Central Ethiopia Regional state OCAA

Central Ethiopia Regional state OCAA Official page of Central Ethiopia Regional State Education and Training Quality Regulation Authority(CERS ETQRA)

09/06/2026
“ትውልድን በሥነ-ምግባር ተቋምን በአሠራር እንገነባለን!!”የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት...
04/06/2026

“ትውልድን በሥነ-ምግባር ተቋምን በአሠራር እንገነባለን!!”

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ለሴክተሩ አመራሮችና ሠራተኞች በኮሚሸኑ ተልዕኮዎች ላይ በማተኮር ሥልጠና ሠጥቷል፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዱራሜ ክላስተር የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት በሙስና መከላከልና መልካም ሥነ-ምግባር ግንባታ የሥልጠና ርዕስ ላይ በማተኮር ሥልጠና ሠጥቷል፡፡ሥልናውን የተሳካ ለማድረግ በባለሥልጣኑ መ/ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች ደረጃ የተለየ ትብብርና ቅንጅት ሥራ መሠራቷን የባለሥልጣኑ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሪክቶሪት የሆኑት ወ/ሮ አሰገደች ዴቢሣ በየሥልጠናውን መረሃ ግብር በማስመልከት በአቀረቡት መልዕክታቸው ገልጸዋል፡፡

የሥልናውን ሠነድ ያቀረቡት አቶ ታረቀኝ ዋኖሬ የዱራሜ ክላስተር የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ትብብርና ቅንጅት ፎረም ሰብሳቢ ሲሆን መድረኩን የተሳካ ለማድረግና ተሣታፊውን ለማነቃቃት ትምህርት ሰጪና አዝናኝ ሥነ-ጽሁፍ በአቶ ጥላሁን ገብሬ አቅራቢነት ቀርቦ ከታዳሚው አድናቆት ተችሮለታል፡፡ሥልጠና ሲሰጥ የተመረጠው የሥልጠና ርዕሱ በሥራ ሥነ-ምግባር ምንነትና አስፈላጊነት ላይ የተቋሙ አመራሮችና ባለሙያዎች በቂ ግንዛቤ በመያዝ የፀረ-ሙስና ትግሉ አካል እንዲሆኑ በማድረግ ላይ ያለመ ነው ፡፡ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኩ ለአንድ ቀን የተሠጠ ሲሆን በመድረኩ የተገኙ አጠቃላይ ተሳታፊዎች 65 መሆናቸዉ ተመዝግቧል፡፡

በበሥልጠናዉ መድረኩ ከአጀማመር እሰከ ማጠቃለያ ምዕራፍ ድረስ የባለሥልጣኑ ሁሉም የሥራ ኃላፊዎችና ፈፃሚ ባለሙያዎች ተሟልተው የተገኙ ሲሆን የዱራሜ ክላስተር የቅንጅትና የትብብር ፎረም አመራር አባላትም በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተዋል፡፡ በዚሁ መሠረት መድረኩን ይበልጥ የተሻለ ለማድረግ ልዩ ልዩ የግንዛቤ መፍጠሪያ ብሮሼሮች፣ እስቲኬሮች እና ትላልቅ ባነሮች አስቀድመው የተዘጋጁ ሲሆን የሻይ ቡና እንዲሁም የምሣ መስተንግዶ በበቂ ሁኔታ እንዲሰናዳ ተደርጓል፡፡

ግንቦት 2018 ዓ/ም

27/05/2026

የማዕከለዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ በዓሉ የሰላም የጤና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል ::

የማዕከለዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለመላው ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው  በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ በዓሉ የ...
12/04/2026

የማዕከለዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለመላው ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ በዓሉ የሰላም የጤና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል ::

የማዕከለዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን 1447ኛ የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም   አደረሳችሁ አደረሰን...
19/03/2026

የማዕከለዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን 1447ኛ የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን እያለ በዓሉ የሰላም የጤና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል ::
ዒድ ሙባረክ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኢ/ፌ/ድ/ሪ/ ስራና ክህሎት ሚንስቴር ሀገር አቀፍ የሙያ ደረጃ ባወጣለቸዉ 26 የሙያ አይነቶች ከክልሉ ሁሉ...
12/03/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኢ/ፌ/ድ/ሪ/ ስራና ክህሎት ሚንስቴር ሀገር አቀፍ የሙያ ደረጃ ባወጣለቸዉ 26 የሙያ አይነቶች ከክልሉ ሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በሙያዊ ክህሎታቸዉ እዉቀታቸዉና ስነ-ምግባራቸ ብቁና ግንባር ቀደም የስራ ገብያዉ (ኢንዱስትሪዉ) ወካይ የሙያ መዛኝ እንዲሆኑ ለተመለመሉ ባለሙዎች ከመጋቢት 01-04/2018 አ.ም በዱራሜ እየተሰጠ በሚገኘዉ የሙያ መዛኝነት ስነ-ምዘና ዘዴ ስልጠና ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ደይሬከተር አቶ ራህመቱ ቦካ ለእጩ የሙያ መዛኞቹ የስራ ገብያዉ .(ኢንዲስትሪ) ወካይነት ሚናቸዉን በዕዉቀት በክህሎትና ሙያዊ ስነ-ምግባር በመላበስ ሙያዊ ሀላፊነታቸዉን እንዲወጡና በቀጣይ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የትምህርትና ስልጠና ጥራት መስጠበቂያ ስራዎችን ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻዎችና ኢንዱስትሪዎች ጋር በትብብርና በጋራ በትኩረት ባለስልጠኑ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ዋና ዳይሬክተሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ወደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሲያድግና ሲለወጥ የስያሜና አደረጃጀት ለዉጥ ብቻ ሳይሆን በክልሉ የሚከሰቱ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና እና የትምህርትና የስልጠና ጥራት ችግሮችን መቅረፊያ በቴክኖሎጂ የታገዘ ስርአት መዘርጋትና ስራላይ ማዋል ተገቢ የሰዉ ሀይል እና የተቋም ግምባታ ስራዎችን በመስራት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና እና የትምህርና ስልጣና ጥራት ቁጥጥርን በተገቢዉ ሀላፊነት ለማስጠበቅ እንደ ሆነ ለስልጠና ተሳታፊ እጩ የሙያ መዛኞች አሳዉቀዋል፡፡

መጋቢት 02 / 2018 ዓ.ም
ዱራሜ

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከኢትዮጲያ ደረጃ መዳቢ ኢንስትቲዩት ጋር በመፈራረም የተከናወነው የ ISO 17024 ትግበራ የታስክ ፎርስ ስልጠ...
28/02/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከኢትዮጲያ ደረጃ መዳቢ ኢንስትቲዩት ጋር በመፈራረም የተከናወነው የ ISO 17024 ትግበራ የታስክ ፎርስ ስልጠና ቀጠይ ክፍልና የመጀመሪያ ዙር የሰነድ ዝግጅት የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እና አመራሮች የኢንስቲቱዩቱ አሰልጣኞች እና የባለስልጣኑ ታስክ ፎርስ አባለት በተገኙበት በቀን የካቲት 9/2018 ዓ.ም በቡታጂራ ከተማ ብራይት ሆቴል የስብሰባ አደራሽ ተጀምሯል :: የISO 17024 ትግበራ የመጀመሪያ ዙር ሰነድ ዝግጅት ታስክ ፎርሱና የኢንሰስቲቱዩቱ አሰልጣኞች በቡታጂራ ከተማ ብራይት ሆቴል ላለፉት 15ተከታታይ ቀናት በአመራር ድጋፍና ክትትል የሰነድ ዝግጅት ሲያካሄዱ ቆይተው በቀን 21/2018 ዓ.ም የባለስልጣኑ ም/ዋና ደይሬክተርና የባለስልጣኑ ISO ትግበራ አስተባባሪዎች የተሰሩትን ስራዎች በመገምገም እና ቀጣይ ተግባራት ሂደት በማመለከት ተጠናቋል::

የምዘና መረጃ አስተዳደር ስርኣትን የሚያዘምን ሲስተም ለምቶ ወደ ትግበራ ሊገባ ነው።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከሚሰጣቸው ዋናዋና አገልግ...
31/12/2025

