ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Gunchire
  • ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት

ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት በከተማችን የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች እናስተዋውቃለን!!

በነገው እለት በታላቅ ድምቀት የሚመረቀው የጉራጌ ዞን አስተዳደር ህንጻን አስመልክቶ የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ትዕይንቱን አሳይቷል።ጳጉሜ 2/2018 (ጉንችሬ ) ...
07/09/2026

በነገው እለት በታላቅ ድምቀት የሚመረቀው የጉራጌ ዞን አስተዳደር ህንጻን አስመልክቶ የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ትዕይንቱን አሳይቷል።

ጳጉሜ 2/2018 (ጉንችሬ )

የጉራጌ ዞን አስተዳደር B+G+9 ህንጻ በነገው እለት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ተጋዥ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይመረቃል።

በጉራጌ ዞን የተገነባው እጅግ ዘመናዊ የዞኑ አስተዳደር( B+ G+9) ህንጻ ነገ በታላቅ ድምቀት ለመመረቅ ዝግጅቱ ተጠናቋል።

ስለሆነም የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በመገኘት የሙዚቃ ትዕይንቱን በዛሬው እለት አሳይቷል።

የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን አስመልክቶ ወደ ወልቂጤ ከተማ የገባውን የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማና የዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በወልቂጤ ከተማ ተገኝተው በክብር ተቀብለዋል።

የማርሽ ባንዱ በከተማዋ ያሳየው የሙዚቃ ትዕይንትም ለነገው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት የበዓል ድባብን በማጠናከር የከተማዋን ድምቀት አሳድጎታል።

ይህ ትልቁ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ህንጻ በአጠቃላይ እስከ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የጨረሰ ሲሆን በዞኑ ይስተዋል የነበረው የቢሮ ጥበት ችግር በመቅረፍ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል።

በምረቃ ፕሮግራሙ የፌደራል፣የክልል የዞን የወረዳና የከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን።
የተንቢ
የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

‎ጳጉሜ 2 "ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በጉንችሬ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎች በመጎብኘት ተከበር።‎‎ጳጉሜ 2 /2018 ዓ.ም (ጉንችሬ)በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ...
07/09/2026

‎ጳጉሜ 2 "ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በጉንችሬ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎች በመጎብኘት ተከበር።

‎ጳጉሜ 2 /2018 ዓ.ም (ጉንችሬ)በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሰራዎች ማከናወን መቻሉ ተገልጿል።

‎የማንሰራራት ቀን ምክኒያት በማድረግ በከተማው እየተሰሩ ያሉ የኮሪደር ልማት፣ ለኮሪደሩ ንጣፍ የሚሆን የተዘጋጀውን የቴራዞ ምርት፣ የከተማው የቢሮ ህንጻ ግንባታ ፣የጉማያ ህንጻ እድሳት ፣የማዘጋጃ ቤት አግልግሎት አሰጣጥ በተመለከተና ሌሎችም የልማት ስራዎች ተጎብኝተዋል።

‎መንግስት ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ በርካታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እና ዝርጋታዎች በማከናወን የህብረተሰቡ የልማት ጥያቄ እየመለሰ መሆኑንም ተገልጿል ።

‎በመሆኑም ከተማውን ለማሳደግ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናቀቅ እና ሌሎችን ለመጀመር ማህበረሰቡ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠንክሮ መቀጠል እንዳለበት ተጠቁሟል ።

‎በጉብኝቱም የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ፣የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪ እና ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሴ ደሴ ፣የከተማው ም/ከንቲባና ስራ እድል ፈጠራ ና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘላለም ትግስቱ ጨምሮ ሌሎችም የከተማው አመራሮች እና የቀበሌ ዋና አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል።
#‎‎ዘገባው የከተማው መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው #

ጷጉሜ 2/2018( ጉንችሬ )ጷጉሜ 2 " ዘላቂ ልማት ለሀገር ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር  የተለያዩ  የመሰረተ ልማት ሥራዎች ምልከታ በማድረግ እየተከበረ ይገኛል...
07/09/2026

ጷጉሜ 2/2018( ጉንችሬ )
ጷጉሜ 2 " ዘላቂ ልማት ለሀገር ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ የመሰረተ ልማት ሥራዎች ምልከታ በማድረግ እየተከበረ ይገኛል።

ጳጉሜ 1፣2018(ጉንችሬ)በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀንን በማስመልከት በከተማችን የሚከናወኑ የግብርና የልማት ሥራዎችን ምልከታ ተደርጓል ዛሬ እንደ ሀገር ጳጉሜ 1 የእምር...
06/09/2026

