Gambella Mass Media Service

Gambella Mass Media Service To make new and up-to-date information available to the public.

የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በተግባራዊ ክህሎት ለማጠናከር ከዘጠኝ ወረዳዎች ለተውጣጡ የተፈጥሮ ሀብት ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ።ስልጠናው በቆላማ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (...
06/09/2026

የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂና በተግባራዊ ክህሎት ለማጠናከር ከዘጠኝ ወረዳዎች ለተውጣጡ የተፈጥሮ ሀብት ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ።

ስልጠናው በቆላማ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአፈር መሸርሸርን ለመቀነስ፣ የውሃ ሀብትን ለመጠበቅና የመሬት ምርታማነትን ለማሻሻል የሚያግዙ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ቴክኖሎጂዎች ላይ ያተኮረ ነው።

የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር አቶ ኬት ቾል እንደገለጹት፣ በስልጠናው የሚያገኙትን እውቀትና ክህሎት ወደ ወረዳዎቻቸው በማስፋፋት በእርከን ሥራና በሌሎች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎች ላይ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

አቶ ኬት አክለውም፣ ስልጠናው ፕሮጀክቱ በ2019 ዓ.ም. ካቀዳቸው የሥራ እቅዶች አንዱ መሆኑን ጠቁመው፣ የግብርና ባለሙያዎችን በክህሎት ማብቃት በቀጥታ ወደ አርሶ አደሩ በመድረስ የአመራረት ሥርዓቱንና የኑሮ ሁኔታውን ለማሻሻል የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

በተጨማሪም ስልጠናው ባለሙያዎች የተማሩትን እውቀት በተግባር በመተርጎም በወረዳና በቀበሌ ደረጃ ለሚከናወኑ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎች የተሻለ የቴክኒክ ድጋፍ እንዲሰጡ ያስችላል።

የቆላማ አከባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት በተለይም በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ሁኔታን፣ የግብርና ምርታማነትንና የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የሚከናወኑ ሥራዎችን በመደገፍ ላይ ይገኛል።

የጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን" በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት ተከበረ።የጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን" — "የማክሮ ኢኮኖሚ እና የአምራችነት ስኬቶች" በሚል መሪ ቃል በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት...
06/09/2026

የጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን" በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት ተከበረ።

የጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን" — "የማክሮ ኢኮኖሚ እና የአምራችነት ስኬቶች" በሚል መሪ ቃል በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል።

​በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ እንደገለጹት፤ ዕለቱን "የእመርታ ቀን" ብሎ መሰየምና ማከበር ያስፈለገው በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመዘገበ ያለው የኢኮኖሚ እድገት ጤናማ አካሄዱን ጠብቆ እንዲቀጥል ለማስገንዘብ ነው ብለዋል።

​በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በኢንዱስትሪ እና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን አብራርተዋል።

የጳጉሜ 1 የእመርታ ቀን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እና "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄን ለማጠናከር የሚደረጉ ጥረቶችን የሚያሳይ እንዲሁም ሀገራችንን ወደ ሙሉ አምራችነት እየለወጥናት መሆኑን የሚያመላክት እንደሆነም ገልጸዋል።

​ያለፉት የለውጥ ዓመታት በበርካታ ውጣ ውረዶችና ፈተናዎች የታጀቡ ቢሆኑም፣ እነዚህን ተደራራቢ ፈተናዎች ወደ ስኬት በመቀየር ዘርፈ ብዙና አኩሪ እምርታዊ ድሎችን ማስመዝገብ መቻሉን አስታውሰዋል።

የተመዘገበው እምርታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በመጪው አዲስ ዓመት መላው የክልሉና የሀገራችን ህዝብ እንደተለመደው ከመንግስት ጎን በመቆም ለዘላቂ ሰላም፣ ለቀጣይ ልማትና ለመልካም አስተዳደር መስፈን የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል።

​የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ጋትሉዋክ ሮን በበኩላቸው እንደሀገር የኢኮኖሚ እመርታን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው፣ በክልሉ በአምራች ዘርፉ ስኬቶችን በአዲሱ አመት ለማምጣት መዘጋጀት አለብን ብለዋል።

