Dansha Town Communication affairs office

Dansha Town Communication affairs office በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን የፌስ ቡክ ገፅ

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሚሊሻ 30ኛው ዓመት የምስረታ ክብረ በአል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ ።ዳንሻ ፡ግንቦት 21/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ...
29/05/2026

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሚሊሻ 30ኛው ዓመት የምስረታ ክብረ በአል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ ።

ዳንሻ ፡ግንቦት 21/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሚሊሻ 30ኛው ዓመት የምስረታ ክብረ በአል በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል ።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብድልዋህብ ማሙ ሚሊሻ ማለት ከህዝብ ለህዝብ የወጣ፤ ሁሌም ከህዝብ እና መንግስት ጎን በመሆን ለህልውናችን መሰረት የሆነ፤
የህዝብ አንድነትን በመጠበቅ ለሀገር ክብር የቆመና ቆርጦ የሚሰራ ሀይል ነው ብለዋል ።

ከንቲባው አክለውም የሚሊሻ ሀይል የሀገራችንን ሆነ የክልላችንን ህዝቦች ህገመግስታዊ መብቶችን በማስከበር ሰላምና ደህንነቱን በመጠበቅ፤

እንዲሁም በውስጣችን ተሰግስጎ የሚገኘው የፅንፈኛው ሀይሎች ጋር ትልቅ መስዋዕት በመክፈል ሀገራዊ ተጋድሎውን እያበረከተ ይገኛል ብለዋል ።

በአማራ ክልል ሚሊሻ መምሪያ የዘመቻ ኃላፊ አቶ ይታገስ አምባቸው የሚሊሻ የ30ኛ አመት የምስረታ በአልን ስናከብር አለማው ሚሊሻ የሰላማችን መሰረት የአድነታችን ደጀን የሆነ እና የሀገራችንን ታሪክ በደምና አጥንቱ የፃፈልን ድንቅ የህዝብ ልጅ መሆኑን ለወዳጆቻችን የምናሳይበት ነው ብለዋል ።

አቶ ይታገስ አክለውም ምንዘጋጀው ለሀገራችን የጭንቅ ቀን ደጀን እና ዘብ ለመሆን እንዲሁም ለሚሰነዝሩብን ጥቃት ለመመለስ ብቻ ሳይሆን ጠላት ሊደፍራት ሲያስብ ስሙ ቀድሞ በህሊናው ሊታወሰው የሚገባው ሀይል ለመመስረት ግድ ነው ብለዋል።

እንዲሁም ኮምሽነር ጋሻው መልካሙ በበኩላቸው የሚሊሻ ሀይላችን ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ላለፈችበት ውጣ ውረድ እና ሉአላዊነቷ ያበረከተው አስተዋፆ ትልቅ እንደሆነ አስተው ፤

በፊት ከጥንት ነጭ ለባሽ፣ሰላም አስከባሪ እንዲሁም አሁን ላይ ሚሊሻ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት በህግ እና በደምብ እየተመራ እስካለበት ድረስ ብዙ ፈተናዎችን አልፎ በጀግንነት ዛሬ ላይ መድረሱ ለፈተናዎች አይበገሬነቱን ማሳያ ነው ብለዋል።

በዕለቱ ስለ ሚሊሻ ታሪካዊ አመጣጥ ጅማሮ እስከ አሁናዊ ቁመናው በፅሁፍ ያቀረቡት የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፖርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ማሩ ሲሆኑ በአፍሪካ ጠንካራ እና የተደራጀ የሚሊሻ ሀይል ካላቸው ሀገራት ኢትዮጵያ ግምባር ቀደምት መሆኗን አንስተዋል ።

ሚሊሻችን በህግ እና በጠንካራ ወታደራዊ ስነምግባር የሚመራ የሀገራችንን ሉአላዊነት ለማስከበር ከመደበኛው ሀይላችን ጋር በመሆን ሰላሙን እያስጠበቀ እንደሚገኝ ገልፀው፤

