Gondar City Education Department/ጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • Gondar City Education Department/ጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ

Gondar City Education Department/ጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ It's all about Gondar, Amhara, Ethiopia Education. ስለ ጎንደር-አማራ-ኢትዮጲያ ትምህርት እናወራለን።
(2)

በጎንደር ከተማ በማራኪ ክፍለ ከተማ ሲቪ አር ፕሮጀክት ለ53 ተማሪዎች ለአካል ጉዳተኞች የትምህርት ቁሣቁስ ደብተር ድጋፍ አደረገ።በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለ ከተማ ሲቪ አር ፕሮጀክት ለ53 ...
03/09/2026

በጎንደር ከተማ በማራኪ ክፍለ ከተማ ሲቪ አር ፕሮጀክት ለ53 ተማሪዎች ለአካል ጉዳተኞች የትምህርት ቁሣቁስ ደብተር ድጋፍ አደረገ።

በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለ ከተማ ሲቪ አር ፕሮጀክት ለ53 አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ፕሮጀክቱ በተማሪዎቹ የትምህርት ተሳትፎና የመማር ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ቁሳዊ ችግሮችን ለማቃለል ያደረገው ድጋፍ ደብተርን ጨምሮ የትምህርት ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው።

የድጋፉ ዓላማ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከሌሎች ተማሪዎች እኩል የመማር ዕድል እንዲያገኙ፣ በትምህርታቸው እንዲበረታቱና የትምህርት ህልማቸውን እንዲያሳኩ ማገዝ መሆኑ ተገልጿል።

ትምህርት ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን የሚደረጉ እንዲህ ያሉ ድጋፎች ማኅበራዊ አካታችነትን ከማጠናከር ባለፈ፣ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች በችግሮች ሳይሸነፉ በትምህርት ላይ እንዲቆዩ የሚያበረታቱ ናቸው።

“ማንም ተማሪ በቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት መራቅ የለበትም” የሚል መርህን በመከተል፣ የተማሪዎቹን ትምህርታዊ ተስፋ ለማጠናከር የሚደረጉ ድጋፎች እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።

ወገን የህፃናትና የእናቶች መረጃ ድርጅት ለ30 ዓይነ ስውራን ተማሪዎች የትምህርት  ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገወገን የህፃናትና የእናቶች መረጃ ድርጅት ከ2015 ዓ.ም. ጀምሮ በወርኃዊ የገንዘብ ድ...
01/09/2026

ወገን የህፃናትና የእናቶች መረጃ ድርጅት ለ30 ዓይነ ስውራን ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

ወገን የህፃናትና የእናቶች መረጃ ድርጅት ከ2015 ዓ.ም. ጀምሮ በወርኃዊ የገንዘብ ድጋፍ እየደገፋቸው ለሚገኙ 30 ዓይነ ስውራን ተማሪዎች የቀጣዩ የትምህርት ዘመን በስኬት እንዲጀምሩ የአልባሳት፣ የትምህርት ቁሳቁስ እና የንፅህና መጠበቂያ ድጋፍ አድርጓል።

ድርጅቱ እስከ 12ኛ ክፍል እና በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የሚማሩ ዓይነ ስውራን ተማሪዎችን በቋሚነት ከሚያደርገው የወርኃዊ የገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ፣ የቀጣዩን የትምህርት ዘመን በተሻለ ሁኔታ እንዲጀምሩ ተጨማሪ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።

የወገን ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ኅብስት መኮንን በድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በተለይም በትምህርት ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

ወገን በተቻለው አቅም ሁሉ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ እየሰራ ሲሆን፣ ወደፊትም ይህንን ተግባር ማጠናከር እንደሚቀጥል ወይዘሮ ኅብስት ገልጸዋል።

ወገን በዓይነ ስውራን ተማሪዎች ዙሪያ መስራት ከጀመረ ጀምሮ ተማሪዎቹ ውጤታማ እንዲሆኑ የተቻለውን ሁሉ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ጠቁመዋል።

