27/03/2026
በኢትዮጵያ ግብርና የሀገር ኢኮኖሚ መሠረት ነው!!
በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ የግብርናው ዘርፍ ለሀገር እድገት መሠረት ነው። የግብርናችን እድገት ለኢንዱስትሪ ትልቅ ግብዓት ይሆናል። ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ፣ የወጪ ንግድን ለማሳደግና ኢንዱስትሪን ለማስፋፋት እያመረተች ትገኛለች። ማንኛውም የሀገር እድገት የሚመጣው ምርታማነትን ከማሳደግ ነው። በሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ምርትን ለማሳደግ በርካታ ምቹ ሁኔታዎች አሉ። ግብርናው ዘርፍ በርካታ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ረገድም ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ስለሆነም የብልጽግና መንግሥት ለግብርናው ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ድህነትን እየቀነሰ ይገኛል። ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን ቀድመው በመገንዘብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ሰፊ ሥራዎችን ሰርተዋል። በመንግሥት ዕቅድ ውስጥ ግብርናን ማዘመን፣ የግብርና ቴክኖሎጂን ማስፋፋት፣ የመስኖ ሥርዓትን ማጠናከር እና ለገበሬው በቂ የግብርና ግብዓት ድጋፍ እንዲያገኝ የማድረግ ጠንካራ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የገበሬውን ገቢ በመጨመር ድህነትን ለመቀነስ ከፍተኛ ድርሻ አለው።