Gofa Zone Government Communication Affairs Department

Gofa Zone Government Communication Affairs Department ይህ የጎፋ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ትክክለኛ የፌስቡክ ገጽ ነው።
(1)

የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ የዓለም ስጋት በመሆኑ፣ ጉዳዩን በተገቢው ተረድቶ ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የክልሉ  የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣ አስታ...
02/09/2026

የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ የዓለም ስጋት በመሆኑ፣ ጉዳዩን በተገቢው ተረድቶ ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የክልሉ የአካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣ አስታወቀ

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

ባለስልጣኑ ክልላዊ የአካባቢ ሁኔታ ለውጥ ዘገባ በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ለመመዘን በክልሉ ከሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑም ተገልጿል

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ፣ የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ አሁን ላይ የዓለም ስጋት መሆኑን ገልጸዋል።

ስጋቱን ለመከላከል ጉዳይን በተገቢው ደረጃ ተረድቶ፣ በክልሉና በማህበረሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በጥናትና በመረጃ ለይቶ እንዲሁም በጠንካራ አመራር መምራትና ተገቢ ምላሽ መስጠት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በክልሉ የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምር የተደገፉ ሥራዎችን በማጠናከር፣ የአካባቢና የአየር ንብረት ችግሮችን በትክክል ለይቶ ለመፍታት መስራት እንዳለባቸውም አስረድተዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ልዩ አማካሪ ቦሻ ቦንቤ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በዘርፉ የሚካሄዱ ጥናቶችና የሚገኙ መረጃዎች በሪፖርት ደረጃ ብቻ ሳይቆዩ ወደ ተግባራዊ ውሳኔና ወደ መፍትሔ ተኮር ሥራዎች እንዲቀየሩ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል።

በመረጃዎች ጥራትና ተአማኒነት ላይ ትኩረት እንዲሰጥም ዶ/ር ቦሻ አሳስበዋል።

የክልሉ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቴ ግጄ በበኩላቸው፣ ባለስልጣኑ በክልሉ ወቅታዊ የሆኑ የአካባቢና የአየር ንብረት ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሆነ ገልጸው ።

ጥናቱ የክልሉን የባለፉት አምስት ዓመታት የአካባቢ ሁኔታ በተጨባጭ መረጃና በሳይንሳዊ ምርምር ለመመዘን ትኩረት ማድረጉን አብራርተዋል ።

ጥናቱ ያተኮረባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች የመሬት አጠቃቀምና የአፈር ጤንነት፣የውሃ ሀብቶችና የሥነ-ምህዳር፣የሥርዓተ-ምህዳርና የብዝሃ ሕይወት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ሁኔታና ተጽዕኖዎች እንዲሁም የቆሻሻ አያያዝና ብክለት መሆናቸውን አስረድተዋል ።

ጥናቱ ማህበረሰብና የተለያዩ የውሳኔ ሰጪ አካላት ስለ አካባቢው ሁኔታ ወቅታዊ፣ ትክክለኛ፣ ተዓማኒና ጠቃሚ መረጃ እንዲያገኙ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረውም ገልጸዋል።

በመድረኩ የጥናቱን ሥራ በሙያዊና በተቀናጀ መንገድ ለማካሄድ የተዘጋጀው የፕሮጀክት ፕሮፖዛል ሰነድ ቀርቦ በመገምገም፣ በክልሉ ከሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትብብር ወደ ተግባር እንዲገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በሚቀጥሉት አስር ቀናት ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ደቡብ ምዕራብና መካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል፤ ነሐሴ 27/2018(ኢዜአ) ፦ በሚቀጥሉት...
02/09/2026

በሚቀጥሉት አስር ቀናት ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ደቡብ ምዕራብና መካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል

፤ ነሐሴ 27/2018(ኢዜአ) ፦

በሚቀጥሉት አስር ቀናት ምዕራብ፣ሰሜን ምዕራብ፣ደቡብ ምዕራብ እና መካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው የኢትዮጵያ የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ መሰረት በሚቀጥሉት አስር ቀናት ምዕራብ፣ሰሜን ምዕራብ፣ደቡብ ምዕራብ እና መካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል።

