Harari Finance & Economic Cooperation Bureau

Harari Finance & Economic Cooperation Bureau Government organization

የዘላቂ ልማት ግቦች (SDGs) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ::ነሐሴ 8/2018*         *        *            *በሐረሪ ...
14/08/2026

የዘላቂ ልማት ግቦች (SDGs) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ::

ነሐሴ 8/2018
* * * *

በሐረሪ ሕዝብ ክልላዊ መንግሥት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አዘጋጅነት፣ የግብርና ቢሮ፣ የውሃ ፍሳሽ አገልግሎት ባለሥልጣን፣ የኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ እና የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የዘርፍ አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት የዘላቂ ልማት ግቦች (SDGs) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ቅድመ ዕቅድ ውይይት መድረክ ተካሄዷል።

ውይይቱን በንግግር የጀመሩት የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ያህያ አብዱራሂም መድረኩ ያለፈውን ዓመት ጥንካሬዎችና ድክመቶች ለመገምገም እና የቀጣይ ዓመት ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ ያለውን ወሳኝነት ገልጸዋል። የልማት ግቦቹን መሬት ላይ በማውረድ የህዝብን ኑሮ ማሻሻልና የሀገሪቱን የዕድገት ጉዞ ማቀላጠፍ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አንስተው ባለፈው ዓመት በተለያዩ ዘርፎች በርካታ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል። አክለውም አሁን የታዩ ስኬቶችን አጠናክሮ ክፍተቶችን የማረሚያ ወሳኝ ጊዜ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በመድረኩ ባለድርሻ ተቋማት በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቶች እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ አቅርበዋል። በሪፖርቶቹ እናእቅዶች ላይም ተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት በማድረግ በጥልቀት ገምግመዋል።

በውይይቱ ወቅት በዋናነት በጀትን ለታለመለት ዓላማ ብቻ ማዋል፣ የፋይናንስ ደንቦችን በጥብቅ መከተል፣ የግዥ ሥርዓትን በጊዜ ማጠናቀቅ እና የኦዲት ግኝቶችን በመቀነስ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ተሰጥቷል። በተጨማሪም የወርሃዊ እና የሩብ ዓመት ሪፖርት አቅርቦትን ተቋማዊ ማድረግ እንዲሁም የመስክ ጉብኝት ፕሮግራሞችን በጊዜ ሰሌዳ መሠረት ማከናወን ይገባል ተብሏል።

በሌላ በኩል በ2018 በጀት ዓመት ለተለዩ ድክመቶች የማሻሻያ እርምጃዎችን በ2019 ዓመታዊ ዕቅድ ውስጥ ማካተት፣ ለፕሮጀክቶች ቅድመ ዝግጅት ማሳወቅ፣ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት መሠራቱን ማረጋገጥ እና የፕሮጀክት መለያ ታፔላዎችን ማዘጋጀት እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል። ከዚህም በላይ በየዘርፉ ለስንት ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር በዕቅዱ ላይ በግልጽ መገለጽ እንዳለበት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ መድረኩ መሠረታዊ የአፈጻጸም ጉዳዮችን በዝርዝር ዳስሶ የጋራ መግባባት ላይ መድረሱን ጠቅሰው የተሳታፊዎች ውይይት ፍሬያማና ገንቢ እንደነበር ገልጸዋል። ውይይቱ ለቀጣዩ በጀት ዓመት ሥራዎች ጠንካራ መነሻ እንደሚፈጥር ሙሉ እምነት እንዳላቸው በመግለጽ መድረኩን አጠናቀዋል።

www.hararibof.gov.et
[email protected]
F.b.www.facebook.com/HBoFED
TikTok.https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ::ነሐሴ 7/2018*     *     *        * የሐረሪ ክልል ገንዘብና...
13/08/2026

የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ::

ነሐሴ 7/2018
* * * *

የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸምን የሥራ ግምገማ መድረክ ከአብይ ኮሚቴ አባላት ጋር አካሄደ።

የስብሰባውን መድረክ በይፋ የከፈቱት የቢሮው ኃላፊ እና የአብይ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መሐመድ ያህያ እንደገለጹት የፋይናንስ ሴክተር ሪፎርም በመንግስት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ፖሊሲዎች መሠረት ተቋማዊ አቅምን ለማጠናከር፣ የፋይናንስ አስተዳደርን ለማዘመን፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማሳደግ እንዲሁም ውጤታማ የፋይናንስ ሥርዓት ለመገንባት የተጀመረ ወሳኝ የለውጥ ፕሮግራም ነው።

