Finote Selam City Revenue Office

Finote Selam City Revenue Office The aim of fenotselam city revenue office is to collect tax properly

ከሐምሌ 1/2018 እስከ ነሐሴ 21/2018         ➚ መደበኛ =  66,968,115.44        ➚  አገ/ት   =  17,345,451.84 በድምሩ   84,313,567.28 ተሰበሰበ...
27/08/2026

ከሐምሌ 1/2018 እስከ ነሐሴ 21/2018
➚ መደበኛ = 66,968,115.44
➚ አገ/ት = 17,345,451.84 በድምሩ 84,313,567.28 ተሰበሰበ ለምን ካላችሁ ይኸው ስታድየሙ ዙሪያ በከፈልነው ግብር የሚሠሩ መንገዶች፣ የጎርፍ ማፋሰሻዎች ወዘተ ልማቶች ሲሠሩ ማየት እንዴት ደስ ይላል፣ ስለዚህ ግብር ለሀገር ክብር ማለት ይህ ነው። ስለዚህ የደረጃ "ለ" ፣ የአከራይ ተከራይ፣ የወፍጮና የተሽከርካሪ ግብር ከፋዮቻችን ABoR የሚል ቴክስት ከመጣላችሁ እሱ የምትከፍሉት ግብር ስለሆነ ከፍታችሁ በማየት እስከ ነሐሴ 30/2018 ከፍላችሁ አጠናቁ። በተጨማሪም በከተማችን የምትገኙ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢዎች ግብይታችሁን በደረሰኝ እንድታከናውኑ አደራ፣ አደራ አዲስ የወጣው የታክስ አስተዳድር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 ደረሰኝ አሳትሞ እየሠራ ያለ ግብር ከፋይ ደረሰኝ ሳይሰጥ ሽያጭ ሲያከናውን ከተገኘ ደረሰኝ ባልቆረጠበት እያንዳንዱ ግብይት 100ሺህ ብር አንዲቀጣ በሚል ወጥቷል። ስለዚህ ደረሰኝ መስጠት ስልጡንነት ነው የሚለውን እንተግብረው።
የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት

የፍ/ሠላም ከተማ አስተዳድር ገቢዎች ጽ/ቤት በተቋማችን የተለያዮ አገልግሎት ለማግኘት የመጡ ባለጉዳዮችን በማስተናገጃ ቦታ ላይ የግንዛቤ ትምህርት ተሠጠ። ትምህርቱ የተሠጣቸው በሥራና ስልጠና ...
27/08/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስተዳድር ገቢዎች ጽ/ቤት በተቋማችን የተለያዮ አገልግሎት ለማግኘት የመጡ ባለጉዳዮችን በማስተናገጃ ቦታ ላይ የግንዛቤ ትምህርት ተሠጠ። ትምህርቱ የተሠጣቸው በሥራና ስልጠና ጽ/ቤት ተደራጅተው የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ ስልጠና የሰጣቸው ወጣቶች ንግድ ፈቃድ አውጥተው ወደ ግብር ከፋይ ኢትዮጵያዊ ለመሆን ደንበኞች አገ/ት/ሥ/ሒደት አሻራ ለመስጠት ባለጉዳይ ማረፊያ ተቀምጠው ተራ ለሚጠባበቁ ስለ ግብር ትርጉምና ጠቀሜታ ግንዛቤ ተሠጥቷል።
ነሐሴ 20/2018 ዓ/ም

08/08/2026

አስቸኳይ ማስታወቂያ
~~~
ከፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የተላለፈ አስቸኳይ ማስታወቂያ!

በፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ስር ንግድ ፍቃድ የአላችሁም ሆነ የሌላችሁ አነስተኛና መካከለኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ፣ የከባድና ቀላል የጭነት ተሽከርካሪ ፣የባለሦሥት እግር ተሽከርካሪ እና የህዝብና የጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶች በሙሉ:-

የ2018ዓ.ም ግብር የሚከፈለው ከነሐሴ 1 እስከ 10/12 /2018ዓ.ም የሚከፈል ሲሆን የአከፋፈል ሒደቱ በማስታወቂያው ላይ የተገለፀ ስለሆነ በተቀመጠው መርሃ ግብር መሰረት እንድትከፍሉ ያሳስባል።

" ግብር ለሀገር ክብር "

የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት

Finote Selam City Communications

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት ከምዕ/ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በመቀናጀት በደረሰኝ ዙሪያ በከተማው የተ.እ.ታክስ ተመዝጋቢዎች ጋር ከደረሰኝ አቆራርጥ ጋር ተያይዞ ስለ ታክስ ህጉ...