ሁሉም ሸዋ ዞኖች፣ አኝዋክ፣ ከፋ፣ ምዕራብ ኦሞ፣ ጉራጌ ፣አዲስ አበባ ፣ድሬዳዋ፣ የምዕራብ ፣የሰሜን ምዕራብ ፣መካከለኛው፣ ምሥራቅ እና ደቡብ ትግራይ ዞኖች ፣የሲዳማ አብዛኛው የክልሉ ዞኖች ደግሞ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።

በምስራቅ ፣ በሰሜን ምሥራቅና በመካከለኛው ኢትዮጵያ አካባቢዎች ዝናብ የሚቀንስ ሲሆን፤ በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ የሃገሪቱ አካባቢዎች ደግሞ በስርጭትም በመጠንም የተሻለ ዝናብ ያገኛሉ።

02/09/2026

የጎፋ ዞን የቱሪዝም አምባሳደር ከተጓዡ ጋዘጤኛ ሄኖክ ስዩም ጋር የተደረገ ቆይታ ፦

‎ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

02/09/2026

ታላቅ የምረቃ ጥሪ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ እና ላሃ ከተማ አስተዳደር:-

በዕለተ ቅዳሜ ቀን 30 -12-2018 ዓ.ም በፍጹም መቅረት አይቻልም!

እንደሚታወቀው ታታሪው የመሎ ኮዛ ወረዳ ህዝብና መንግስት የመሠረተ ልማት ፍላጎቱን በራስ ጥረት ለመፍታት በርካታ የማሽነሪዎች ግዢ አከናውኗል።

ቅዳሜ ቀን 30 -12-2018 ዓ.ም ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በላሃ ከተማ ሁለገብ ስታድየም በይፋ የምረቃ ሥነ ሥርዐት ይካሄዳል።

በመሆኑም በኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ የምትኖሩ የጎፋ ዞን የመሎ ኮዛ ተወላጆች እና ወዳጆች በስፍራው ተገኝታችሁ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆን ሲሉ የመሎ ኮዛ ወረዳ እና የላሃ ከተማ አስተዳደር ጥሪያቸውን ያስተላልፋሉ።

#ለልማት ሁሌም በጋራ እንቆማለን!!

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
02/09/2026

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች

ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”

ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

በጎፋ ዞን የ16 ቅድመ አንደኛ ደረጃ አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች የግንባታ አፈጻጸም ተገመገመሣውላ፣ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ምበጎፋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እየተገነቡ ያሉ 16 የቅድመ አንደ...
02/09/2026

በጎፋ ዞን የ16 ቅድመ አንደኛ ደረጃ አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች የግንባታ አፈጻጸም ተገመገመ

ሣውላ፣ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

በጎፋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እየተገነቡ ያሉ 16 የቅድመ አንደኛ ደረጃ አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች የግንባታ ደረጃ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችና በሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገምግሟል።

የግንባታ አፈጻጸሙ ከጎፋ ዞን አስተዳደር ጋር በመቀናጀት የተገመገመ ሲሆን፣ በውይይቱ የግንባታዎቹ ወቅታዊ አፈጻጸም፣ ያጋጠሙ ችግሮችና በቀጣይ ሊወሰዱ የሚገባቸው እርምጃዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ፣ በክልሉ እየተገነቡ ያሉ የአፀደ ሕፃናት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የነገ ትውልድ መሠረት የሚጣልባቸው እና በትምህርት ዘርፉ የተፈጠረውን ክፍተት ከመሠረቱ ለመቅረፍ ትልቅ አስተዋፅኦ የሚኖራቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።

እንደ አቶ አብዮት ገለጻ፣ የትምህርት ስብራቱን ለመቅረፍ ከታች ጀምሮ ጠንካራ የትምህርት መሠረት መጣል በመሆኑ፣ የአፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች ግንባታ ትኩረት የተሰጠው የሥራ መስክ ነው።

