Dansha Town Communication affairs office

Dansha Town Communication affairs office በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን የፌስ ቡክ ገፅ

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በክረምት በጎ አድራጎት የሰበሰባቸውን የትምህርት ቁሳቁሶች አስረከበ::ዳንሻ፦ነሀሴ 21/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ...
27/08/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በክረምት በጎ አድራጎት የሰበሰባቸውን የትምህርት ቁሳቁሶች አስረከበ::

ዳንሻ፦ነሀሴ 21/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በክረምት በጎ አድራጎት የሰበሰባቸውን የትምህርት ቁሳቁሶች አስረከበ::

በማስረከቢያ መረሀ ግብሩ የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ እና የሲቭል ሰርቪስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደራጀው ዋኘው፣የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አምባቸው ንጉሱ፣የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አዜብ እያዩና የከተማው ካቢኔዎች የተገኙ ሲሆን፤

ከማበረሰቡ የተሰበሰቡ ከ239 ደርዘን በላይ ደብተር ፣39 ባኮ ስክርቢቶና 1 ደርዘን እርሳስ ለትምሀርት ጽ/ቤት አስረክበዋል ።

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ።
26/08/2026

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ።

ወ/ሮ አልጋነሽ ሙሉ ለዞኑ ሻምፖዮና ዳንሻ ከነማ ክለብ የማልያና የጫማ ድጋፍ አደረጉ።ዳንሻ ፦ነሀሴ 20/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ለዳንሻ ከተማ አስተዳደር...
26/08/2026

ወ/ሮ አልጋነሽ ሙሉ ለዞኑ ሻምፖዮና ዳንሻ ከነማ ክለብ የማልያና የጫማ ድጋፍ አደረጉ።

ዳንሻ ፦ነሀሴ 20/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ለዳንሻ ከተማ አስተዳደር ለዞኑ ሻምፕዮን የእግርኳስ ክለብ የስፖርት ትጥቅ ድጋፍ አድርገዋል።

ግለሰቧ ከሁለት ዓመት በፊት የኳስ ድጋፍ ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን የከተማዋን የስፖርት እንቅስቃሴ ለማሳደግ የከተማ አስተዳደሩ ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት የሚያደርገውን ብርቱ ትግል በማድነቅ የበኩላቸውን ለመወጣት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

ድጋፉን የስፖርት ዘርፍ ቡዴን መሪ አቶ አሸናፊ ደርብ ስፖርተኞቹ እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች በተገኙበት ያስረከቡ ሲሆን ተጫዋቾች በበኩላቸው ድጋፋ እጅግ እንዳስደሰታቸው እና ለተሻለ ጥረት እንደሚያነሳሳቸው በመግለፅ ከዚህ በበለጠ ጠንክረው በመስራት ከከተማ አስተዳደሩ አልፎ ዞኑንም ሀገርንም ለማስጠራት እንደሚፈልጉ በዕለቱ ተናግረዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተሻሻለውን የስትራቴጅክ ማስተር ፕላን አስመልክቶ ከማህበረሰቡ ጋር ተወያይቷል።ዳንሻ ፦ነሀሴ 20/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ...
26/08/2026

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተሻሻለውን የስትራቴጅክ ማስተር ፕላን አስመልክቶ ከማህበረሰቡ ጋር ተወያይቷል።

ዳንሻ ፦ነሀሴ 20/2018 ዓ/ም በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር በተሻሻለው የስትራቴጅክ ማስተር ፕላን ጥናቱ ለማህበረሰቡ በባለሙያዎች ቀርቦ ውይይትእና ማብራሪያ የተደረገበት ሲሆን ፤በውይይቱ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አብድልውሃብ ማሙ ፣የዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ መሀመድ ኑር ፣ የከተማ አስተዳደሩ ብልፅግና ፓርቲ አቶ ሀብታሙ ማሩ እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮችና ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ከተማዋ ለህብረተሰቡ ለኑሮ የሚመጥን ምቹ የሆነችና ለኗሪዎቿም ብቻ ሳይሆን ለእግዶች የቆይታ ጊዚያቸውን የማስረዘም ስራ እንደሚሰራ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አብድልውሃብ ማሙ በመክፈቻ ንግግራቸው አስገንዝበዋል።

