Gambella Prosperity Party- ብልጽግና

Gambella Prosperity Party- ብልጽግና ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያ ገዥ ፓርቲ ነው ! ጋምቤላ ብልጽግና ፓርቲ

የመንግሥት ኢንቨስትመንቶች አቅጣጫን የማሳየት፣ የማስቀየርና ሽግግርን የመፍጠር ተልዕኮ አላቸዉ፡፡ የመደመር መንግሥት ገጽ 140
03/09/2026

የመንግሥት ኢንቨስትመንቶች አቅጣጫን የማሳየት፣ የማስቀየርና ሽግግርን የመፍጠር ተልዕኮ አላቸዉ፡፡

የመደመር መንግሥት ገጽ 140

03/09/2026
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ወሰን ተሻጋራ የክረምት በጎ ፈቃድ አምባሳደሮች በጋምቤላ የሚገኙ የጤና ተቋማት የዓይነት ድጋፍ አበረከቱ ​"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በደቡ...
02/09/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ወሰን ተሻጋራ የክረምት በጎ ፈቃድ አምባሳደሮች በጋምቤላ የሚገኙ የጤና ተቋማት የዓይነት ድጋፍ አበረከቱ

​"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ የክረምት በጎ ስራ ወጣት አምባሳደሮች በጋምቤላ አጠቃላይ ሆስፒታል እና በጋምቤላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተኝተው ለሚታከሙ ህሙማን የዓይነት ድጋፍ አበርክተዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ለህሙማን እንክብካቤ እና ይገዛ የሚሆኑ ልዩ ልዩ የዓይነት ድጋፎች የተበረከቱ ሲሆን፣ በተለይም በሆስፒታሎቹ ውስጥ የሚገኙ ተኝቶ ታካሚዎችን ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከክልል ወሰን በላይ በመሻገር የአንድነት፣ የመደጋገፍ እና የጋራ ልማት ባህልን በተግባር ያሳየበት መሆኑን ተገልጿል።

በተለይም በሁለቱ አጎራባች ክልሎች መካከል ያለውን ወንድማማችነት እና ህዝባዊ ወዳጅነት ከማጠናከርም ባለፈም ለቀጣይም ተመሳሳይ ህዝባዊ አገልግሎቶችን በጋራ ለመስራት መንገድ የሚከፍት መሆኑን አጽንኦት ተሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣...
02/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!

የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናትና በፈጠራ በመሻገር፣ በአሁን ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ዘይቤ ውስጥ ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ወረቶች የሚደመሩበት እንዲሁም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር በመሆሃ በሳቢ ኹነቶችና የንቅናቄ መንገዶች የሚመራ ይሆናል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ እንደሚሆንም የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አመላክቷል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት፤ ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ወሰን ተሻጋራ የክረምት በጎ ፈቃድ አምባሳደሮች በጋምቤላ ከተማ ማህበራዊ ድጋፍ አደረጉ​"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ...
02/09/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ወሰን ተሻጋራ የክረምት በጎ ፈቃድ አምባሳደሮች በጋምቤላ ከተማ ማህበራዊ ድጋፍ አደረጉ

​"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ሀሳብ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ የክረምት በጎ ስራ ወጣት አምባሳደሮች በጋምቤላ ከተማ ለሚገኙ ወላጅ አልባ ተማሪዎች እና ለመቄዶኒያ የአረጋውያን ማዕከል የቁሳቁስና የዓይነት ድጋፍ አድርገዋል።

የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ቱት ጆክ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት፤ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት፣ሰው ተኮር አሰራር እና የማህበራዊ ፍትህ እሴቶችን በተግባር ያሳየ ነው ብለዋል። በተለይም ወሰን ተሻጋሪ ተግባራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ከማጠናከርም ባለፈም ለተቸገሩ ወገኖች፣ለወላጅ አልባ ህጻናትና ለአረጋውያን ትልቅ ተስፋ መሆኑን ጠቁመዋል ።

በተለይም ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የወንድማማችነት እሴቶችን ከማጠናከር ባለፈም በህዝቦች መካከል ያለው ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ እንዲጎለበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም አስታውቀዋል ።

​የጋምቤላ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የባህልና ዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ፔን ኡጁሉ በበኩላቸው፥ብልጽግና ፓርቲ በልዩነት ውስጥ ያለውን ውበትና አብሮነት በማጠናከር ረገድ ወጣቶች የለውጡ ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆኑ ትኩረት እነሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በተለይም ወጣቶች የሰላም፣ የልማት እና የህብረተሰብ አቀፍ ድጋፍ ሰጪዎች በመሆን የሀገሪቱን ከፍታ እንዲያረጋግጡ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር የፓርቲው ቁልፍ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም ​ይህ ዜጋ ተኮር ልማትና እንክብካቤ መርሃ ግብር ወጣቶች ከክልል ወሰን ወጥተው ለወገን የሚቆሙበትን አቅም ያሳየና የብልጽግና ፓርቲን የህብረተሰብ ተኮር አስተሳሰብ በተግባር የገለጸ ታላቅ ሀገራዊ እርምጃ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተወል።