አያይዘውም፣ በዞኑ ለመገንባት የተያዙት ትምህርት ቤቶች በውል መሠረት ተጠናቀው ለአገልግሎት ሊበቁ የተሰጠው ጊዜ እያለቀ በመሆኑ፣ እንዲሁም የመማርና ማስተማር ሥራ የሚጀመርበት ወቅት እየተቃረበ በመሆኑ የግንባታ ሥራው በፍጥነት መከናወን እንዳለበት በአጽንኦት ገልጸዋል።

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ በበኩላቸው፣ ከግንባታ ተቋራጮች ጋር ውል በመግባት የተጀመሩ ሥራዎች በአጀማመራቸው ከፍተኛ መዘግየት እንደታየባቸው ገልጸው፣ ተቋራጮቹ የሥራ አፈጻጸማቸውን በድጋሚ በመገምገም ለሕብረተሰቡ ተጠቃሚነት ቅድሚያ በመስጠት ሥራቸውን ማፋጠን እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

አክለውም፣ በሕብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወኑ ሥራዎችን ከወረዳዎች ጋር በመቀናጀትና በትብብር መሥራት እንደሚያስፈልግ ገልጸው፣ ለግንባታዎቹ መጠናቀቅ የዞኑ አስተዳደር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የትምህርት ዘርፍ አጠቃላይ ኃላፊ አቶ ኢሳይያስ እንድርያስ፣ የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ የመንግሥት ሁለተኛው የኮሪደር ልማት ሥራ አካል መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ሀገር 1,400 ትምህርት ቤቶች ለመገንባት ታቅዶ ሥራ ላይ መሆኑን የገለጹት አቶ ኢሳይያስ፣ ከእነዚህ ውስጥ 140 ትምህርት ቤቶች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገነቡ ሲሆን፣ በጎፋ ዞን 16 የቅድመ አንደኛ ደረጃ አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤቶች እየተገነቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም፣ ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት ከተቋራጮች ጋር የጊዜ ገደብ ያለው የውል ስምምነት ቢደረግም፣ አንዳንድ ተቋራጮች በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ መሠረት ሥራቸውን በማፋጠን ለማጠናቀቅ ያልተጠበቀ ክፍተት እንዳሳዩ አንስተዋል።

በመድረኩ በየወረዳዎቹ እየተገነቡ ያሉትን ትምህርት ቤቶች የግንባታ ደረጃ የሚያሳይ ሰነድ ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን፣ ተቋራጮችም በግንባታ ሂደቱ ያጋጠሟቸውን ችግሮችና ማስተያየቶች አቅርበዋል።

በዚህም በቀጣይ ያጋጠሟቸውን ችግሮች በፍጥነት በመፍታት የግንባታ ሥራቸውን በማፋጠን እስከ መስከረም 15/2019 ዓ.ም ድረስ ግንባታዎቹን አጠናቀው ለአገልግሎት ለማስረከብ ተቋራጮቹ ቃል ገብተዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጎፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ማነጅመንቶች ፣የወረዳና ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤቶች ማኔጅመንቶች የ2018 ዓ.ም አፈፃፀም ግምገማ የሁለተኛ ቀን ውሎ ቀጥሏል ።ሣውላ፦ነሀ...
02/09/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጎፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ማነጅመንቶች ፣የወረዳና ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤቶች ማኔጅመንቶች የ2018 ዓ.ም አፈፃፀም ግምገማ የሁለተኛ ቀን ውሎ ቀጥሏል ።

ሣውላ፦ነሀሴ 27/2018 ዓ/ም

በሁለተኛው ቀን መድረክ የአመራሩ የአመለካከት ሁኔታ፣ የተግባር አፈፃፀም ፣የሥነ ምግባር ችግሮች እንዲሁም ኪራይ ሰብሳቢነትንና ብልሹ አሠራርን የመታገል ቁርጠኝነት ላይ ያተኮረ ሰፊና ጥልቅ ግምገማ እየተካሄደ ይገኛል ።