የሚሊሻው ሚና አሰተማማኝ ሰላም እና መረጋጋት ከመፍጠር እንዲሁም በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ጊዜ ከህዝብ እና መንግስት ጎን በመሆን የህዝብ አለኝታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል ብለዋል።

በመጨረሻም ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሚልሻ አባላት የእውቅናና የሽልማት መርሐ ግብር በማካሄድ በአሉ ተጠናቋል ።

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሚሊሻ 30ኛው ዓመት የምስረታ ክብረ በአል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ነው ።ዳንሻ ፡ግንቦት 21/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳን...
29/05/2026

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሚሊሻ 30ኛው ዓመት የምስረታ ክብረ በአል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ነው ።

ዳንሻ ፡ግንቦት 21/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሚሊሻ 30ኛው ዓመት የምስረታ ክብረ በአል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል ።

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በድምቀት ተከበረ።ዳንሻ፦ግንቦት 19/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳ...
27/05/2026

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በድምቀት ተከበረ።

ዳንሻ፦ግንቦት 19/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር 1447ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በድምቀት ተከብሯል ።

በበአሉ የተገኙት ከንቲባ አብዱልዋሀብ ማሞ፣የፓርቲ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ማሩ፣የእስልምና ጉዳዮች ሰብሳቢ አቶ መሀመድ ቃሲም፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የከተማው የእስልምና እምነት ተከታዮች ተገኝተዋል ።

በበአሉ የተገኙት ከንቲባ አብዱልዋሀብ ማሞ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት በማስተላለፍ ከበአሉ እንደምንረዳው የመታዘዝ፣የመስዋዕትነት፣ ያለመጠራጠር፣ የእምነት ማረጋገጫ ታላቅ በዓል ነው ብለዋል ።

አቶ ሀብታሙ ማሩ በበኩላቸው ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሃ በዓል በሰላም አድረሳችሁ አደረሰን በማለት፤

በአሉ ስናከብር እርስ በእርሳችን በመደጋገፍ እና በመቻቻል፣ በመተባበርና በአብሮነት ሊሆን ይገባል ብለዋል ።

እንዲሁም በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የእስልምና ጉዳዮች ሰብሳቢ አቶ መሀመድ ቃሲም እንዳሉት በአሉ ሀይማኖታዊ ትውፊቱ በጠበቀ መልኩ ማክበር አለብን ያሉ ሲሆን ፤

መላው የከተማችን ህዝበ ሙስሊም ለረዢም ዓመታት እየጠየቀ የቆየው የመስጊድ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል ።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ የግምገማ መድረክ አካሄደ።ዳንሻ፦ግንቦት 18/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አ...
26/05/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ የግምገማ መድረክ አካሄደ።

ዳንሻ፦ግንቦት 18/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።

በከተማ አስተዳደር የተሰሩ የመንግስት እና የፓርቲ አበይት ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

እንደ ዳንሻ ከተማ አስተዳደር ዘርፈ ብዙ ስራዎች በዚሁ ወር ውስጥ ተከናወነዋል ያሉት ሪፖርቱን በለቱ ያቀረቡት የክላስተር እና ወረዳ አደረጃጀት

ሪፖርቱ ያቀረቡት የዞኑ ደጋፊ አመራር መ/ር ፋኑስ አብርሀም ሲሆኑ በተለይ በፀጥታ ዘርፉ እጅግ አመርቂ ውጤት መምጣቱን አንስተው ካሉት የክላስተር አዋሳኞች የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ግባር ቀደም መሆኑን ገልጸዋል ።

እንደ መ/ር ፋኑስ ገለፃ ከሆነ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ሰላም ከማስጠበቅ አኳያ እየተወሰዱ ያሉት እርምጃዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ከማድረግ አንፃር የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት እና ተደጋግፎ መስራትን ይጠይቃል ብለዋል።

መ/ር ፋኑስ አያይዘዉ ዳንሻ ከተማ አስተዳደር እየሰራቸው ያሉትን የመልካም አስተዳደር ፣የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም አጠቃላይ የቀጠናውን ሰላም እና ፀጥታ አስጠብቆ በማስቀጠል ደረጃ እያበረከተው ያለውን አስተዋፅኦ አድንቀዉ በዚህ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የሁሉም የጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው እንደ ዳንሻ ከተማ አስተዳደር መጠነ ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተው፤