ጳጉሜ 1፣2018(ጉንችሬ)
በጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀንን በማስመልከት በከተማችን የሚከናወኑ የግብርና የልማት ሥራዎችን ምልከታ ተደርጓል

ዛሬ እንደ ሀገር ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀን"እምርታ ለዘቂ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ነው የተከበረው።

ጳጉሜ ቀናት የተገኙ የልማት ውጤቶችን የሚታዩበት፣ ቀጣይ የልማት አቅጣጫዎችን የሚተለሙበትና ሕብረተሰቡን ለቀጣይ የልማት ጉዞ የሚያሰባስቡበት ወቅት ነው።

በዚህም የምግብ ዋስትናችንን ለማረጋገጥ የተሠሩ ስራዎች ፣ ኑሮን ለማረጋጋትና ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ ሥራዎች ምልከታ ተደርጓል

በሌማት ትሩፋት የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በምልከተው የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ኑጉሴ ደሴ የጨምሮ የከተማው የስራ ሀላፊዋችና ሌሎችም ተገኝተዋል

#የከተማው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው!

በጉራጌ ዞን ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀንን በማስመልከት የዞንና የወረዳ ሥራ ኃላፊዎች በቸሀ ወረዳ የሚከናወኑ የግብርና የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።ዛሬ እንደ ሀገር ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀን"...
06/09/2026

በጉራጌ ዞን ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀንን በማስመልከት የዞንና የወረዳ ሥራ ኃላፊዎች በቸሀ ወረዳ የሚከናወኑ የግብርና የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ይገኛሉ።

ዛሬ እንደ ሀገር ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀን"እምርታ ለዘቂ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል።

በመሆኑም በጉራጌ ዞን ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀንን በማስመልከት የዞንና የወረዳ ሥራ ኃላፊዎች በቸሀ ወረዳ የሚከናወኑ የግብርናና ሌሎች የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።

ጳጉሜ ቀናት የተገኙ የልማት ውጤቶችን የሚታዩበት፣ ቀጣይ የልማት አቅጣጫዎችን የሚተለሙበትና ሕብረተሰቡን ለቀጣይ የልማት ጉዞ የሚያሰባስቡበት ወቅት ነው።

በዚህም የአምራች ኢንዱስትሪ፣ የገጠር ኮሪደር ልማት፣ የግብርናና የማዕድን ሀብት ልማት፣ ኑሮን ለማረጋጋትና ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተከናወኑ ሥራዎች ምልከታ ይደረግባቸዋል።

በመስክ ምልከታው የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ፣የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን ፣የዞንና የቸሀ ወረዳ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

#የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ

‎የሳምንቱ አበይት ዜናዎች‎ ጷጉሜ 1/2018 ዓ.ም (ጉንችሬ)‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ እና የዞኑ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሱፐርቪዥን ቡድን በ...
06/09/2026

‎የሳምንቱ አበይት ዜናዎች
‎ ጷጉሜ 1/2018 ዓ.ም (ጉንችሬ)
‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ እና የዞኑ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሱፐርቪዥን ቡድን በጉንችሬ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ እና ህገ ወጥ የመሬት ወረራ ለመከላከል እየተሰራ ያለው ተግባር ተዟዙረው ምልከታ አደረጉ።

‎የጉንችሬ አከባቢ ቅድሚያ ማህበር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ለ 5 መቶ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉንና ደረጃውን የጠበቀ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዱን አስታወቀ።

‎የጉንችሬ ከተማ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ለ 2 መቶ 39 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ ተገለፀ።

‎እያደገ የመጣው የህዝባችን የልማት ጥያቄ አቅም በፈቀደ መጠን ምላሽ ለመስጠት ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ ይገባል፦ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ መደበኛ ውይይት አደረገ።

‎ወደ ውጭ ሀገራት ለስራ የሚሄዱ ዜጎች መንግስት ባመቻቸው በህጋዊ መንገድ ብቻ በመጓዝ የሚደረስባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የህይወት መስዋዕትነት መከላከል እንዳለባቸው ተገለፀ።