አመራሩ የህዝቡን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የሚሰጡ ተልዕኮዎችን በባለቤትነትና በቁርጠኝነት የመውሰድና የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በትኩረት በመምራት የአገልግሎት አሰጣጥ አስተሳሰብን በመገንባት ፖሊስ አመራሩ የአመለካከት ችግሮችን መቅረፍ እንዳለበት ተገምግሟል።

አመራሩ በተግባር አፈፃፀም ወንጀልን ከመከላከል የህግ የበላይነትን ከማስከበር የማህበረሰብ ዓቀፍ የፖሊስ አገልግሎትን በማጠናከር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችና ክፍተቶች ላይ እየተገመገመ ይገኛል ።

በተለይ እንደ ጎፋ ዞን ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውሮች መኖርና መከማቸት፣ፖሊስ አባላት ህገ ወጡ ላይ መሳተፍ ለዚህም የፖሊስ አመራሩ ሙያዊ ግዴታዎችንና ተልዕኮዎችን በአግባቡ ያለመወጣት ፣አካባባዊነት መታየት ፣የሥራ ተነሳሽነት መጓደል ፣ራሱን ያለማብቃት ችግሮች በጥልቀት እየተገመገሙ ይገኛል ።

የሥነ ምግባር ችግሮች መኖር ለህዝብ አገልግሎት ታማኝ ያለመሆን ብልሹ አሰራሮች መታየት ፖሊስ ፌከኛ መሆን ለዚህም አመራሩ ለህዝብ አገልግሎት ታማኝ እና የፀዳ እንዲሆንና ትኩረት እንድሰጥበት ተደርጓል ።

ብልሹ አሰራሮችንና የኪራይ ሰብሳቢነት እይታዎችን በግልጽነት መታገል በተለይ በትራፍክ ዘርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየታዩ ያሉ ችግሮች ካለመቅረፋቸው ከሙስና የጸዳና ግልጽነት ያለው እንድሆን የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት እንድዘረጉ ተገምግሟል።

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው ።ነሐሴ 27/2018 ዓ.ምእየተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላ...
02/09/2026

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው ።

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

እየተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶችን እንዳስመዘገበች የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ የዘንድሮ የጳጒሜን ቀናት የሚከበሩበትን ዓውድ፣ የቀናቱን ስያሜ እና መሪ መልእክት ይፋ ያደረገበትን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

መግለጫዉን የሰጡት የአገልግሎቱ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ከበደ ዴሲሳ “ጳጒሜን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ወር ብሎ ለማክበር የሚያስችሉ ስኬቶች እየተጠናቀቀ ባለው ዓመት መመዝገባቸውን ገልጸዋል ፡፡

ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ቴክኖሎጂ ነክ ዓመታዊ ስኬቶችን በመግለጫቸዉ ያነሡት ሚኒስትር ድኤታዉ የጳጒሜን ቀናት በልዩ ልዩ ስያሜዎች እና ኹነቶች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አመላክተዋል፡፡ አካታች፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተሳተፉበት ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተካሄደበት፣ ኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በፅኑ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ አካታች እና የነበሩ ልዩነቶችን በመፍታት የጋራ ትልሞች ላይ እንዲተኮር የሚያስችል ሀገራዊ ምክክር በስኬት የተጠናቀቀበት፣ የውስጥ አንድነቷ የተጠናከረ እና የዲፕሎማሲ ዐቅሟ ያደገች ኢትዮጵያ የታየችበት ዓመት እንደነበር አቶ ከበደ በመግለጫቸዉ አመላክተዋል፡፡

ከኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አንጻር የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመፍጠር በወቅታዊ ዓለማቀፋዊ ቀውሶች ጭምር ታልፎ ስኬት የተመዘገበበት፣ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር የተቻለበት፣ የዕዳ ጫና በከፍተኛ ደረጃ የቀነሰበት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅም ከ1.5 ትሪሊዮን ብር የተሻገረበት፣ የኢንዱስትሪ ምርታማነት እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት ታሪካዊ ዕድገት ያስመዘገበበት፣ የወጪ ንግድ ገቢ ከ10.2 ቢሊዮን ዶላር የተሻገረበት፣ በአንድ ዓለማቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ብቻ ከ13.2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት የመግባቢያ ሰነድ የተፈረመበት እና በአብዛኛዉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወደ ማውጣት ደረጃ የተሸጋገሩበት፣ የግብርና ምርት እና ምርታማነት በጋ ከክረምት በግብዓት አቅርቦት ታግዞ በከፍተኛ ደረጃ የጨመረበት ስኬታማ ዓመት ነበር፡፡

የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ያስቻሉ ከ100 በላይ የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎቶች የተስፋፉበት፣ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በፅኑ መሠረት የሚያስቀምጥ እና ማኅበራዊ መስተጋብርን የሚያጎለብት ስኬታማ ምክክር የተደረገበት፣ የሕዝቡን የማኅበራዊ መሻቶች ለማሳካት ሰፋፊ የበጎ አድራጎት እና የመሠረተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎች የተከወኑበት በውጤቱም ኢትዮጵያን ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበት ዕድገት ማሸጋገር የተቻለበት ዓመት እንደነበር ክቡር አቶ ከበደ በመግለጫቸዉ አመላክተዋል፡፡

በታዳሽ ኃይል አቅርቦት፣ ግዙፍ መሠረታዊ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት እና ዐዳዲስ መሠረተ ልማቶችን ወደ ግንባታ በማስገባት የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶችንም ዳስሰዋል፡፡ የዐፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና የቢሾፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጀመር ከሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል በክቡር ሚኒስትር ድኤታዉ በአብነት ተነሥተዋል፡፡ እነዚህን ስኬቶች፣ ከተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እና በዕቅድ ከተያዙ ሀገራዊ ትልሞች ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መኾኗንም አመላክተዋል፡፡
የጳጒሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል የጋራ መሪ መልእክት ይከበራሉ፡፡
ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፣
ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን፣
ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን፣
ጳጉሜን 4- የኅብር ቀን እና
ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎች እንደ ቅደም ተከተላቸዉ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበሩ ያስታወቁት ሚኒስትር ድኤታዉ ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል፡፡

ዜጎች በዐዲስ ዓመት ለግል ስኬቶቻቸዉ እንደሚያቅዱት ኹሉ ለኹለንተናዊ ሀገራዊ ብልጽግናም የሚጫወቱትን ሚና ታሳቢ እንዲያደርጉ፣ የመንግሥትን ፖሊሲ እና ስትራቴጂ እንዲሁም ዕቅድ ተገንዝበዉ ተሳትፏቸዉን እንዲያሳድጉ ለማነሣሣት ቀናቱ እንደሚከበሩም ገልጸዋል፡፡ የጳጒሜን ቀናቱን ስያሜ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎች፣ የበጎ አድራጎት እና ማዕድ ማጋራት ተግባራት፣ ነፃ ጤና ምርመራ፣ የደም ልገሳ፣ የፓናል ውይይት እና መሰል መርሐ ግብሮች እንደሚኖሩም አስታውቀዋል፡፡

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የትውልድ ግንባታ መሠረት የሆነው የኢትዮጵያ ትምህርት ዘርፍ የሪፎርም ጉዞ**************************ትምህርት የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ምሰሶ እና የነገዋን ሀገር የሚቀር...
02/09/2026

የትውልድ ግንባታ መሠረት የሆነው የኢትዮጵያ ትምህርት ዘርፍ የሪፎርም ጉዞ
**************************

ትምህርት የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ምሰሶ እና የነገዋን ሀገር የሚቀርጹ የሰው ሀብቶች ማፍሪያ ዋና ግንባር ነው።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር እይታ ላይ የተመሠረተው የመንግሥት የትምህርት ዘርፍ ፖሊሲ፣ በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ላይ መሠረታዊ እና መዋቅራዊ የፖሊሲ፣ የነባር አሠራሮች እንዲሁም የእውቀት ሽግግር ማሻሻያዎችን ሲያካሂድ ቆይቷል።

እነዚህ ሰፋፊ ተግባራት የትምህርት ተዳራሽነትን ከማስፋት ባለፈ፣ ትኩረታቸውን የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ፣ የሥርዓተ-ትምህርት ማሻሻያ ማድረግ እና የተማሪዎችን ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ማደራጀት ላይ አድርገዋል።