ህገወጥ የቤቶች ግንባታ እና የመሬት ወረራ በከተማው በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ በመሆኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር እልባት መበጀት አለበት ብለዋል።

በተጨማሪም በከተማችን አልፎ አልፎ እየታየ ያለውን ህገወጥ የመሳሪያ ዝውውር እና የሰዎች እገታን በተመለከተ ከፀጥታ አካላት ጋር ከፍተኛ ቅንጅት በማድረግ እርምጃ እየተወሰድ እንዳለ አስገንዝበው ስራውም ቀጣይነት ይኖረዋል ሲሉ ኃላፊዎቹ ገልፀዋል።

የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሠን አስመላሽ የዳንሻ ቅርጫፍ ጽ/ቤት የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ አካሄደ።ዳንሻ፦ግንቦት 16/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ...
24/05/2026

የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሠን አስመላሽ የዳንሻ ቅርጫፍ ጽ/ቤት የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ አካሄደ።

ዳንሻ፦ግንቦት 16/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሠን አስመላሽ የዳንሻ ቅርጫፍ ጽ/ቤት የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ አካሂዷል ።

በመድረኩ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ የአብይ ኮሚቴ ም/ ሰብሳቢ አቶ ጌጤ አዳል፣የዳንሻ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ አብዱልዋህብ ማሙ፣የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ መ/ር ጌታቸው ደሳለኝ ፣የከተማ አስተዳደሩ እና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም አባላት ተገኝተዋል።

በፕሮግራሙ ላይ ለማንነታቸው የተሰው ጀግኖች በማስታወስ የህሊና ፀሎት የተደረገ ሲሆን፤

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ጌጤ አዳል መድረኩ ህልውናችን እና ማንነታችን አስጠብቆ ለመቀጠል ትናንት የተከፈለውን የሂወት እና የአካል መስዋት ሳንረሳ ነገን በማሰብ ትግላችን ጠንካራ አደረጃጀት ፈጥረን መጓዝ እንድችል ነው ብለዋል።

አቶ ጌጤ አዳል አክለውም የወልቃይት ጠገዴ የአማራ የማንነት ታጋይ ለወልቃይት ጠገዴ የማንነት እና የወሰን ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የታገለው ለተጨቆኑ ህዝቦች ሁሉ መሆኑ ታውቆ ትግሉን ዳር ለማድረስ ከሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የሚጠበቅ ጉዳይ ነው ተብሏል።

በመድረኩ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሠን አስመላሽ የዳንሻ ቅርጫፍ ጽ/ቤት የ9 ወር የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እና ግምገማ ተደርጎበታል።

ተሳታፊዎች አማራዊ ማንነታችን ወሰናችን ለማፅናት በማንነቱ የማይደራደር ህብረተሰብና አደረጃጀት በመፍጠር እዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግርን በጋራ እየፈታን ቅንጅታዊ አሰራር ይዘን በቀጣይ ልንሰራቸው የሚገቡን ስራዎች ናቸው ብለዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር እና አጎራባች ወረዳዎች በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ከማህበረሰቡ ጋር የውይይት መድረክ አካሄዱ።ዳንሻ፦ግምቦት14/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ...
22/05/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር እና አጎራባች ወረዳዎች በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ከማህበረሰቡ ጋር የውይይት መድረክ አካሄዱ።

ዳንሻ፦ግምቦት14/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር እና አጎራባች ወረዳዎች በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ከማህበረሰቡ ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል።

በውይይቱ በአማራ ክልል የዞኑ ደጋፊ አቶ አበበ እምቢአለ ፣የዞኑ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዋኘው ደሳለኝ ፣የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብደልዋሀብ ማሞ፣የዞን እና የአጎራባች ወረዳ አመራሮች፣ የፀጥታ አካላት ፣የሀገር ሽማግሌዎችና የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል ።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አብደልዋሀብ ማሞ እንዳሉት የሰከነ ሰላም እንዲኖረን ህዝብ እና መንግስት በተባበረ ክንድ ለህዝብ ሰላም መስፈን ከፍተኛ የሆነ ድርሻ መኖራቸውን አውቀው ስለ ሰላም መጠነ ሰፊ ስራዎች ሊሰሩ ይገባል።