የተጀመሩ የልማትና የመሰረተ ልማት ስራዎች ግባቸውን እንዲመቱ ህዝቡ ከአመራሩ ጋር ያለው ቅንጅትና አንድነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

​የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኡማን አሙሉ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት ዓመታት ያጋጠሙትን ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ማነቆዎች ለመፍታት መጠነ-ሰፊ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በጠንካራ የኢኮኖሚ ፖሊሲና አቅጣጫ አማካኝነት ፈታኝና ውስን የነበረውን የፋይናንስ አቅም በመሻገር፣ ከፍተኛ የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጥ ያስመዘገብንበት የስኬት ዓመት እንደነበር አብራርተዋል።

በእለቱ በዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች ጥሩ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት እና ሞዴል አርሶአደሮች የምስክር ወረቀት እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።

ጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን"  በፓናል ውይይት  በጋምቤላ ከተማ እየተከበረ ነው።በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር፣ የብልጽ...
06/09/2026

ጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን" በፓናል ውይይት በጋምቤላ ከተማ እየተከበረ ነው።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር፣ የብልጽግና ፓርቲ ጋምቤላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን ፣ ሌሎች የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ጳጉሜን 1 (እመርታ ቀን)፦ ሀገራችን ከተረጂነትና ጥገኝነት ተላቃ ወደ አምራችነት እያደረገች ያለችውን ታሪካዊ ሽግግር ለማብሰር፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬቶች እና የምግብ ሉዓላዊነት ድሎች የተመዘገቡበት ቀን ነው።

የጋምቤላ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የሚያደርገውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በማጠናከር በጋምቤላ ከተማ 04 ቀበሌ ለምትገኝ አንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት የመሥራ...
05/09/2026

የጋምቤላ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የሚያደርገውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በማጠናከር በጋምቤላ ከተማ 04 ቀበሌ ለምትገኝ አንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት የመሥራት ሥራ ጀመረ።

ቢሮው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የተቸገሩ ወገኖችን ለመደገፍ ያቀደው መርሃ ግብር፣ በከተማው በሚገኙ አምስቱም ቀበሌዎች በየስድስት ወሩ አንድ አንድ ቤት በመሥራት ተጠቃሚዎችን ለመደገፍ ያለመ ነው።

የቤት ግንባታ ፕሮግራሙ የቢሮው ሰራተኞች በበጎ ፈቃድ በሚያደርጉት አስተዋጽኦ የሚከናወን ሲሆን፣ በዚህም በተጨማሪ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ተጨባጭ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ የመረዳዳትና የመተባበር ባህልን ለማጠናከር ያግዛል።

በዛሬው ዕለት በ04 ቀበሌ የተጀመረው የቤት ግንባታ ሥራም የዚሁ መርሃ ግብር አካል ሲሆን፣ ቢሮው በቀጣይም በአምስቱም ቀበሌዎች በተያዘው ዕቅድ መሠረት ተግባሩን እንደሚያስፋፋ ተገልጿል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የጋምቤላ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አሪያት ኡጁሉ፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ችግረኛና አቅመ ደካማ ወገኖችን በመደገፍ የማህበረሰቡን የመረዳዳት መንፈስ የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።

ወይዘሮ አሪያት እንዳሉት፣ የቢሮው ሰራተኞች በጋራ በመሆን በየስድስት ወሩ አንድ ቤት ለመሥራት ያቀደው ዕቅድ ተግባራዊ በማድረግ በእውነተኛ የበጎ ፈቃድ ሥራ ለተቸገሩ ወገኖች የሚደርሰውን ድጋፍ ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

የቢሮው የሴቶች ግንዛቤ ንቅናቄ ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ግሩም ገ/የሱስ በመርሃ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የበጎ ፈቃድ ሥራ እንደ ተቋም ብቻ ሳይሆን እንደ ማህበረሰብ ሊጎለብት የሚገባ እሴት መሆኑን ጠቁመው፣ ሰራተኞችና ሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎች በዚህ መልካም ተግባር እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ቢሮው ከቤት ግንባታ በተጨማሪ በአዲሱ ዓመት እስከ 500 ለሚደርሱ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ እንዲሁም ለሴቶች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ አቅዷል።