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ጉንችሬ ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና #233 ተማሪዎች ተፈትነዉ #32 ተማሪዎች ማሳለፉን የከተማው ትምርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሀቢብ ናስር ተናግረዋል
ከታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ያገኙ
‎📌በፌስቡክ
https://www.facebook.com/gunchireadiminstrationtowncity
‎📌በቴሌግራም
https://t.me/cummugovaffairsofficegunchire
‎ 📌 በቲውተር
https://x.com/gunchirecitygov
‎📌 በቲክቶክ
https://vm.tiktok.com/ZS91K4XwcWTuB-UQTZP/
‎📌 በኢንስታግራም
https://www.instagram.com/gunchire.comu?igsh=djhxMnBmNWw0dnFk
‎📌 በዩቲዩብ
https://youtube.com/-by6hf3wh5s?si=OebcCF92T8h4HVTI
‎ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

በዞኑ የሚገኙ ከተሞች በማሳደግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ አበረታች ስራዎች በቀጣይም ይበልጥ ማጠናከር ይገባል:- አቶ አበራ ወንድሙነሀሴ 30/2018ዓ.ም(ጉንችሬ) የጉራጌ...
05/09/2026

በዞኑ የሚገኙ ከተሞች በማሳደግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ አበረታች ስራዎች በቀጣይም ይበልጥ ማጠናከር ይገባል:- አቶ አበራ ወንድሙ

ነሀሴ 30/2018ዓ.ም(ጉንችሬ) የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ የ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ሴክቶሪያል ጉባኤ "አንድነት ለጽዳት፣ ትጋት ለአገልግሎት፣ ውሳኔ ለልማት" በሚል መሪ ቃል የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ እንዳሉት በዞኑ የሚገኙ ከተሞች ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ለዚህም በዞኑ ከተሞች በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን አንስተው፤ በቀጣይም የከተሞቹ እድገት በማረጋገጥ ማህብረሰቡን የሚመጥኑ ለማድረግ ህብረተሰቡን ይበልጥ በማሳተፍ መስራት ይገባል ብለዋል።

በከተሞች ለህብረተሰቡ የምሰጠውን የአገልግሎት በላቀ ደረጃ ማሳደግ እንደሚገባ ያነሱት አቶ አበራ ከዚህም ባለፈ ህገወጥ የመሬት ወረራና ግንባታ መከላከል ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ነው ያሉት።

ከተሞች ያላቸውን የመሬት ሀብት በተገቢው ማወቅና መምራት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ ከዚህም ባለፈ ከተሞቹ ይበልጥ ለማሳደግ ያላቸውን የገቢ አርዕስት በመለየት ገቢ መሰብሰብ ላይ በልዩ ትኩሩት መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ እንዳሉት ከተሞች ነጋቸውን ሳይስቱ በፕላን መሰረት እንዲያድጉ ከማድረግ ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹና ጽዱ እንዲሆኑ የቆሻሻ አወጋገድ ስርአት ማሻሻል ላይ በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።

በከተሞች እየተገነቡ ያሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እንዳለባቸውም አንስተዋል።

በዞኑ የሚገኙ ከተሞች በማሳደግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ አበረታች ስራዎች በቀጣይም ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትብለጥ እስጢፋኖስ በበኩላቸው በ2018 በጀት አመት በዞኑ የሚገኙ ከተሞች ከፍተኛ መነቃቃትና ተጨባጭ ዕድገት ማስመዝገባቸውን አመላክተዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ህብረተሰቡ በጥሬ ገንዘብ፣ በጉልበት፣ በቁሳቁስ ከ7 መቶ 22 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

በዚህም 70 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ግንባታና 149 ነጥብ 7 ኪሎሜትር ከፈታ ከማድረግ ባሻገር 62 ነጥብ 57 የመብራትና 77 ነጥብ 4 የውሃ መስመር ዝርጋታ ማከናወን መቻሉንም ተናግረዋል።

በዞኑ በ5ቱም ከተማ አስተዳደሮች 15 ነጥብ 34 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እየተገነባ መሆኑን ያነሱት ወይዘሮ ትብለጥ በዚህም በእስካሁኑ 7 ነጥብ 6 ኪሎሜትር ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

ይህም ከተሞች ለስራና ለመኖሪያ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ ውበታቸው እንዲገለጥ እንዳደረገም አንስተው፤ ከዚህም ባለፈ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ በጥራትና በስፋት እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

በሁለተኛ ዙር የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ኢንሼቲቭ 28 ፕሮጀክቶች በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ ተችላል ነው ያሉት።

የህብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍና ተገልጋዮችን በፍትሃዊነት ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ማዘመን ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች እንዳሉት በዞኑ የህብረተሰብ ተሳትፎ በማጠናከር ከተሞች ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን አንስተው ይህ በቀጣይም ሊጠናከር ይገባል።