የምዘና መረጃ አስተዳደር ስርኣትን የሚያዘምን ሲስተም ለምቶ ወደ ትግበራ ሊገባ ነው።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከሚሰጣቸው ዋናዋና አገልግሎቶች ውስጥ የሆነው የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና ስርኣትን ከጅምር እስከ ፍጻሜ ያለውን አሰራር ለማዘመን የሚያስችል ሲስተም በባለስልጣኑ ሶፍትዌር ኢንጅነሮች ለምቶ ወደ ስራ ለማስግባት የሚያስችል ስልጠና ለባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች፣የማኔጅመንት አካላትና ለአጠቃላይ ሰራተኞች ስልጠና ተዘጋጅቶ መሰጠት ተጀምሯል።
በስልጠና ፕሮግራሙ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ስልጠናውን ያስጀመሩት የባለስልጣኑ ምክትል ዳይሬክተርና የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት የተከበሩ አቶ ቀድሩ አብደላ ስለ ምዘና መረጃ አስተዳደር መዘመን አስፈለጊነት አንስተዋል። ሀላፊው እንዳሉት ተቋም ማዘመን አሁናዊ አስፈላጊነትን አንስተው እንደ መንግስትም የተያዘውን የዲጅታል ኢትዮጵያ 2030 ትግባራ በየዘርፉ ሀላፊነትን በአግባቡ መወጣት እንደሚገበ አሳስበዋል። ዲጅታላይዜሼን እና ተቋም ማዘመን እንዲሁም የምዘና መረጃን ከምዘና ጣቢያዎች ከመቀበል ጀምሮ እስከ ኦንላይንና ዳታ አርካይቪንግ ድረስ ያለው ስርኣት በማዘመን በሰርተፊኬሽ ሂደት ውስጥ የተጀመረውን የISO 17024 አለም ኣቀፍ እስታንዳርድ ለማስተግበር ቁልፍ ሚና እንዳለው ሀላፊው አክለው አንስተዋል።
ስልጠናው ለሁሉም ዳይሬክቶሬቶች በየዘርፍና እንደ ፕሪቬሌጃቸው ወሰን በተግባር የሚሰጥ ሲሆን በዛሬው እለትም ለሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዛና ዳይሬክቶሬት መስጠት የተጀመረ ሲሆን አጣቃላይ መርሃ ግብሩ በክልሉ ለሚገኙ ፍቃድ ላላቸው ሁሉም የምዘና ጣቢያዎች የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል።
ይህንን ዴስክቶኘ አኘልኬሽን ሶፍትዌር ከክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ የተወጣጣ የአመራርና ቴክኒካል ኮምቴ ገምግሞ ሶፍትዌሩ ሥራ ላይ እንድውል የወሰነና በቀጣይ ሙሉ ለሙሉ ወደ ዌብቤዝድ ክላውድ ሠርቪስ /Web based Cloud Service/ መሻሸል / Upgrade/ መደረግ እንዳለበት ተወስኖ ወደ ሥራ እንዲገባ አቅጣጫ ተቀምጦ ከሁለቱም መ/ቤት በአመራር የሚመራ የባለሞያዎች ቡድን ተዋቅሮ እየተሠራ ይገኛል ።

በ23/03/2018 ዓ.ም ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮች ማናጅመንት አባለት እና ለመላዉ የባለስልጣኑ ሰራተኛ  እንደ ሀገር ህዳር ...
02/12/2025

በ23/03/2018 ዓ.ም ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮች ማናጅመንት አባለት እና ለመላዉ የባለስልጣኑ ሰራተኛ እንደ ሀገር ህዳር 23 የሚከበረዉን የኤችአይቪ/ኤድስ ቀን አስመልክቶ ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይቪ /ኤድስን ምላሽን ዘላቂነት እናረጋግጥ በሚል መሪቃል ከከምባታ ዞን ጤና መምሪያና ጸረ-ኤች አይቪ /ኤድስ ማህበር በተጋበዙ በለሙዎች የግንዘቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

29/11/2025

Address

Central Ethiopia Region
Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Regional state OCAA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share