ከንቲባው አክለውም አንድ ከተማ የህዝብን ጥያቄና ቁጥር ከግምት ውስጥ በማስገባትና የአገልግሎት አጠጥን ለማዘመን ሲባል ማስተር ፕላኑን ማሻሻል አስፈላጊ እንደሆነ አስተዋል።

የአንድን የከተማ እድገት የሚወስነው መሰረታዊ የሆነ የፕላን አሰራርና ዝርጋታ ሲኖራት እንዲሁም ደግሞ ፕላኑን እንደ ህገመንግስት የማየትና የማክበር ልማድ ማዳበር ሲቻል እና ለተፈጻሚነቱም የሁሉም አካላት እርብርብ ይጠይቃል ሲሉ የዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ መሀመድ ኑር ተናግረዋል።

ጥናቱን የክልሉ ፕላንና ኢንስትቱዩት ባለሙያ የሆኑት አቶ ምናላቸው ታየ እና የኢኮኖሚው ባለሙያ አቶ ምስጋናው ብርሀኑ በጋራ ለውይይት ተሳታፊዎች አቀርበዋል።

በጥናቱ መሰረት ከተማዋ ከ850- 630ሜ ከፍታ እንዳላትና የሙቀት መጠኗም ከ19-42 ዲግሪ ሴልሸስ እና በአማካኝም 28 ዲግሪ ሴልሸስ እንደሆነ በማንሳት የአፈር አይነትም 70% ያህሉ ጥቁር እንደሆነና ለዚህም ለምርታማነት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው በጥናቱ ተመላክቷል።

ከዚህ በፊት የተሰራው ፕላን የነበረበት ችግር የተነሳ ሲሆን ይህም የዋናው መንገድ ጥበትና ባለሙያው ሙያውን ተከትሎ ከመስራት ይልቅ የአመራርን ትዛዝ በማክበር መሰራቱና የተቋማት አለመጣጣም እንዲሁም የነፋስን አቅጣጫን ተከትሎ አለመሰራቱ እንደ መሰረታዊ ችግር ተነስቷል።

በፕላን አመቱ መጨረሻ የአገልግሎት ሰጭ ተቋማትን ለአብነት ያክል የጤና ፣የትምህርት መሰል ተቋማትን ቁጥራቸውን መጨመር እንደሚቻል በጥናቱ መፍትሄ እንደተቀመጠለት ተብራርቷል።

የህብረተሰብ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስትራቴጅክ ፕላኑ መሻሻሉ እንዳስደሰታቸው በማንሳት ተጨማሪ የአገልግሎት ተቋማት በማስተር ፕላኑ ተካተው መሄድ ይገባቸዋል ሲሉ ሀሳባቸውን ገልጸው በተጠናው ፕላን መሰረት ተፈጻሚነቱን በማረጋገጥ ደረጃ ከተማ አስተዳደሩ ህዝቡን ከጎኑ በማድረግ ወደ ስራ በመግባት የማህበረሰቡን የመኖሪያ ዕጦት መፍታት እንደሚገባ አስተዋል።

በተጨማሪም ሀቀኛ የሆነ ባለሙያ በማሰለፍ ለህብረተሰብ አገልግሎት በመትጋት እንደ መጠባበቂ የተያዘውን ቦታ ለታለመለት አገልግሎት ብቻ እንዲዉል ህገወጥ የቤት ግንባታን በማስቆም ለተሻለ ለውጥ የአመራሩ ቁርጠኝነት አስፈላጊ ነው ሲሉ አክለዋል።

በመጨረሻም ይህ የከተማ ስትራቴጅክ ማስተር ፕላን ማሻሻያው ወደተግባር ለመግባት ጌዜ በመስጠት መመሪያ መሰረት አድርጎ እና ከአካባቢው የጠገዴ ወረዳ አመራሮችና የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እንደሚደረግ ተመላክቷል።

‎በአማራ ክልል ፕላን ኢንስቲቱዩት ባለሙያዎች የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተሰራውን የስትራቴጅክ ፕላን በሰነድ ቀረበ።‎‎ዳንሻ ፦ነሀሴ 19/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃ...
25/08/2026

‎በአማራ ክልል ፕላን ኢንስቲቱዩት ባለሙያዎች የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተሰራውን የስትራቴጅክ ፕላን በሰነድ ቀረበ።

