምነቱ በክልሉ ከሚገኙ ዞኖችና የልዩ ወረዳ ህብረት ሥራ መዋቅሮች ጋር የተደረገ ነው።
ስምምነቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጎዴቦ ከዞንና ከልዩ ወረዳ ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር ተፈራርመዋል።
ይህም በ2018 የተገኙ ስኬቶችን በ2019 በተሻለ መንገድ አስፍቶና አልቆ ለማስቀጠል ጉልህ አበርክቶ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።