06/08/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት ከምዕ/ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ ጋር በመቀናጀት በደረሰኝ ዙሪያ በከተማው የተ.እ.ታክስ ተመዝጋቢዎች ጋር ከደረሰኝ አቆራርጥ ጋር ተያይዞ ስለ ታክስ ህጉና ስለ አስተዳዳርና በወንጀል ስለሚወሰድ ቅጣቶች በዞኑ ገቢዎች መምሪያ አቃቢ ህግ በአቶ አብርሀም አመካኝነት ግንዛቤና በከተማው በኩል ደግሞ በበጀት ዓመቱ ስለነበሩ ችግሮች ቀርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ውይይቱን የምዕ/ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ካሴ እየተመራ የሚሰበሰበው የተጨማሪ እሴት ታክስ ግብር ከፋዩ ኪሱ የሚከፍለው ሳይሆን ከደንበኞች የሚሰበሰብ መንግስት ሰብስባችሁ ገቢውን አንድታመጡለት በአደራ የተሰጣችሁ ነው፣ ነገር ግን ይህ እየሆነ አይደለም እኛም ወደ እርምጃ ከመግባታችን በፊት ለመጨረሻ ጊዜ እንወያይ ብለን ነው በማለት ገልፀው ግብር ከፋዮች ሀሳብ፣አስተያየትና ጥያቄ ካላቸው ዕድል ሰጥተው፣ መድረኩ መዘጋጀቱ ጥሩና አስፈላጊ ነው ከአሉ በኋላ፣
▸ ከአ/አበባ ዕቃ ስንገዛ ደረሰኝ አይሰጡንም፣
▸ የሽያጭ መ/መሳሪያ ጉዳይ ችግሩ ይፈታልን፣
ወዘተ... የመሳሰሉት ሀሳቦች ተነስተዋል። ለተነሱትም ምላሽ በባለሙያዎች ተሰጥቶ መምሪያ ኃላፊው ማጠቃለያ በመስጠት ተጠናቋል። በመድረኩ የዞንና የከተማ ማኔጅመንት አካላትና የክትትል ባለሙያዎች ተገኝተዋል። የዕለቱ ውይይትም መድረኩ በየ ሦስት ወሩ እንዲቀጥል በመግባባት ተጠናቋል።

የፍ/ሠላም ከተማ አስተዳድር ገቢዎች ጽ/ቤት በአለፈው ሳምንት የበጎ አድራጎት ሥራ በመሥራት ረዳት ለሌላቸው ተማሪዎች የሚሆን ከተቋሙ ባለሙያዎች በተሠበሠበ ገንዘብ ደብተርና ስክርቢቶ በመግዛት...
02/08/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስተዳድር ገቢዎች ጽ/ቤት በአለፈው ሳምንት የበጎ አድራጎት ሥራ በመሥራት ረዳት ለሌላቸው ተማሪዎች የሚሆን ከተቋሙ ባለሙያዎች በተሠበሠበ ገንዘብ ደብተርና ስክርቢቶ በመግዛት የአስረከበና በቀጣይም በኑሮ ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑ የአንድ ሰው ቤት ለመጠገን በዝግጅት ላይ እንደሆነ ጠቅሰን እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ተቋሙ የጀመረውን ዳር ሳያደርስ መተው ሽንፈት ነው በሚል ወኔ በ04 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑትን የወ/ሮ የአልጋነሽ ዘለቀን ቤት ሙሉ ጣራውን በእንደዚህ ሁኔታ ጠግነን የቀበሌው የአገር ሽማግሌዎች በተገኙበት በማመስገን አስረክቧል። የገቢ ተቋሙ ባለሙያዎች ምንጊዜም ለበጎ አድራጎት ሥራ ግንባር ቀደም ሆነው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ ለዚህ ተግባር ከብር 36,000 በላይ ወጪ ሆኗል። የተጠገነው ቤት ይህን ይመስላል።

የበጎ አድራጎት ሥራ በመሥራት የሚታወቁት የፍ/ላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች1. ረዳት የሌላቸውን ተማሪዎችን ለቀጣዩ የት/ት ዘመን መማሪያ ደብተርና ስክርቢቶ መግዣ የተ...