እንዲሁም ለአዲሱ ዓመት የመዓድ ማጋራት መርሃ ግብር በማካሄድ ከተቸገሩ ወገኖች ጋር በመካፈል የበዓል ደስታን በጋራ ለማጣጣም የተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራትን ለመፈጸም መዘጋጀቱ ተገልጿል።

በዚህም ቢሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱን በማጠናከር አቅመ ደካማ ወገኖችን መደገፍ፣ የተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ማጎልበት እና ሴቶች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በተገቢው ሁኔታ እንዲያገኙ ማገዝ የሚያስችሉ ተግባራትን በተቀናጀ መልኩ እያከናወነ መሆኑ ተመልክቷል።

ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ምዕራብ ምዕሪብ ሪጅን የአዲሱን ዓመት መግቢያ አስመልክቶ “በበጎነት” በሚል መርህ በጋምቤላ ከተማ ለሚገኘው የመቄዶንያ ማዕከል 525 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።የኢ...
05/09/2026

ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ምዕራብ ምዕሪብ ሪጅን የአዲሱን ዓመት መግቢያ አስመልክቶ “በበጎነት” በሚል መርህ በጋምቤላ ከተማ ለሚገኘው የመቄዶንያ ማዕከል 525 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

የኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ምዕራብ ምዕራብ ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አዲሱ ሽፈራው፣ ተቋሙ ከመደበኛ የቴሌኮም አገልግሎት ባሻገር የማኅበረሰቡን ሕይወት ለማሻሻልና የሀገር አለኝታነቱን ለማጠናከር በተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።

ተቋሙ በ“እድማስ፡ ዲጂታል እና ከዚያም ባሻገር 2028” የሦስት ዓመት ስትራቴጂ በመመራት፣ ዘመናዊ የዲጂታል መፍትሔዎችን ከማቅረብ ጎን ለጎን ትምህርት፣ ጤና፣ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማትን ጨምሮ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንም አቶ አዲሱ ገልጸዋል።

እንደ አቶ አዲሱ ገለጻ፣ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ በእነዚህ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ከ492 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል። ባለፉት አምስት ተከታታይ ዓመታትም በ“በበጎነት” መርሀ ግብር ለ117 የበጎ አድራጎት ማዕከላት ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።

በዘንድሮው ዓመትም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 50 የበጎ አድራጎት ማዕከላት ለሚገኙ 22 ሺህ 212 አረጋውያን፣ ሕፃናት፣ እናቶችና አካል ጉዳተኞች ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉም ተጠቁሟል።

በጋምቤላ ክልል የመቄዶንያ ማዕከል የሚገኙ ወገኖችን በመደገፍ የተደረገው የ525 ሺህ ብር ድጋፍም የዚሁ የ“በበጎነት” መርሀ ግብር አካል መሆኑ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮ ቴሌኮም ከብሔራዊ የደም ባንክ ጋር በመተባበር ዋና መሥሪያ ቤቱን ጨምሮ በተለያዩ ዞኖችና በጋምቤላ ሪጅን በአጠቃላይ በ22 ቦታዎች የደም ልገሳ መርሀ ግብር ማካሄዱን አቶ አዲሱ ገልጸዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም በቀጣይም ዘመናዊ የዲጂታል ሶሉሽኖችን ከማቅረብ ጎን ለጎን ሰው ተኮር በሆኑ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ያለውን ዘላቂ አጋርነት በማጠናከር ሀገራዊ አለኝታነቱን እንደሚያጠናክር አቶ አዲሱ ገልጸዋል።

የአዲሱን ዓመት መምጣት ተከትሎም ለቀጣዮቹ አምስት ተከታታይ ቀናት በጋምቤላ ከተማ የተለያዩ የበጎ አድራጎትና የድጋፍ ሥራዎችን እንደሚያከናውን ኢትዮ ቴሌኮም ገልጿል።

