03/09/2026
በትምህርት ስርዓት ውስጥ የመምህራን ሙያዊ ብቃት ማደግ ያለው አበርክቶ
በትምህርት ስርዓት ውስጥ የመምህራን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎች ሙያዊ ብቃት ማደግ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ዋናው መሠረት ነው::
የዚህን ተልዕኮ ስኬት ለማረጋገጥ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት 3 ዓመት ጊዜያት በርካታ ተግባራትን በማከናወን ተስፋ ሰጪ ለውጦችን አስመዝግቧል::
⭕️የአካባቢ ቋንቋዎችን ማበልጸግ እና ብዝሃነትን ማጎልበት
የቋንቋ እና የባህል ብዝሃነትን ከትምህርት ስርዓቱ ጋር ለማቀናጀት በተደረገው ጥረት በሆሳዕና ኮሌጅ የየምሳ፣ ሀላቢሳ፣ ጠምባሪሳ፣ ጉራጊኛ እና ማረቆኛ አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ትምህርት ክፍሎች ተከፍተው ስራ ጀምረዋል::
ይህም መምህራን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ተሰልጥነው ተካኪ ትውልድን በብቃት እንዲያፈሩ ትልቅ እድል ፈጥሯል::
⭕️የስልጠና ፕሮግራሞች ማስፋፊያ እና አቅም ግንባታ
የትምህርት ሽፋንን ለማሳደግ በሆሳዕና፣ ዱራሜ፣ ወራቤ እና ወልቂጤ የሳምንት መጨረሻ (Week-end) ፕሮግራሞች በመከፈታቸው የቅድመ-አንደኛ መምህራን ሽፋን ከ27.5% ወደ 29.5% ማደግ ችሏል::
ከዚህ በተጨማሪ በክረምት ወቅት 1,200 የቅድመ-አንደኛ መምህራን ስልጠናቸውን አጠናቀዋል::
⭕️የመምህራን እና አመራሮችን ክፍተት ለመሙላት ከተከናወኑት አቅም ግንባታዎች መካከል፡
የ2ኛ ደረጃ ተፈጥሮ ሳይንስ መምህራንልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና፣የማህበራዊ ሳይንስ መምህራን ስልጠና እና የትምህርት ቤት አመራሮችየአመራርነት ብቃት ማጎልበቻ ስልጠና ተጠቃሽ ናቸው።
በዘርፉ እየተደረገ ያለው ዘርፈ ብዙ ርብርብ የክልሉን የትምህርት ጥራት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ያፋጥነዋል::