የክረምቱን የትምህርት ጊዜ በስኬት በማጠናቀቅ በ2019 ዓ.ም. የትምህርት ሂደታችሁን በስኬት እንድታከናውኑ ይህ ድጋፍ መደረጉን ገልጸው፣ “2019 ዓ.ም. የደስታና የስኬት ዓመት እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ነጋሽ በበኩላቸው፣ ወገን በተለይም በትምህርት ዙሪያ እያደረገ ያለው ድጋፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው፣ በትምህርት መምሪያው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

ወገን በትኩረት ለሚሹ ወገኖች እንዲህ ዓይነት ድጋፍ ማድረጉ ትልቅ አስተዋፅኦ መሆኑን ገልጸው፣ ድጋፍ የተደረገላቸው ተማሪዎችም በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ለዚህ ድጋፍ አስደሳች ምላሽ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

ተማሪዎቹ በትምህርታቸው በርትተው በመማር ለሀገር፣ ለወገን እና እንደነሱ ላሉ ወገኖች ምሳሌ በመሆን በሞራል ግንባታ ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱም ተስፋ እንዳላቸው አቶ ስንታየሁ ገልጸዋል።

የትምህርት መምሪያው የሚችለውን ድጋፍ በማድረግ ከተማሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አረጋግጠዋል።

በድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ የጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ሲሳይ ጣሰው ፣ከጎንደር ከተማ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ወይዘሮ መሪም የሱፍ ተገኝተዋል።

ድጋፍ የተደረገላቸው ተማሪዎችም ወገን ከጎናቸው በመሆን እያደረገላቸው ያለው ድጋፍ በትምህርታቸውና በሕይወታቸው ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም የአልባሳት፣ የፖርሳ እና የንፅህና መጠበቂያ ድጋፉ ቀጣዩን የትምህርት ዘመን በደስታና በተስፋ እንዲጀምሩ መልካም መሆኑን ገልፀው ለወገን ድርጅት ምስጋናቸውን አቅርበዋል ሲል ጃንተከል ክፍለ ከተማ ዘግቧል።

🏆 ጎንደር ከተማ በአፈጻጸም አንደኛ ደረጃን በመያዝ የዋንጫና የመኪና ሽልማት ተበረከተለት! 🎉በአማራ ክልል በ2018 በጀት ዓመት በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች የተመዘገበው ...
01/09/2026

🏆 ጎንደር ከተማ በአፈጻጸም አንደኛ ደረጃን በመያዝ የዋንጫና የመኪና ሽልማት ተበረከተለት! 🎉

በአማራ ክልል በ2018 በጀት ዓመት በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች የተመዘገበው አፈጻጸም ተገምግሞ፣ ከከተማ አስተዳደሮች መካከል ጎንደር ከተማ አንደኛ ደረጃን በመያዝ የዋንጫና የመኪና ሽልማት ተቀብሏል። 🏆🚗

ይህ ውጤት የጎንደር ከተማ አስተዳደር በሰላም ግንባታ፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ያከናወናቸው ተግባራትና ያስመዘገባቸው ውጤቶች እውቅና ያገኙበት ነው።

👏 ለዚህ ውጤት ለተጋችሁ የከተማዋ አመራሮች፣ ሠራተኞችና መላው የጎንደር ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ!

💚 ጎንደር ከተማ — በተግባር የሚመዘን ስኬት!
#ጎንደር

Gondar City Education Department/ጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ

🚀 የሳይንስ እና ፈጠራ አቅማችሁን ለዓለም የምታሳዩበት ወርቃማ ዕድል! 🔬💡​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በበጀት ዓመቱ በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል...
27/08/2026

🚀 የሳይንስ እና ፈጠራ አቅማችሁን ለዓለም የምታሳዩበት ወርቃማ ዕድል! 🔬💡

​የጎንደር ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በበጀት ዓመቱ በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ያሉ የፈጠራ አቅም ያላቸውን ተማሪዎች አወዳድሮ በሀገር አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ውድድር ላይ ለማሳተፍ የአካባቢያዊ የሳይንስ ፈጠራ (Local Science Fair) ውድድር አዘጋጅቷል።