‎ዳንሻ ፦ነሀሴ 19/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር የክልሉ ፕላን ኢንስቲቱዩት ባለሙያዎች የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተሰራውን የእስትራቴጅክ ፕላን የከተማ አስተዳደሩ ም/ከንቲባ አቶ አደራጀው ዋኘው ፣የከተማ አስተዳደሩ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ማሩ እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮሮች በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

‎የስትራቴጅክ ፕላኑን አጥንተው ለውይይት ያቀረቡት የክልሉ የፕላን ኢንስቲቱዩት ባለሙያ የሆኑት አቶ ምናላቸው ታየ እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥናት ባለሙያ የሆኑት አቶ ምስጋናው ብርሀኑ በጋራ በመሆን ሲሆነ የከተማዋን ታሪካዊ አመሰራረት እና ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥንም መሰረት በማድረግ ጥናቱ ቀርቧል።

‎የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊ አመሰራረት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በጠገዴ ወረዳ የምትገኝ ከተማ ስትሆን በርሀማውንና ደጋማውን አካባቢ የምታገናኝና በደረቅ ወደብነት የምታገለግል ከተማ ናት።

‎ከተማ አስተዳደሩ በጠገዴ ወረዳ ስር የምትገኝና ከአዲስ አበባ 900 ኪሎ ሜትር ርቀት እንዲሁም ከክልሉ ርዕሰ መዲና ባህርዳር በ335 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደምትገኝ ጥናቱ ይገልፃል።

‎ከተማዋ አስካሁን የሁለት ጊዜ የፕላን ዘመን እንዳሳለፈች በማንሳት የመጀመሪያው ፕላን በ1995 ዓ/ም የተሰራ የእድገት ፕላንና ለሁለተኛ ጊዜ የተሰራው ደግሞ በ2005 ዓ/ም በ677.18 ሄክታር የእስትራክቸር ፕላን እንደተሰራላት ጥናቱ አመላክቷል።

‎አሁን ላይ ለ3ኛ ጊዜ የሚሰራው የስትራቴጅክ ፕላን 4710 ሄክታር ስፋት ያለውና 26,649 በላይ ህዝብ የያዘና በፕላን አመቱ መጨረሻ ከ40,506 የሚደርስ ህብረተሰብን ታሳቢ በማድረግ ፕላኑ መሰራቱን ገልጾ በተጨማሪም ስትራቴጅክ ፕላኑ ሲሰራ ተፈፃሚ የሚሆነው በሰፈር ልማት ፕላን እንደሆነ ግንዛቤ መያዝ ይኖርበታል ሲሉ አጥኝዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎አዲሱ የማስተር ፕላን ጥናት ተጠናቆ መሬት ላይ በሚወርድበት ወቅት ከተማዋን አዲስ ገፅታ ከማላበስ በተጨማሪ የአገልግሎት ሰጭ ተቋማትን በቁጥር እስከመጨመርና ጥራታቸውንም በዛው ለክ እንደሚያመጣ በባለሙያዎች ተብራርቷል።

‎ለጥናቱ አስቻይ ሁኔታ የሚነሳው የከተማዋም ሆነ የዙሪያው ወረዳዎች ከፍተኛ የሆነ የእንስሳትና የተፈጥሮ ሀብት፣ ሊታረስ የሚችል ሰፊ የእርሻ መሬት ፣ ሰፊ የሆነ የሰው ሀይል አቅምና መልካም የሆነ የስራ ባህሪ የተላበሰ ማህበረሰብ መኖሩ በተጨማሪም የዞኑ የግብርና ኢኮኖሚ እቅስቃሴ ማዕከል መሆኗ አስቻይ ሁኔታ እንደሚያደርገው ተገልፆል።

‎ተሳታፊዎቹ በበኩላቸው ማስተር ፕላኑ እንዳዲስ መሻሻሉ እንደመልካም ያኑሱ ሲሆን በመሻሻሉ ላይ የቦታዎች ስያሜ ወጥ የሆነና የፊደል ግድፈት ሳይኖራቸው እንዲሰሩና በተጨማሪም የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት እንደሆነም በማስተር ፕላኑ ላይ እንዴታወቅ ሲሉ ሀሳባቸውን አንስተዋል።






‎አቶ ጎፍንን ጫቅሌ በድጋሜ የ10 ሺ ብር ድጋፍ አደረጉ።‎‎ዳንሻ:-ነሀሴ18/2018 ዓ.ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር አቶ ጎፍ...
24/08/2026