በአማራ ክልል የባህልና ቱሪዝም አመራር አቶ አበበ እምቢአለ በበኩላቸው እንደ ክልል ለሰላምና ለልማት ለማረጋገጥ ዝግጁ መሆናቸውን በማንሳት ፤ ይህ ለማፅናት እንደ ህዝብ የውስጣችን ሰላም ማጎልበት ተገቢ እደሆነ ገልፀዋል ።

ሁላችን እጅ እና ጓንት በመሆን በእገታና ዝርፍያ ወንጀለኞች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰድ እና ቋሚ የሆነ አሰሳ መጀመር እዳለበት የተናገሩት አቶ ጌታቸው ሙሉጌታ ሰላምና ፍትህ ለማግኘት ሁሉም ሀላፊነቱን መወጣት አለበት ብለዋል።

የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዋኘው ደሳለኝ በበኩላቸው በተለያዩ ወንደሎች በርካታ ወጀለኞችን በመያዝ ለህግ አቅርበን ውሳኔ አስወስነናል ያሉ ሲሆን አሁን እየተባባሰ የመጣው ግድያና እገታ በጥብቅ ልናወግዘው እና ልንታገለው ይገባል ብለዋል ።

በመጨረሻም መንግስት የወንጀለኞች አያያዝ እና በተወሰኑ የፀጥታ አካላት ላይ ጠንከር ያለ ለውጥ እንዲያደርግ፤

እንዲሁም ሁሉም የዳንሻ እና አካባቢው ማህበረሰቦች ከፀጥታ አካላት ጎን ተሰልፈው አስፈላጊውን ጥቆማና ወንጀለኞች ለፍርድ እንዲያቀርብ የጋራ ተደርጎ መድረኩ ተጠናቋል።

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት በደጅ አዝማች ደስታ ማሩ  አንደኛና መካከለኛ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የቅድመ አንደኛ ተማሪዎችን አስመረቀ። ዳንሻ፦ ግንቦት 13/2018 ዓ/ም በአ...
21/05/2026

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት በደጅ አዝማች ደስታ ማሩ አንደኛና መካከለኛ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የቅድመ አንደኛ ተማሪዎችን አስመረቀ።

ዳንሻ፦ ግንቦት 13/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት በደጅ አዝማች ደስታ ማሩ አንደኛና መካከለኛ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የቅድመ አንደኛ ተማሪዎችን አስመርቋል ።

በመርሐ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የት/ቤቱ ዕርሰ መምህር የሆኑት መምህርት ብዙአየሁ ትምህርት ለአንድ ሀገር እድገት መሰረት እና የመጀመሪያ ቁልፍ መሳሪያ እንደመሆኑ የትምህርት ዘርፍ ለማሳደግ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን መወጣት አለበት ብለዋል።

ርእሰ መምህሯ አክለውም ሀገርን ማዳን ካስፈለገ ትዉልድ በስነምግባር የታነፀ እና ጠንካራ የት/ት ስርዓት መገባት ለነገ የማይባል የህብረተሰብ እና የመንግስት የቤት ስራ መሆን እዳለበት አሳስበዋል ።

ወላጆች በልጆች አስተዳደግ ዙሪያ ጠንካራ የቤተሰብ መመሪያ ሊኖር እደሚገባ ገልፀዉ ማህበራዊ ማዲያ አጠቃቀማችን መለየት እና መገደብ ከወላጅ የሚጠበቅ ሀላፊነት ነው ።

የወረዳ ደጋፊ መ/ር ጀጃው ተክላይ በበኩላቸው መንግስት የትምህርት ጥራት ለማሻሻል ትልቅ ትኩረት ስጥቶ እየሰራ መሆኑ ገልፀው ፤
በዙሁ አመት በትምህርት ቤቱ ከ73 ተማሪዎች ውስጥ 47ቱ ሴቶች ሲሆኑ ቀሪ 26ቱ ወንዶች መሆናቸው ተናግረዋል ።