ተቋሙ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የበረከት ዓመት እንዲሆን ምኞቱን አስተላልፏል።

የሰላም፣ የእርቅ፣ የአንድነትና የጽናት መልዕክትን ይዘው የሚንቀሳቀሱት ፓስተር ፖች ኦክዌር እና የሰላም ጉዞ እንግዳ የሆኑት አምባሳደር ፓስተር ኢዮብ ከተለያዩ ሃይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማ...
05/09/2026

የሰላም፣ የእርቅ፣ የአንድነትና የጽናት መልዕክትን ይዘው የሚንቀሳቀሱት ፓስተር ፖች ኦክዌር እና የሰላም ጉዞ እንግዳ የሆኑት አምባሳደር ፓስተር ኢዮብ ከተለያዩ ሃይማኖት አባቶች፣ ከሀገር ሽማግሌዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋምቤላ ከተማ ውይይት አድርገዋል።

የሰላም አምባሳደር ፓስተር ኢዮብ ባስተላለፉት መልዕክት ይቅርታ ያለፉትን ቁስሎች እና በግጭት የተፈጠሩ በደሎችን በይቅርታ በመሻገር ወደፊት ለመራመድ በር የሚከፍት እና በህዝቦች መካከል ያለውን አለመግባባት በማስወገድ እርስ በርስ የመደጋገፍ ባህልን ያጠናክራል።

የሰላም ጉዞው በክልሉ ህዝቦች መካከል ወንድማማችነትን ለማስረፅ እና ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽዖ እንደሚኖረውም ጠቁሟል።

ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ ወደ ትውልድ ቀዬው የተመለሰው ፓስተር ፖች ኡኩዌር፣ አባቱን ፕሪስት ኦክዌርን ጨምሮ በቤተሰቡና በሌሎች ሰዎች ላይ የደረሰውን አሳዛኝ ጉዳት በልቡ ይዞ ቆይቷል።

ይሁን እንጂ ይህንን የግልና የቤተሰብ ሐዘን ወደ በቀል ሳይቀይር፣ ይቅርታን፣ እርቅን፣ አንድነትንና ሰላምን መምረጡን በተግባር እያሳየ ይገኛል።

ባለፈው ሳምንት የአባቱንና ሌሎች የጉዳቱ ሰለባ የሆኑ የቤተሰብ አባላትን መቃብር በመጎብኘት ጸሎት ያደረገው ፓስተር ፖች፣ የሰላምና የይቅርታ መልዕክትም አስተላልፏል።

ይህ የሰላም ጉዞ በCommunity Peace, Reconciliation, Unity and Development Association (CPRDA) በኩል የሰላም፣ የእርቅ፣ የአንድነትና የጽናት መልዕክትን ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።

አምባሳደር ፓስተር ኢዮብ በጋምቤላ የሚያደርጉት የሰላም ጉዞ፣ በማህበረሰቡ መካከል የመተሳሰብ፣ የይቅርታና የእርቅ እሴቶችን ለማጠናከር አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል።

የፓስተር ፖች ኦክዌር የሰላም ጉዞ ከበቀል ይልቅ ይቅርታን፣ ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን፣ ከጥላቻ ይልቅ ሰላምን መምረጥ የሚቻል መሆኑን የሚያሳይ የተግባር ምስክር ሆኗል።

የጋምቤላ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ኡቶር ኡኩጉ በወቅቱ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚነሱ አለመግባባቶችን በውይይትና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ግንዛቤ የማስጨበጥ እና አወንታዊ ሰላምን የማስፈን ሥራዎችን ለማምጣት ያግዛል ተብለዋል።

ምክትል ከንቲባው አክለውም የአይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች የራሳቸውን ዕውቅና በመጠቀም በሰላም ዙሪያ በየእምነታቸው ስለ ሰላም ጥቅም በመናገር የራሳቸውን ሃላፊነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

ኦፔኖ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም 15ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን በማካሄድ በተለያዩ የትምህርትና ሙያ መስኮች የሰለጠኑ 159 ተማሪዎችን አስመርቋል።ከተመራቂዎቹ መካከል 155 ተማሪዎ...
05/09/2026