‎አቶ ጎፍንን ጫቅሌ በድጋሜ የ10 ሺ ብር ድጋፍ አደረጉ።

‎ዳንሻ:-ነሀሴ18/2018 ዓ.ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር አቶ ጎፍንን ጫቅሌ በድጋሜ 10,000ብር ድጋፍ አድርገዋል።

‎ ባለፈው ሳምንት ከ30 ሺ ብር በላይ ወጭ በማድረግ 30 ደርዘን ደብተር ለተማሪዎች አገልግሎት የሚውል የበጎ አድራጎት ድጋፍ ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን አሁንም በድጋሜ 10,000 ብር ለተማሪዎች የቁሳቁስ ግብዓት የሚውል ለዳንሻ ከተማ አስተዳደር ት/ጽ/ቤት ድጋፋቸውን አስረክበዋል።

ስለሚያደርጉት የበጎ ተግባር ለሌሎች አርያ ይሆናሉና እናመሰግናለን ።

አቶ ጎፍንን ጫቅሌ የበጎ አድራጎት ስራው ለበጎ አላማ መሆኑን ተረድተው 30 ደርዘን ደብተር ድጋፍ አደረጉ።‎ዳንሻ ፦ነሀሴ 15/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ...
21/08/2026

አቶ ጎፍንን ጫቅሌ የበጎ አድራጎት ስራው ለበጎ አላማ መሆኑን ተረድተው 30 ደርዘን ደብተር ድጋፍ አደረጉ።

‎ዳንሻ ፦ነሀሴ 15/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር የበጎ አድራጎት ስራው በተለያዩ መስኮች የቀጠለ ሲሆነ፤

‎ለተማሪዎች ቁሳቁስ ማሰባሰብ በተደራጀ ሁኔታ እየተካሄደ የሚገኝና በተለየ ትኩረት ተሰጥቶት ከግለሰብ እስከ ተቋማት ድጋፍ እያደረጉም ይገኛል።

‎ትውልድ ላይ መስራት የዜግነት ግዴታየ ነው ሲሉ አቶ ጎፍንን ጫቅሌ እየተደረገ ባለው የበጎ አድራጎት ስራው የድርሻየን ልወጣ ሲሉ 30,600 ብር ወጭ በማድረግ 30 ደርዘን ደብተር ለከተማ አስተዳደሩ አስረክበዋል።

‎አቶ ጎፍንን ጫቅሌ በከተማ አስተዳደሩ ስም ስላደረጉት ድጋፍ እናመሰግናለን!!

ደስታ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም ለዳንሻ ከተማ አስተዳደር ለተማሪዎች አገልግሎት የሚሆን 20 ደርዘን ደብተር ድጋፍ አደረጉ። ዳንሻ ፦ነሀሴ 15/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መን...
21/08/2026

ደስታ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም ለዳንሻ ከተማ አስተዳደር ለተማሪዎች አገልግሎት የሚሆን 20 ደርዘን ደብተር ድጋፍ አደረጉ።

ዳንሻ ፦ነሀሴ 15/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዳንሻ ከተማ አስተዳደር ደስታ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋም እየተደረገ ባለው የክረምት የበጎ አድራጎት ተግባር ለተማሪዎች የሚዉል የ20 ደርዘን ደብተር ድጋፍ አደረጉ።

በዛሬው ዕለት በተወካያቸው በአቶ ሁሴን ሙሀመድ አማካኝ ድጋፉን ለአስተዳደር ያስረከቡ ሲሆን ከስራቸው ጎን ለጎን ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ሀገር የትውልድ ቅብብሎሽ ውጤት ናት መሰረቷም የምትጸናውም በትውልድ መሆኑን በመገንዘብ ስላደረጋቹሁት ድጋፍ ከተማ አስተዳደሩ ከልብ ያመሰግናቹሀል።

የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ በይፋ ዛሬ በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ት/ቤቶች ተጀምሯል።ዳንሻ ፦ነሀሴ 14/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ...
20/08/2026

የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ በይፋ ዛሬ በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ት/ቤቶች ተጀምሯል።
ዳንሻ ፦ነሀሴ 14/2018 ዓ/ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ በዛሬው ዕለት በሁሉም ት/ቤቶች በይፋ አስጀምሯል።