እንዲሁም መ/ርት እጅንሱ ት/ቤቱ እንዳሀገር ትውልድ የማፍራት ሀላፊነቱን እየተወጣ ሲሆን በቀጣይ ለሀገር እና ለወገን የሚቆረቆር ዜጋ ማፍራት ካስፈለገ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስት መንት ፅ/ቤት በመስክ ምልከታው ላይ ጠንካራ እና መሻሻል ስላለባቸው ጉዳዮች ተወያይተው የቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።ዳንሻ ግንቦት...
18/05/2026

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስት መንት ፅ/ቤት በመስክ ምልከታው ላይ ጠንካራ እና መሻሻል ስላለባቸው ጉዳዮች ተወያይተው የቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።

ዳንሻ ግንቦት 10/2018ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት የዞን አመራሮች እና የከተማው አስተዳደር ከፍተኛ ሀላፊዎች በተገኙበት የተወያየ ሲሆን፤

በፅ/ቤቱ ተግዳሮት እየሆነበት ያለው ባለሀብቶች በራሳቸው ቦታ መርጠው የመውሰድ ፍላጎት ተነስቶ በአስተዳደሩ ሳይትፕላን መሰረት ብቻ መስተናገድ እዳለባቸው የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀሀየ በላይ ገልፀዋል።

በአጠቃላይ የሚያስፈልጉ የመብራት ፣የውሃ እና የመንገድ ስራዎች እዲሰሩ የመፍትሄ አቅጣጫ የተነሳ ሲሆን በሊዝ የተያዙ ቦታዎችን ውሳኔ በመስጠት ከ3ተኛ ወገን ነፃ አድርጎ ማስረከብ እየተሰራባቸው መሆኑን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ማሩ ተናግረዋል

በተጨማሪም ከባለሀበቶች እንዲሁም ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከተማውን ለልማት ሳቢ እና ተመራጭ በማድረግ በኩል ለወደፊት መሰራት እንዳለባቸው መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስት መንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረጀ ደመቀ ሲሆኑ መሻሻል ያለባቸውን ነገሮች በመነጋገር ማሻሻል ይቻላል ብለዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር  ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት ከዞን ከመጡ አመራር ጋር የመስክ ምልከታ አደረጉ።  ዳንሻ፦ ግንቦት 10/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁ...
18/05/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት ከዞን ከመጡ አመራር ጋር የመስክ ምልከታ አደረጉ።

ዳንሻ፦ ግንቦት 10/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት ከዞን ከመጡ አመራሮች እንዲሁም ከከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና በለሙያዎች ጋር በመሆን የመስክ ምልከታውን አድርጓል።

ምልከታው የዞኑ ኢንዱስትሪ እና እንቨስት መንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረጀ ደመቀ ፣የከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ እና ስቪል ሰርቪስ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አደራጀው ዋኘው ፣ የብልፅግና ቅርጫፍ ፅ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አምባየ ፣የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀሃየ በላይ ጨምሮ የተለያዩ ባለሙያዎች በመስክ ምልከታው ተገኝተዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከተማውን በዘመናዊነት ለማልማት መጠነ ሰፊ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በከተማው በባለሀብቶች ተይዘው እየለሙ ያሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀግቶች የሚገኙ ሲሆን ለአብነት ያክል በአምራች ኢንዱስትሪ ፣በአገልግሎት ዘርፍ እዲሁም በከተማ ግብርና ዘርፈ ብዙ ልማቶች እየለሙ ይገኛል።

ባለሀብቶቹ ከከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ፅ/ቤት የተሰጣቸውን የማልሚያ ቦታ በከፍተኛ ሁኔታ እያለሙ የሚገኙ ሲሆን የመብራት እና መሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲስተካከልላቸው ጠይቀዋል።