ኦፔኖ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም 15ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን በማካሄድ በተለያዩ የትምህርትና ሙያ መስኮች የሰለጠኑ 159 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል 155 ተማሪዎች በደረጃ አራት፣ አራቱ ተማሪዎች ደግሞ በደረጃ ሦስት ትምህርታቸውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀው ምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጋምቤላ ክልል ሥራና ክህሎት ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰናይ አኩዎር፣ የተመራቂ ተማሪዎች የዛሬ ስኬት ምስክር ወረቀት ማግኘት ብቻ ሳይሆን የጥረታቸውና የተስፋቸው ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሰናይ አክለውም፣ በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ውስጥ ዕውቀትን ብቻ ማግኘት ሳይሆን እጅ ላይ ሥራ የሚፈጥር ክህሎት አዳብሮ መውጣት ዋና ዓላማ መሆኑን ጠቁመዋል።

ተመራቂ ተማሪዎቹ ባገኙት ሙያና ክህሎት መሠረት ራሳቸውን፣ ቤተሰቦቻቸውንና ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ አቶ ሰናይ አሳስበዋል። ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ለሀገር ልማትና እድገት ያለው አስተዋጽኦም ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ተመራቂዎቹ ከዛሬ ጀምሮ በተማሩት ሙያና ባገኙት ክህሎት በመታገዝ፣ በጥሩ ሥነ-ምግባርና ችሎታቸውን በአግባቡ በመጠቀም የማኅበረሰቡን ችግር ፈቺ በሆኑ ሥራዎች እንዲሰማሩና የሕዝብ አገልጋይ እንዲሆኑም አስገንዝበዋል።

የኦፔኖ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ኤሊያስ ያዕቆብ በበኩላቸው፣ 15ኛው ዙር የተማሪዎች ምረቃ ልዩ የሚያደርገው ኢትዮጵያ በራሷ የሰው ኃይል፣ በዕውቀትና በክህሎት የሀገር ግንባታ በምታካሂድበት ወቅት መሆኑን ገልጸዋል።

የቴክኒክና ሙያ ተመራቂዎች በግንባታ፣ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና፣ በመረጃ ቴክኖሎጂና በሌሎች የሥራ መስኮች ያገኙትን ክህሎት በአግባቡ በመጠቀም ሀገራቸውን ወደምትፈልገው የብልጽግና ጉዞ ማሻገር እንደሚችሉም አቶ ኤሊያስ ተናግረዋል።

ተመራቂዎቹ ሥራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆኑ ሥራ ፈጣሪዎች በመሆን፣ በሙያቸው ያሉ ችግሮችን በመለየት ተግባራዊ መፍትሔ እንዲፈልጉ፣ አዳዲስ ሀሳቦችን እንዲያፈልቁና ሀሳቦቻቸውን ወደ ምርትና አገልግሎት እንዲቀይሩ ዋና ዲኑ አሳስበዋል።

ኮሌጁ ባለፉት አራት ዓመታት ሥልጠናውን የተከታተሉ 159 ሰልጣኞችን ማስመረቁን የተገለጸ ሲሆን፣ ከእነዚህም 40 ወንዶች እና 119 ሴቶች መሆናቸው ተጠቅሷል።
በተጨማሪም ባለፉት አራት ዓመታት ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቷል።

የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ሁለተኛ ዙር (LLRP-II) የ2018 ዓ.ም የዓመት የሥራ ዕቅድና በጀት አፈጻጸም ግምገማ እንዲሁም የ2019 ዓ.ም የዓመት የሥራ ዕቅድና በጀት ለሁ...
05/09/2026

የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ሁለተኛ ዙር (LLRP-II) የ2018 ዓ.ም የዓመት የሥራ ዕቅድና በጀት አፈጻጸም ግምገማ እንዲሁም የ2019 ዓ.ም የዓመት የሥራ ዕቅድና በጀት ለሁሉም የፕሮጀክቱ ባለድርሻ አካላትና ሠራተኞች የማስተዋወቅ መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሄደ።