ከተሞች ይበልጥ ለማሳደግ በፕላን መምራት፣ ህገወጥነትን መከላከልና የገቢ አርዕስቶችን አሟጦ መሰብሰብ ላይ በትኩሩት እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

በመጨረሻም የመምሪያው ኃላፊ ከታችኛው መዋቅር ጋር የ2019 በጀት አመት የግብ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን በ2018 በጀት አመት የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ 1ኛ,ጉመር፣ 2ኛ, እዣና 3ኛ, አበሽጌ ወረዳዎች ሲሆኑ ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት 1ኛ, እምድብር፣ 2ኛ, ጉንችሬና 3ኛ,አገና በመሆን እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

እንዲሁም ከወረዳዎች የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳና ከከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል።
የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

ነሃሴ 30፣2018(ጉንችሬ)የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ የ2018 በጀት አመት የሴክተራል ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ አካሂደዋል በዚህም የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ...
05/09/2026

ነሃሴ 30፣2018(ጉንችሬ)
የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ የ2018 በጀት አመት የሴክተራል ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ አካሂደዋል

በዚህም የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ከዞኑ ካሉ ከተሞች በ2018 በጀት አመት በተግባር አፈፃፀም 2ኛ በመውጣት ዋንጫና ሰርተፍኬት ተሸልመዋል።

/አለን

ለህዝባችን ተጠቃሚነትና ውጤታማነት ዘወትር ተግተን እሰራለን!

‎የጉንችሬ አከባቢ ቅድሚያ ማህበር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ለ 5 መቶ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉንና ደረጃውን የጠበቀ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዱን አስታወቀ።‎‎...
04/09/2026

‎የጉንችሬ አከባቢ ቅድሚያ ማህበር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ለ 5 መቶ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉንና ደረጃውን የጠበቀ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ለመገንባት ማቀዱን አስታወቀ።

‎ነሃሴ 29 ፣ 2018 ዓ.ም (ጉንችሬ) ማህበሩ 6 መቶ 50 ሺህ ብር ወጪ በማድረግ በጉንችሬ እና በእኖር ወረዳ ለሚገኙ ለ 5 መቶ ተማሪዎች ደብተርና እስክሪብቶ ድጋፍ አድርጓል።

‎የቅድሚያ ማህበር የጉንችሬ አከባቢ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዝምበላቸው ክፈተው እንደገለጹት በህጻናት በሁለንተናዊ እድገትና እና ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ለመረዳት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ከነዚህም መካከል 5 ህፃናቶች በሀገር ውስጥ ጉዲፈቻ ዘላቂ ወላጅ እንዲያገኙ መደረጉ ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ተጥለው የተገኙ 8 ህፃናቶች ወደ ማቆያ ማዕከል በማስገባት ሁለንተናዊ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑ እና ለ40 ተጋላጭ ቤተሰቦች የማአጤመ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ክፍያ መፈጸሙን ገልጸዋል።

‎የኢኮኖሚ አቅም እጥረት ላለባቸው 85 ወላጅ እናቶች በንግድ ወጤታማነት ዙሪያ ስልጠና እንደተሰጠና ከነዚህም ለ51 እናቶች በተለያየ የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው አቶ ዝምበላቸው ከፈተው ተናግረዋል።

‎በርካታ ህጻናትን በማህበረሰብ አቀፍ የድጋፍ ፕሮግራም ተጠቃሚ በማድረግ፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በማህበራዊና በስነ ልቦና ግንባታ እና የህጻናት ወላጆች የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ብለዋል።

‎ለ2019 የትምህርት ዘመን 6 መቶ 50 ሺህ ብር ወጪ በማድረግ በጉንችሬ እና በእኖር ወረዳ ለሚገኙ
‎ለ 5 መቶ ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው አንድ ደርዘን ደብተርና 12 እስክሪብቶ መሰጠቱን ገልጸዋል።

‎ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ ለማድረግ በአጽንኦት እየተሰራ መሆኑንና በቀጣይ በመስከረም ወር ደረጃውን የጠበቀ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ይቀመጣል ብለዋል።
‎‎ዘገባው የከተማው መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ ነሀሴ29/201...
04/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ

ነሀሴ29/2018(ጉንችሬ )

ዘላቂ የትምህርት ጥራት ለላቀ የመማር ውጤት እና ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በኤግዚቢሽኑ ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎች ቀርበው ለእይታ ክፍት የተደረጉ ሲሆን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በ2018 በጀት አመት ያከናወናቸውን ስራዎች የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ ርዕይ ቀርቧል።
የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን

Address

Gunchire

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share