የዞኑ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረጀ ደመቀ ባለ ሀብቶች ላነሱላቸው የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና የመብራት የአቅርቦት ችግር ከሚመለከታቸው የከተማው አሰተዳደር እና አመራሮች ጋር በመሆን ለመፍታት ጥረት እያደረጉ እንደሚገኝ አስተው በከተማው የማልሚያ ቦታ ወስደው ወደስራ ያልገቡ ባለ ሀብቶች ወደ ስራ መግባት እዳለባቸው አስተላልፈዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ዙሪያ  ከመምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።     ዳንሻ።፦ ግምቦት 09/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ...
17/05/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ዙሪያ ከመምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።

ዳንሻ።፦ ግምቦት 09/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ዙሪያ ከመምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል።

በውይይቱ የከተማ አሰተዳዳደሩ መምህር አብድልዋህብ ማሙ ፣የከተማው ም/ከ እና የሲቭል ሰርቪስ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አደራጀው ዋኘው ፣የትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ መምህር አምባቸው ንጉሱ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተካሄዷል

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከተማው አስተዳደር መምህር አብድልዋህብ ማሙ ሲሆኑ በመክፈቻ ንግግራቸው መምህራን በከተማችን ብሎም በሀገራችን ጉዳይ ግምባር መሪዎች እና የመፍትሄ አካል ናቸው ብለዋል።

አስተዳደሩ አያይዘው መምህራን ሀገርን በመገንባት ደረጃ ሚናቸው ከማንኛውም ማህበረሰብ ጋር ሊወዳደር ቀርቶ ለንፅፅር ሊቀርብ እንደማይገባ ገልፀው እየተዋጋነው ባለው ጠላት የድርሻቸውን ከመወጣት አኳያ ግምባር ቀደም ተሰላፊዎች መሆን እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመድረኩ የመወያያ ሰነድ በአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊው በአቶ ነጋ አምባየ የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ላይ አጠቃላይ የፅንፈኛው ሀይል የጥፋት አጀንዳ ቀርቧል ፤ሰነዱ ህውሀት ከተለያዩ የባዳ እና የባንዳ ሀይሎች የተለያዩ የጥፋት ስራወችን እየሰራች እንደምትገኝ ገልጿል።

አቅራቢው አያይዘው ከአካባቢያችን ጅኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እና ተፈላጊነት ተያይዞ ኮሪደሩን ለመቆጣጠር የጠላት ሀይል ከውጭ እንደ ግብፅ ፣ሱዳን ፣ሻቢያ ጋር በመሆን ከውስጥ በሚገኙ ለተላላኪ ባንዳዎች ስምሪት በመስጠት ዞናችን የሽብር ቀጠና ለማድረግ አቅደው እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።

ማህበረሰባችን የጠላትን ሀይል ማግዘፍም ሆነ አቅልሎ ማየት አስፈላጊ አለመሆኑን አስተው ክልላችንን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳው ያለ የነጠላ ትርክ መሆኑን ጠቅሰው የወል ትርክት በመገባት ከጠላት ሀይል አቅም በላይ በሆነ ደረጃ እራሳችን አዘጋጅተናል ለዚህ ደግሞ በቂ እና አስቻይ ሁኔታ አለ ብለዋል።

የውይይቱ አላማ ክልላችን ብሎም ዞናችን የተጋረጠበትን የህልውና አዳጋ ለመጋፈጥ መሆኑን የተናገሩት የት/ት ፅ/ቤት ኃላፊው መምህር አምባቸው ንጉሱ ሲሆኑ በዘመቻ በመሳተፍ እንዲሁም ለመካላከያ ሰራዊታችን ድጋፍ እና ደጀን በመሆን የተጋረጠብንን የህልውና አደጋ ለማስወገድ መምህራን የበኩሉን መወጣት እንዲችል መሆኑን አሰገንዝበዋል።

ዞናችን የክልሉ አገት መሆኑን የገለፁት የከተማ አስተዳደር ም/ ከንቲባ እና የሲቭል ሰርቪስ ኃላፊ አቶ አደራጀው ዋኘው ጠላት ቀጠናውን ተቆጣጥሮ የክልላችን አልፎም የሀገራችን ሰላም ማናጋት እና ሰላማዊ ምርጫ እንዳይካሄድ የሽብር ሴራ አላማው አድርጎ እየሰራ እንዳ አስተዋል

