18/08/2026
አመራሩ ውጫዊና ውስጣዊ አደጋዎችን በመገንዘብ ለሠላምና ልማት በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በምዕራብ ጎጃም ዞን የቡሬ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት “ውጫዊ የወረራ ስጋትንና ውስጣዊ የጽንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሠላምና ልማት እናረጋግጣለን።” በሚል መሪ ሃሳብ ከከተማ አስተዳደሩ ጠቅላላ አመራሮች ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ የቡሬ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አንማው ብዙዓየሁ የውይይቱን መነሻ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በአቀራረባቸውም የጽንፈኝነትና የጥፋት ኃይሎችን እኩይ ዓላማ በማክሸፍ፣ የሠላም ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አመራሩ በአካባቢው ሊከሰቱ የሚችሉ ውጫዊና ውስጣዊ አደጋዎችን በቅድሚያ በመለየትና በመገንዘብ የሠላም ጥበቃን ከልማት ሥራዎች ጋር በማስተሳሰር በንቃትና በቁርጠኝነት መሳተፍ እንዳለበትም ገልፀዋል።
በውይይቱ የተሳተፉ አመራሮች በበኩላቸው፣ ማህበረሰቡ የጽንፈኝነትን አስተሳሰብና ድርጊት በመቃወም ሠላምን ለማስፋት እያደረገ ያለው ተሳትፎ እየጎለበተ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በተጨማሪም ሕግን የማስከበር ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።
ተሳታፊዎቹ አክለውም፣ ሁለንተናዊ የህብረተሰብ ተሳትፎንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሠላምን ማስጠበቅ መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታ መሆኑን በመግለፅ ሠላም ሲረጋገጥ የልማት ሥራዎች በተቀላጠፈ ሁኔታ መከናወንና ማህበረሰቡም ከልማቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
አመራሩ የሠላም ጥበቃን በተቀናጀ መልኩ በማጠናከር፣ የጽንፈኝነትንና የጥፋት አስተሳሰቦችን በመቃወም እንዲሁም ማህበረሰቡን በማሳተፍ ለዘላቂ ሠላምና ልማት በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት አፅንዖት ተሰጥቷል።
West Gojjam Zone Prosperity