​በመሆኑም በፈጠራ ሥራዎቻችሁ መወዳደር የምትፈልጉ ተማሪዎች እስከ መስከረም 15/2019 ዓ.ም ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

​የውድድር ዘርፎች (Categories)፦
1️⃣ የጤና፣ ግብርና እና አካባቢ ችግሮች መፍትሔ (Health Tech, Agriculture & Environmental Solutions)
2️⃣ የማምረቻና ኢንዱስትሪ (Manufacturing & Industrial Solution)
3️⃣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እና የሶፍትዌር ልማት (Digital Technology & Software Dev't)
4️⃣ ሮቦቲክስ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች (Robotics & Emerging Technology)

​📝 የአመዘጋገብ እና የፈጠራ ሥራ ማስረከቢያ መንገድ፡
ተወዳዳሪዎች ሙሉ ስም፣ ዕድሜ፣ ጾታ፣ የክፍል ደረጃ፣ የመጡበት ትምህርት ቤት እና የፈጠራ ሥራችሁን ዝርዝር መግለጫ (Proposal) በመያዝ፦
​📧 በኢሜይል፡ [email protected] በመላክ ወይም
​🏢 በአካል፡ በዩኒቨርሲቲው ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ማዕከል አስተባባሪ ቢሮ በመገኘት መመዝገብ ትችላላችሁ።

​📅 ማስታወሻ፦
​የምዝገባ ማብቂያ ቀን፡ እስከ መስከረም 15/2019 ዓ.ም
​ውድድሩ የሚካሄድበት ቀን፡ ጥቅምት 11 - 12/2019 ዓ.ም
​📍 ዒላማ የተደረጉት፡ በጎንደር ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚገኙ የ9ኛ - 12ኛ ክፍል ተማሪዎች።

​✨ የነገ የቴክኖሎጂ ባለቤቶች ዛሬ ይፈጠራሉ! እድሉን ተጠቀሙበት!

​📲

እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸው ተማሪዎች 100% ሙ...
26/08/2026

እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸው ተማሪዎች 100% ሙሉ በሙሉ 50% እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል 📈📚

በአማራ ክልል ይህንን ድንቅ ውጤት ካስመዘገቡ 8 ትምህርት ቤቶች መካከል 2ቱ በከተማችን የሚገኙ በመሆናቸው ታላቅ ኩራት ይሰማናል 👏🏫

በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጎንደር ከተማ ተፈታኞች ከፍተኛውን ውጤት ያመጣው የአዘዞ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ዳግም በሪሁን ጌታቸው ሲሆን ያስመዘገበ...
26/08/2026

በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጎንደር ከተማ ተፈታኞች ከፍተኛውን ውጤት ያመጣው የአዘዞ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ዳግም በሪሁን ጌታቸው ሲሆን ያስመዘገበው ውጤት 576.45 ነው።

#ከሀገርተስፋዎች👏

የትምህርት ስራችን ውጤታማ ለማድረግ የተማሪ ወላጆች ማህበር ሚና የጎላ ነው።አቶ መኳንት አደመ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊየአማራ ክልል የተማሪ ወላጆች ማህበር አመታዊ ጉባኤውን...
25/08/2026

የትምህርት ስራችን ውጤታማ ለማድረግ የተማሪ ወላጆች ማህበር ሚና የጎላ ነው።
አቶ መኳንት አደመ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ

የአማራ ክልል የተማሪ ወላጆች ማህበር አመታዊ ጉባኤውን ዛሬ በባህርዳር ከተማ አካሂዷል።

በጉባኤው መክፈቻ የተገኙት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንት አደመ የትምህርት ስራችን ውጤታማ ለማድረግ የተማሪ ወላጆች ማህበር ሚና የጎላ ነው ብለዋል።