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት መምህራን በበኩላቸው ህውሀት ሀገራችን በቀይ ባህር እና በቀጠናው የነበረንን የሀይል የበላይነት አዛብተው የባህር በር አልባ እስከ ማድረግ ብሎም የተሰሚነት ሚናችንን አሳጥተውናል እያሳጡነም እንደሚገኙ አስተው ለተከዜ ዘብ የማንሆንበት ምንም አይነት ምክኒያት የለም ብለዋል።

መምህራን አያይዘው ጉዳዩ የመኖር እና ያለመኖር የህልውናችን እዲሁም የማንነታችን ጉዳይ መሆኑን ገልፀው ከተማ አሰተዳደሩ በሚሰጠው መመሪያ መሰረት በሎጀስቲክስ ከመደገፍ ግምባር እስከ መዝመት ዝግጁ መሆናቸውን አስተው ሀገራችን የጋራ እስከሆነች ድረስ በጋራ መስራት እና የጋራ ጠላትን መዋጋት አስፈላጊ መሆኑን አስተዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ዙሪያ በከተማዋ ከሚገኙ አሽከርካሪዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።ዳንሻ፦ግንቦት 07/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን...
15/05/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ዙሪያ በከተማዋ ከሚገኙ አሽከርካሪዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።

ዳንሻ፦ግንቦት 07/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በወቅታዊ የፀጥታ ዙሪያ ከአሽከርካሪዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ማሩ ሀገራችን ብሎም ዞናችን በአራቱም አቅጣጫ ከቦ ለመውረር ተዘጋጅቶ የመጣወብንን ጠላት ለመመከት እና ለመከላከል የአሽከርካሪዎች ሚና እጂግ የጎላ መሆኑን አስተው፤

በአሽከርካሪዎች ላይ ተግዳሮት እየሆነ ያለውን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ መጠነ ሰፊ ስራዎች እንደ ከተማ አሰተዳደር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።

ኃላፊው አክለው አገልግሎት የምሰጠውን አካል መለየትና የመረጃ ሰዉ መሆን ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን አያይዘው ገልፀዋል።

በከተማችን ህገወጥ የጦር መሳሪያ ይታያል ፣የሰዎች ዝውውርም እንደነበር ለተነሱላቸው የመድረክ ጥያቄዎች ጥያቄው እውነት መሆኑን ተቀብለው ከፀጥታ ሀይላችን ጋር ተቀናጅተን ስራ እየሰራን በመሆኑ፤

እርምጃ መውሰድ ችለናል በማለት ከተማችንን ፍፁም ሰላም ለማድረግ የሁላችንም እርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።

የመንገድ፣ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ቃኘው መኮንን በበኩላቸው የታገልነው እና እየታገልን ያለነው ህግ እንዲከብር ፤ስርዓት እንዲሰፍን ነው፤

በተለይ አሽከርካሪዎች ደግሞ የአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን፣ፀጉረ ልውውጦች በመለየት እና በመጠቆም ለፀጥታ አካላት ደጋፊ መሆን ይኖርብናል ብለዋል ።

የመድረክ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለሰላማችን ከተማ አስተዳደሩ በሚሰጠን መመሪያ መሰረት ተልዕኳችንን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አስተው፤

ተጀምሮ ያለው የነዳጅ እና ቤዚን አቅርቦት እንዲሁም ፍትሀዊ የሆነ ስርጭት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

መደራጀት ለስራችን ብሎም ለህልውናችን አስፈላጊ ነው ያሉት የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነጋ ደጀን በማህበር በመደራጀት ህገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርን በማስቀረት፤

እንደ ተቋም የነዳጅ እና ቢዚን እጥረት ለመቅረፍ እና ተደራሽ ለማድረግ መጠነ ሰፊ ስራዎችን እየሰራን ነው ብለዋል።

Address

ዳንሻ
Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dansha Town Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share