28/07/2026

የበጎ አድራጎት ሥራ በመሥራት የሚታወቁት የፍ/ላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች
1. ረዳት የሌላቸውን ተማሪዎችን ለቀጣዩ የት/ት ዘመን መማሪያ ደብተርና ስክርቢቶ መግዣ የተቋሙ አመራሮችና ባለሙያዎች ከኪሳቸው ገንዘብ በማዋጣት፣
- 9 ደርዘን ደረጃውን የጠበቀ ባለ 50 ገፅ ሲነር ላይን ደብተር፣
- 2 ፓኮ ኦርጂናል ቢክ ስክርቢቶ በመግዛት ለፍ/ሠላም ከተ/አስ/ሴ/ህ/ጽ/ቤት አስረክበናል።
2. በኑሮ ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑ ቤታቸው ፍሳሽ የሚስቸግራቸውን አንድ ቤት ጠግነን ለማስረከብ ማቴሪያሎችን የማሰባሰብ ሥራ እየሠራን ሲሆን እስካሁን 13 ዚንጎ ቆርቆሮ እና 1 ፓኮ ወይም 5 ኪ.ግ ሚስማር ከ3 በጎ አድራጊዎች ድጋፍ ተደርጎልናል። ድጋፍ ማሰባሰቡን እንደጨረስን የሚጠገነውን ቤት ጠግነን ለባለቤቶች የምናስረክብ ይሆናል። ቀጣይ የደረስንበትን ውጤት በቀጣይ እናሳውቃለን።

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 ዓ/ም የገቢ አሰባሠብ አፈፃፀምን ገመገመ።የገቢ ተቋሙ የ2018 ዓ/ም የገቢ አሰባሰቡን ማጠቃለያ ሪፖርት ከጠቅላላ ባለሙያዎች ጋር ገምግሟል። ግ...
21/07/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 ዓ/ም የገቢ አሰባሠብ አፈፃፀምን ገመገመ።
የገቢ ተቋሙ የ2018 ዓ/ም የገቢ አሰባሰቡን ማጠቃለያ ሪፖርት ከጠቅላላ ባለሙያዎች ጋር ገምግሟል። ግምገማው ማጠቃለያ ሪፖርቱን የተቋሙ የዕቅድ ባለሙያ አቶ ጎጃም ታገለ በየሥራ ሒደቱ የተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር በማቅረብና የነበሩ ጠንካራና ድክመቶችን በመግለፅ ጭምር አቅርበዋል።
በመቀጠልም የተቋሙ ዋና ኃላፊ አቶ አዝመራው ሙሉሰው የ2018 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰበችን ከአለፉት ዓመታት ጥንካሬ የታየበት፣ ማኔጅመንቱ፣ባለሙያው ጠንካራ እንቅስቃሴ የአደረገበትና ውጤት የአመጣንበት ለከተማችን የሻለ ገቢ የሰበሰብንበት ስለሆነ ልንኮራ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። አያይዘውም በቀጣዩ የበጀት ዘመን ዕቅዳችን ከፍ ብሎ የሚታቀድ ስለሆነ ከወዲሁ ተዘጋጅተንና ጥሩ ገቢ በመሰብሰብ ከተማችንን ሪጅኦ ከተማ ለማድረግ ገቢ አንዱ መስፈርት ስለሆነ የእኛን ድረሻ መወጣት አለብን ብለዋል። በመጨረሻም በአፈፃፀም ጥሩ ውጤት በማስመዝገብ ወደፊት የወጡ ለ3 የሥራ ሒደት አስተባባሪዎች የዕውቅና የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተሰጥቷል።

20/07/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት በ 2018 በጀት ዓመት እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ/ም ድረስ ብር 428,877,260.71 ገቢ ሠበሰበ።
ተቋሙ በበጀት ዓመቱ፣
✈ መደበኛ ገቢ፣
▸ ዕቅድ= 357,148,096
▸ ክንውን= 339,247,132
▸ አፈፃፀም= 95%
✈ ከተማ አገ/ት ገቢ፣
▸ ዕቅድ= 174,587,105
▸ ክንውን= 89,630,128.62
▸ አፈፃፀም= 51.34%
✈ ጠ/ድምር፣
▸ ዕቅድ= 531,735,201
▸ ክንውን= 428,877,260.71
▸ አፈፃፀም= 80%
ይህ አፈፃፀም ከ 2017 ዓ/ም ገቢ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር፣
▸ መደበኛ ገቢ:- በብር 141,178,683.55
አፈፃፀም የ 71.3%
▸ ከተ/አገ/ት ገቢ:- በብር 28,610,337.47
አፈፃፀም 46.9% ሲሆን በድምሩ የብር
169,789,021 በመቶኛ ደግሞ የ65.5% በብልጫ መሠብሰብ ተችሏል።
በተጨማሪም ተቋሙ ከተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/፣
▸ ዕቅድ= 51,500.000
▸ ክንውን = 50,729,394
▸ አፈፃፀም= 98.5% ሲሆን ይህ ገቢ ከአለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በብር 28,825,685 በመቶኛ ደግሞ የ131.6% ብልጫ አለው።

የፍ/ሠላም ከተማ አስተዳድር ገቢዎች ጽ/ቤት በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 301/2017 መሠረት የተጠናውን የቀን ገቢ  ጥናት በ5ቱ የአጥኝ ቡድንና በሌሎች የተቋሙ ባለሙያዎች ወደ ሲስተም...