‎ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት መረጋገጥና አስተማማኝ ሰላም መምጣት የሚችለው የተማረ የሰው ሀይል ስናፈራ ብቻ ነው ክቡር አብድልውሃብ ማሙ።‎‎ዳንሻ  ነሀሴ 13/2018 ዓ/ም የዳንሻ ከተ...
19/08/2026

‎ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት መረጋገጥና አስተማማኝ ሰላም መምጣት የሚችለው የተማረ የሰው ሀይል ስናፈራ ብቻ ነው ክቡር አብድልውሃብ ማሙ።

‎ዳንሻ ነሀሴ 13/2018 ዓ/ም የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ት/ት ጽ/ቤት የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።

‎በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ትም/ት ጽ/ቤት የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ የንቅናቄ መድረክ አካሄዷል።

‎በመድረኩ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አብድልዉሃብ ማሙ ፣አቶ ጌታሁን ብርሃኔ የዞን የህብረት ስራ ማህበር መምሪያ ሀላፊ እና ደጋፊ አመራር ፣አቶ ቸሩ ሀጎስ ከዞን ትምህርት መምሪያ የኢንስፔክሽን ቡድን መሪ ፣የዳንሻ ከተማ ት/ት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አምባቸው ንጉሱ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና ባለ ድርሻ አካለት በተገኙበት የፓይለት ምዝገባው የንቅናቄ መድረኩ ተካሄዷል።

‎መድረኩን በንግግር መክፈቻ ያስጀመሩት የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አብድልውሃብ ማሙ ሲሆኑ እሳቸው እንዳሉት የፓይለት ምዝገባው በከተማ አስተዳደር ብቻ ሳይሆን እንደ ዞን የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የኔነት ስሜት በመውሰድ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ በማንሳት መልዕክት አስተላልፈው ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት መረጋገጥና አስተማማኝ ሰላም መስፈን የሚቻለው የተማረ ትውልድ ማፍራት ስንችል ነው ብለዋል።

‎ሁሉም በሚባል ደረጃ የሚመለከታቸው የት/ት ባለ ድርሻ አካላት በቅንጅት መሰራት መቻሉ የተሻለ እምርታ ማምጣት እንደተቻለ በዕለቱ በቀረበው ሰነድ የተገለፀ ሲሆን እንደ ሪፖርቱ ገለፃ ከሆነ የማህበረሰባችን የቆየ የኋላ ቀርነት አስተሳሰብ ባለመቀረፉ ለትምህርት የደረሱ ልጆችን በጊዜው ወደ ምዝገባ ቦታ አለመላክ እንደ ተግዳሮት ተነስቷል።

‎የፓይለት ምዝገባው ከነሀሴ 14 እስከ 16 በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ሁሉም ት/ቤቶች እንደሚሰጥ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት እርብርብ ማድረግ እንዳለበት በሰነዱ ተመላክቷል።

‎የፓይለት ምዝገባው የቀጣይ የትምህርት ወቅት ያለውን የስራ ጫና ከመቀነስና የትምህርት ፍሰቱን ዘላቂ በማድረግ አኳያ ትልቅ አስተዋጵኦ እንዳለው የከተማ አስተዳደሩ ት/ት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አምባቸው ንጉሱ አስገንዝበዋል።

‎አክለውም በተያዘው የትምህርት ዘመን የመረጃ ስርዓታችን በሁሉም ት/ት ቤቶች ወጥ በማድረግ ለትምህርት ውጤት መሻሻል በጋራ እንደሚሰሩ እና የመማሪያ ቦታወችን ምቹና ሳቢ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።

‎እንደ ዞን ከ213 ,000 በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እቅድ መያዙን የተገለፀ ሲሆን አንድም እድሜው ለትምህርት የደረሰ ህፃን ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆን እንደሌሌበት በማንሳት ልዩ ድጋፍ የሚሹ ህፃናትን የመማሪያ ድጋፍ መደረግ ይኖርበታል ሲሉ ከዞን ት/ት መምሪያ አስተባባሪ አቶ ቸሩ ሀጎስ ጠቁመዋል።

‎የህዝብ ግንኙነት ስራውን በከፍተኛ ደረጃ በማካሄድ የታቀደውን እቅድ ማሳካት የማይቻልበት መንገድ እንደለለ በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ተናግረዋል።

Address

ዳንሻ
Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dansha Town Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share