ባለፈው ዓመት ከ3 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ የሆኑበተና 2ሺ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች አለመከፈታቸውን የገለጹት ኃላፊው በቀጣይ የትምህርት ዘመን ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ የማህበሩ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

የተማሪ ወላጆች ማህበር አደረጃጀት በትምህርት ቤት፣ በወረዳ፣ በዞን፣ በክልል እንዲሁም በሀገር ደረጃ ጠንካራ አደረጃጀት እንዲኖር በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።

በዚህ ጉባኤ የምትሳተፉ አካላት 7.6 ሚሊየን ተማሪዎችን ወክላችሁ የመጣችሁ መሆኑን ተረድታችሁ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ሲሉ ሀላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

በጉባኤው የሀገር አቀፍ የተማሪ ወላጆች ማህበር አደረጃጀትና አተገባበር መመሪያ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

የተማሪ ወላጆች ማህበር የትምህርት ቤት ወላጅ ግንኙነትን በማጠናከር የመማር ማስተማሩን ሂደት ውጤታማ ማድረግ ይገባል ነው የተባለው።

የውይይት ተሳታፊዎች በበኩላቸው የመማር ማስተማሩን ሂደት ውጤታማ ለማድረግ ማህበረሰቡን በማስተባበር የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ረገድ ሰፊ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ማህበሩ ከአደረጃጀት ባለፈ በእቅድና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም ተገልጿል። የተቀበልነው የትውልድ አደራ ነው ያሉት የጉባኤው ተሳታፊዎች ክልሉ ከገጠመው የትምህርት ስብራት ለመውጣት በቅንጅት ልንሰራ ይገባል ኢሉ በአጽንኦት ተናግረዋል።

ማህበሩ በትምህርት ቤት ውስጥ ያለውን ክፍተት በመለየት የመማር ማስተማሩን ስራ ውጤታማ ማድረግና በባለቤትነት ስሜት መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የቀድሞው የአማራ ክልል የተማሪ ወላጅ ማህበር አመራር ባለፍት አመታት ብዙ ውጣውረድ አይተን የተሻለ ሰርተናል አዲሱ አመራር በቀጣይ የተሻለ ስራ እንዲሰራ ከጎን ሆነን እናግዛለን ብለዋል።

በጉባኤው ማጠቃለያ ከጉባኤው ተሳታፊዎች በተመረጡ አስመራጭ ኮሚቴዎች 22 የክልልና 5 የፊደራል አዲስ የስራ አስፈፃሚዎች የተመረጡ ሲሆን የአማራ ክልል የተማሪ ወላጆች ማህበር ፕሬዘዳንት ኢንጅነር አስማማው አከለን በመምረጥና አዲሱ አመራር ከነባሩ አመራር የስራ ርክክብ በማድረግ ጉባኤው ተጠናቋል።

የቅጥር  #ማስታወቂያበጌምድር አካዳሚ ጎንደር ከተማ
25/08/2026

የቅጥር #ማስታወቂያ

በጌምድር አካዳሚ
ጎንደር ከተማ

🚨 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ!​"የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ"— የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት​የ2018 ትምህ...
25/08/2026

🚨 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች በሙሉ!

​"የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ"
— የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

​የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አማራጭ አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።

​ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ከታች በተቀመጡት ሊንኮች (Links) በመግባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ።

​📌 የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜን በተመለከተ፦
ቅሬታ ያለው ማንኛውም ተፈታኝ በአካል መምጣት ሳያስፈልገው ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ማስፈንጠሪያ ቅሬታውን ማቅረብ እና ምላሹንም በዚያው መከታተል የሚችል መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል።

​👇 ውጤት ለማየት እና ቅሬታ ማቅረቢያ ሊንኮችን ከታች በአስተያየት መስጫ ሳጥን (Comment Box) ውስጥ ያገኛሉ!

Address

Gondar

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 11:30
13:30 - 17:30

Telephone

+251581110123

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gondar City Education Department/ጎንደር ከተማ ትምህርት መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share