የክልሉ የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶክተር ቤል ቢቾክ ቸፕሮጀክቱ በ2018 ዓ.ም ያከናወናቸውን ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶችንና በአፈጻጸም ወቅት የታዩ ተግዳሮቶችን በመገምገም የቀጣይ ዓመት ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ መፈጸም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ዶክተር ቤል ቢቾክ እንደገለጹት፣ የLLRP-II ፕሮጀክት ዋና ትኩረት በቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ ማህበረሰቦችን የኑሮ መረጋጋትና የመቋቋም አቅም ማጠናከር ሲሆን፣ ይህንን ለማሳካት የፕሮጀክቱ ባለድርሻ አካላት በዕቅድ፣ በአፈጻጸምና በክትትል ሂደት በቅንጅት መሥራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

በተለይም የፕሮጀክቱ የ2019 ዓ.ም ዕቅድ በተገቢው ሁኔታ እንዲፈጸም፣ የተመደበው በጀት ለታቀዱ ተግባራት ብቻ በብቃትና በጥንቃቄ መጠቀም፣ የሥራ አፈጻጸም በየደረጃው በመከታተል የታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ ማስተካከል እንደሚገባ አስተባባሪው አሳስበዋል።

በመድረኩ የ2018 ዓ.ም የዓመት የሥራ ዕቅድና በጀት አፈጻጸም በመገምገም፣ በ2019 ዓ.ም ለፕሮጀክቱ የተያዘው ዕቅድና በጀት ለተሳታፊዎች ቀርቧል። በተጨማሪም በፕሮጀክቱ የተካተቱ የግጭት ተያያዥ የሀብት አያያዝ፣ የአየር ንብረት መቋቋምና ዘላቂ የኑሮ ማጠናከሪያ ሥራዎች ላይም ትኩረት ተደርጓል።

በሌላ በኩል፣ የፕሮጀክቱ የጥራት አስተዳደር፣ የሥራ ክትትልና ግምገማ፣ የግዥና የፋይናንስ አስተዳደር እንዲሁም የቅሬታ አፈታት ሥርዓት በተገቢው እንዲተገበር ተሳታፊዎቹ በጋራ መወያየታቸው ተገልጿል።

የ2019 ዓ.ም ዕቅድ በውጤታማነት መፈጸም በመስክ የሚገኙ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች፣ የዞንና ወረዳ አካላት እና ሌሎች ባለድርሻዎች በጋራ በመስራት ለማህበረሰቡ የሚደርሱ የልማት ጥቅሞችን ማሳደግ እንደሚጠይቅ በውይይቱ ተገልጿል።

LLRP-II በክልሉ የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ መረጋጋትንና የማህበረሰብ መቋቋም አቅምን ለማጠናከር የሚሰራ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በዓለም ባንክና በIFAD ድጋፍ ከፌዴራልና ከክልል ተቋማት ጋር በመተባበር የሚተገበር መሆኑ ከመድረኩ መረጃ ይታያል።

የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ከኢሉአባቦር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመሆን በአኙዋኣ ብሔረሰብ ዞን ወሰን ተሻጋሪ የዜግነት አገልግሎት አበረከቱ።​በኢ...
04/09/2026

የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ከኢሉአባቦር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመሆን በአኙዋኣ ብሔረሰብ ዞን ወሰን ተሻጋሪ የዜግነት አገልግሎት አበረከቱ።​

በኢሉአባቦር ወጣቶች ክንፍ የተደረገው የዜግነት አገልግሎት፥የዞኑ ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን ከማስታገስ ባለፈም በዜጎች መካከል የትብብር፣ የአብሮነት እና የጋራ ኃላፊነት መንፈስን ይበልጥ የሚያጠናክር ነው ተብሏል።

የአኙዋኣ ብሔረሰብ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የውኃና ማዕድን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ አቡዎላ ኡኳዮ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት፥ የኢሉአባቦር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የክልል እና የዞን ወሰኖችን በማሻገር ያበረከተው የዜግነት አገልግሎት በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ውስጥ አብሮነትን እና አጋርነትን ማጠናከር የሚቻልበትን የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው ብለዋል።