በትምህርት ዘርፉ የተከናወኑ ዐበይት ተግባራትና ያመጧቸውን አዎንታዊ ለውጦች ስንመለከት፣ የሀገራችንን ታሪክ፣ ባህላዊ እሴቶች እና ወቅታዊ የዓለም አቀፍ ቴክኖሎጂ እድገትን ያገናዘበ አዲስ የትምህርት ማዕቀፍ ተቀርጾ ወደ ሥራ ገብቷል።

በዘርፉ ሀገር በቀል እውቀቶችን በማካተት የሚሰጡ ትምህርቶች ከሀገራዊ እውነታዎች ጋር እንዲጣጣሙ በመደረጉ፣ የተማሪዎችን ሀገራዊ ፍቅር እና ሥነ-ምግባር የመገንባት ሥራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል።

ከዚህ ጎን ለጎን የቋንቋ እና የፈጠራ ክህሎትን ለማሳደግ በተሠራው ጥረት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ ትምህርቶች በሰፊው እንዲስፋፉ ተደርጓል።

በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ የነበረውን የማጭበርበር እና የስርቆት ባህል በመስበር እውነተኛ የተማሪዎችን እውቀት የመመዘን አሠራር መዘርጋቱ የዚሁ ሪፎርም ዋና አካል ነው።

በተለይም በ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ ፈተናዎች በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንዲሰጡ በማስቻል፣ ትምህርት በራሱ ጥረትና እውቀት ብቻ የሚገኝበት ፍጹም ፍትሐዊ አሠራር እንዲሰፍን ተደርጓል።

ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉና በምግብ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ እንዳይስተጓጎሉ ሰፊ የሥርዓተ-ምግብ ሥራዎች ተከናውነዋል።

በዚህም የትምህርት ቤት ምግባ ፕሮግራም በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልሎች በሰፊው በመተግበሩ የተማሪዎች የመማር ፍላጎትና ውጤታማነት ያደገ ሲሆን፣ ህጻናት ገና በለጋ እድሜያቸው ለመደበኛ ትምህርት ዝግጁ የሚያደርጓቸው መሰረተ-ልማቶችም ተዘርግተዋል።

ሀገራችን ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ጉዞ ለማፋጠን በትምህርት ተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲስፋፋ ተደርጓል።

የኮዲንግ እና የዲጂታል ክህሎት ሥልጠናዎችን በመዘርጋት ወጣቶች በዓለም አቀፍ የዲጂታል ገበያ ተወዳዳሪ የሚሆኑበት ሰፊ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች የዲጂታል ቤተ መጻሕፍት፣ የኦንላይን መማሪያዎች እና የላቦራቶሪ ቁሳቁስ አቅርቦትን የማሻሻል ሥራዎች ተከናውነዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ምርምር ተኮር እንዲሆኑ መዋቅራዊ ለውጦች ተደርገዋል።

የራስ-ገዝነት ሥርዓት በመዘርጋት ዩኒቨርሲቲዎች በበጀት፣ በአካዳሚክ እና በምርምር ነፃነታቸውን አግኝተው በገበያ ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ የትምህርት ዓይነቶችን እንዲቀርጹ አቅጣጫ ተቀምጧል፤ ለአብነትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ተሸጋግሯል።

ምንም እንኳ አሁንም የትምህርት መሰረተ-ልማት ልዩነቶችን ማጥበብ እና የመምህራንን ጥቅም ማስጠበቅ ላይ ቀጣይነት ያለው ሥራ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ የተጀመሩት መዋቅራዊ ሪፎርሞች ኢትዮጵያን ወደተሻለ የእውቀት እና የቴክኖሎጂ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ጠንካራ መሠረቶች ናቸው።

01/09/2026

የጎፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የአፈፃፀም ግምገማ እያካሄደ ነው

‎ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

Address

Felege Niway

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gofa Zone Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gofa Zone Government Communication Affairs Department:

Shortcuts

Share