15/07/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስተዳድር ገቢዎች ጽ/ቤት በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 301/2017 መሠረት የተጠናውን የቀን ገቢ ጥናት በ5ቱ የአጥኝ ቡድንና በሌሎች የተቋሙ ባለሙያዎች ወደ ሲስተም በመመዝገብ እየሠሩ ነው። ግብር ከፋዮች ይህ ምዝገባ እንደተጠናቀቀ የግብር ውሳኔ ከምትከፍሉበት ቁጥር ጋር በእጅ ስልካችሁ በአጭር የጽሁፍ መልዕክት የሚደርሳችሁ ስለሆነ
1ኛ/ ስልካችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትጠባበቁ፣
2ኛ/ ስልክ በትክክል የአልሰጣችሁ ከሆነ በአካል በመምጣት ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን የገቢ ተቋሙ የአሳስባል። ከዚህ በተረፈ የምዝገባው ሂደት አየተፋጠነ መሆኑን ይህን ይመስላል።

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት ለቀን ገቢ መረጃ ሰብሳቢ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፣የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገቢዎች ቢሮ አዲስ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ የደረጃ "ሐ"  ግብር...
01/07/2026

የፍ/ሠላም ከተማ አስ/ገቢዎች ጽ/ቤት ለቀን ገቢ መረጃ ሰብሳቢ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ፣
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገቢዎች ቢሮ አዲስ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይን በደረጃ "ለ" ሥር በማጠቃለል ተርን ኦቨር ታክስ የተሠረዘ መሆኑን በአዋጁ መቀመጡን ተከትሎ በከተማችን የሚገኙ ከደረጃ "ሀ" ውጭ የሆኑ ግብር ከፋዮች የቀን ገቢያቸው በአዲስ በገቢ ተቋሙ ባለሙያዎች ተጠንቶና የተጠናውን መረጃ በኢ- ታስ ሲስተም በማስገባት ግብር ወስኖ በኤስ.ኤም.አስ በመላክ ግብር አንዲከፍሉ ለማድረግ ለተቋሙ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናውን በይፋ የከፈቱት የተቋሙ ም/ኃላፊ አቶ ታየ ሠሎሞን ሲሆኑ ስልጠናውን በደንብ ተከታትላችሁ ተግባራዊ እንድታደርጉ ሲሉ ገልፀዋል። አክለውም ስልጠናውን የተቋማችን የመረጃ ቴክኖሎጅ አስተዳድር ልማት የሥራ ሒደት አስተባባሪ አቶ ጥላሁን ደምል የሚሠጧችሁ ይሆናል በማለት ገልፀዋል። አቶ ጥላሁንም የአዘጋጁትን ሰነድ ለሠልጣኞ አንድ በአንድ በመግለፅ ስልጠናውን ለተቋሙ የቀን ገቢ መረጃ ሰብሳቢዎቸ፣ የኢንስፔክሽን ቡድኑና ሌሎች የተቋሙ ባለሙያዎች ስልጠናውን የተሳተፉ ሲሆን ግልፅ የአልሆነላቸውን ጥያቄዎች በማንሳት ምላሽ ከተሰጠባቸው በኋላ፣ ይህ ስልጠና በተደጋጋሚ በተግባር እየሠራን በደንብ አውቀን መሥራት አለብን በማለት አስተያየት በመስጠት ተጠናቋል።
* መረጃው:- የግብ/ትም/ኮሙ/ የሥራ ሒደት ነው፤

Address

Finote Selam

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Finote Selam City Revenue Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Finote Selam City Revenue Office:

Shortcuts

Share