የኢሉአባቦር ዞን ወጣቶች ክንፍ ያበረከተው ድጋፍ የእርስ በእርስ ትስስርና የጋራ አላማ ከማጠናከር ባለፈም ​ፓርቲያችን ብልጽግና የያዛቸውን ታላላቅ የልማትና የመልካም አስተዳደር ዕቅዶች ለማሳካት በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ የጎላ ሚና እንደሚኖረው አመላክተዋል።

​የኢሉአባቦር ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ምትኬ ለገሰ በበኩላቸው፥የኢሉአባቦር ዞን ወጣቶች ክንፍ ክልላዊ ወሰንን አልፈው ወደ አኙዋኣ ብሔረሰብ ዞን የመጡት አካላዊ ርቀትን ሰብረው ከወንድም ህዝቦች ጋር ያላቸውን ፍቅርና አብሮነት በተግባር በማሳየት የዜግነት አገልግሎት ለማበርከት መሆኑን ጠቁመዋል።

ወጣቱ ትውልድ የሀገሪቱን የሰላም፣ የልማት እና የዴሞክራሲ ጉዞ በባለቤትነት እየመራ መሆኑን የገለፁት ወይዘሮ ምትኬ፥የዛሬው የዜግነት አገልግሎት መርሃ ግብሩ የብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ከፍታ በወጣቶች ጉልበት እና ትብብር እውን ለማድረግ የያዘውን ፅኑ አቋም የሚያሳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

በተለይም ብልጽግና ፓርቲ ልዩነቶችን እንደ ጸጋ ወስዶ በጋራ በመቆም ኢትዮጵያን በጋራ ለመገንባት የሚያስችለውን አቅጣጫ በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ጠቁመዋል።

ለአኙዋኣ ብሔረሰብ ከተደረገላቸው ድጋፎች ፍራሽ ፣ብርድ ልብስ፣ ፣ደብተር ፣እስክሪብቶ፣ቦርሳ ፣የምግብ ዘይትና ሳሙና እንደሚገኝባቸውን ወይዘሮ ምትኬ ጨምሮ ገልጸዋል።

የጋምቤላ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የባህልና ዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዘርፈ ኃላፊ አቶ ፔን ኡጁሉ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ፥የኢሉአባቦር ዞን ወጣቶች ወሰን ተሻግረው ያሳዩት የዜግነት አገልግሎት ተግባር የኢትዮጵያ ህዝቦች በተለይም የወጣቶች ትስስር ምን ያህል የፀና እና የማይበጠስ መሆኑን ህያው ማሳያ ነው ብለዋል።

አያይዘውም የጋምቤላ ክልል ህዝብ ከሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች ከመጡ ወንድም ህዝቦች ጋር ባለው ታሪካዊ ትስስር እንደሚያኮራ ገልጸው፣ የብልጽግና ፓርቲ እውነተኛ ሀገራዊነትን እና ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን በተግባር እየገነባ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም የኦሮሚያ እና የጋምቤላ ክልል ህዝቦች ከጥንት ጀምሮ የነበራቸውን የጋራ እሴቶችን ይበልጥ የሚያጸና እና ወሰን አቋርጦ የሚቀጥል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከሪያ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን  ለማጠናከር  በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ  የሚሳተፉ የጋምቤላ ክልል እንግዶች ደምቢዶሎ ከተማ ገቡየቡድኑ አባላት  ውይይቱ በሚካሄድበት ወደ ደምቢዶ...
04/09/2026

የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን ለማጠናከር በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የሚሳተፉ የጋምቤላ ክልል እንግዶች ደምቢዶሎ ከተማ ገቡ

የቡድኑ አባላት ውይይቱ በሚካሄድበት ወደ ደምቢዶሎ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል

ከክልሉ በመድረኩ ላይ የሚሳተፉ እንግዶች ደንቢዶሎ አየር ማረፍያ ሲደርሱ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የሁለቱ ክልሎች የጋራ የውይይት መድረክ በነገው ዕለት እንደሚካሄድ ተገልጿል

Address

Gambella
Gambela

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gambella Mass Media Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share