በክልሎች መካከል የተጀመሩ በጎ አድራጎታዊ ተግባራት ህዝብ ለህዝብን የሚያጠናክሩና የጋራ ልማታችንን የሚያፋጥኑ በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የባህልና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ግርማ ባሻ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፥የበጎ ፈቃድ ስራዎች የፓርቲውን የህዝብ ተኮር ፖሊሲዎች በተግባር ማሳያ መሆናቸውን ጠቁመው፣ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" መሪ ሀሳብ ኢትዮጵያን በጋራ ጥረት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የምንተጋበት ማሳያ ነው ብለዋል።

በተለይም ​ህዝባዊና ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድ ፓርቲው የተለያዩ ክልሎችን እና ማህበረሰቦችን በበጎ አድራጎት እና በጋራ ልማት በማስተሳሰር የኢትዮጵያን አንድነት በጠንካራ ማህበራዊ መሰረት ላይ መገንባትን ዓላማ አድርጎ እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይም ወጣቶቻችን በእውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና ባላቸው አቅም ሁሉ ማህበረሰባቸውን እና ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸውን ገልጸው፥ ተግባሩ የብልጽግና ፓርቲን ሰብአዊነትንና አብሮነትን ማዕከል ያደረገ የልማትና የበጎ አድራጎት አቅጣጫ ቁልፍ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲን የለውጥ ሥራ አደነቀ።በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ነብዩ ስሑል የተመራ...
01/09/2026

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲን የለውጥ ሥራ አደነቀ።

በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ነብዩ ስሑል የተመራ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ልዑክ በቻይና ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።

ልዑኩ በቤጂንግ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የአፍሪካ ጉዳዮች ኮሚቴ ጋር የፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነትን በተመለከተ ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ ላይ አቶ ነብዩ ስሑል፣ ብልፅግና ፓርቲ የሚመራበት የመደመር እሳቤና የፓርቲው ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ለሚታዩት ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ለውጦች ዋነኛ መሠረት መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤታማነት፣ የከተማና የገጠር ልማትን በተቀናጀ መልኩ ማከናወን፣ ሕዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች እና የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የፓርቲውን የእሳቤ ጥራትና የማስፈጸም አቅም የሚያሳዩ ዋነኛ ተግባራት መሆናቸውንም አቶ ነብዩ ጠቁመዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከሀገር ውስጥ የልማት ሥራ ባሻገር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ አቅም እያጠናከረ ያለ ተግባር መሆኑንም ገልጸዋል።

በፖለቲካው መስክ እየተመዘገቡ ያሉ አበረታች ለውጦችን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ በ2026 የአፍሪካ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጉባኤን በአዲስ አበባ ለማስተናገድ መመረጧንና ለጉባኤው ዝግጅት እያደረገች መሆኗን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል፣ ልዑኩን የተቀበሉት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል ወ/ሮ ሪኦ ዩሃ ብልፅግና ፓርቲ “ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግሥት፤ ጠንካራ መንግሥት ለጠንካራ ሀገር” በሚል እሳቤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እያስመዘገበ ያለውን ለውጥ ፓርቲያቸውና መንግሥታቸው በከፍተኛ አድናቆት እንደሚከታተሉ ገልጸዋል።

ወ/ሮ ሪኦ ዩሃ አክለውም፣ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲና ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነት የሚያደርጉትን ትብብር እና የጋራ ጥቅሞችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ቅንጅት በቀጣይ ለማጠናከር ፓርቲያቸው ጠንካራ አቋም እንዳለው አረጋግጠዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ልዑክ በቤጂንግ በነበረው የመጀመሪያ ቀን ውሎ፣ ከሁለትዮሽ ውይይቱ በተጨማሪ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን ታሪክ፣ ልምድ፣ ድሎችና ተግዳሮቶች የሚያሳየውን የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ሙዚየም ጎብኝቷል።

ጉብኝቱ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ካለፈው ታሪኩ በመማር የአሁኑን ስኬቶች እንዴት እያጠናከረ እንደሚገኝና የወደፊት ራዕዩን ለማሳካት እያከናወነ የሚገኘውን እንቅስቃሴዎች ለመመልከት ጠቃሚ የመማማሪያ ልምድ ሆኗል።

በቀጣዮቹ ቀናት የሁለቱ ፓርቲዎች አመራሮች የጋራ ልምድ የሚጋሩበትና እርስ በእርስ የሚማማሩበት መርሃ ግብር ይከናወናል።

Address

Gambela

Telephone

+251908218626

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gambella Prosperity Party- ብልጽግና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share