የቢሮው ኃላፊ አያይዘውም ይህ የሪፎርም ትግበራ የክልላችንን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል እና የመንግስትን ሀብት በብቃት ለመጠቀም ወሳኝ ሚና አለው። በተለይም አሠራራችንን በዲጂታላይዜሽን ማስደገፋችን ለዘመናዊ የፋይናንስ አስተዳደር ግንባታ የላቀ ፋይዳ ይፈጥራል ሲሉ አስገንዝበዋል።

በመቀጠልም በቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ በአቶ ኑረዲን መሐመድ አማካይነት በዝግጅት ምዕራፉ እስካሁን የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና የቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫን ያካተተ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የአብይ ኮሚቴ አባላት በበኩላቸው የተዘጋጁ ሰነዶች በፍጥነት እንዲጸድቁ፣ የሚወጡ የሕግና የመመሪያ ማሻሻያዎች ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስፈላጊው ግብዓት ተሰብስቦ ሥራው እንዲጠናቀቅ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ያህያ አብዱራሂም በዝግጅት ምዕራፉ የተከናወኑ ሰነዶችና የቅድመ ዝግጅት እንቅስቃሴዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል።የሪፎርም ሥራው በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅም የክትትልና ድጋፍ ሥራው እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።አያይዘውም በቀጣይ የዳይሬክቶሬቶች ቅንጅት የበለጠ ተጠናክሮ የተጀመሩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ወደ ሙሉ ትግበራ ለመሸጋገር መስርት መጣል እንዳለባቸው አፅኖት ስጥቶዋል።

በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የቢሮው ኃላፊ አቶ መሐመድ ያህያ በሰጡት የመዝጊያ ንግግር የቴክኒክ ኮሚቴው ያቀረበውን አጠቃላይ አፈጻጸምና በውይይቱ የተነሱ ገንቢ አስተያየቶችን አድንቀዋል።

በመጨረሻም ቢሮ ኃላፊው ይህ የሪፎርም ሂደት ለክልላችን ፋይናንስ ዘላቂነት፣ ለሀብት አጠቃቀም ውጤታማነት እና ለዘመናዊ የአስተዳደር ሥርዓት ግንባታ የላቀ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ የቢሮው አመራሮችና የሪፎርም አፈጻጸም ኮሚቴዎች የሪፎርሙን ዓላማዎች ከግብ ለማድረስ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቁ ሁሉም አካል በኃላፊነት ስሜት መስራት አለበት" ሲሉ ጥሪያቸውን በማቅረብ የመድረኩን ፍጻሜ አብስረዋል።

www.hararibof.gov.et
[email protected]
F.b.www.facebook.com/HBoFED
TikTok:-http://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ ክልል ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለአቅመ-ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ::ነሐሴ 6/2018  *       *          *              *በሀረሪ ክ...
12/08/2026

የሀረሪ ክልል ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለአቅመ-ደካማ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ::

ነሐሴ 6/2018

* * * *

በሀረሪ ክልል በየዓመቱ የሚካሄደው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰባችንን በርካታ ችግሮች እያቃለለ ይገኛል።

የዚህ በጎ ተግባር አካል የሆነው የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለአዲሱ የትምህርት ዘመን የሚሆኑ የትምህርት ቁሳቁሶችን በማዘጋጀት ለሀረሪ ክልል ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ቢሮ ማስረከቡን አስታውቋል።

በዕለቱ ከተደረጉት ድጋፎች መካከል 200 ደርዘን ደብተር እና 1,000 ፍሬ እስክሪብቶዎች ይገኙበታል እነዚህ ቁሳቁሶች በአቅም ማነስ ምክንያት ለልጆቻቸው ደብተርና እስክሪብቶ ማሟላት ለሚቸገሩ ወላጆች ትልቅ እፎይታ የሚፈጥር ነው።

በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዲያቋርጡ አለመፍቀድ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።

እንዲህ ዓይነቶቹ ድጋፎች ልጆች ያለ ስጋት እንዲማሩ ከማድረጋቸውም በላይ በትምህርታቸው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችላቸውን ተስፋና ጥንካሬ እንደሚሰጣቸው በስነ-ስርዓቱ ወቅት ተገልጿል።

በመጨረሻም አንድም ልጅ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ቤት እንዳይቀር በሚለው መርህ መሰረት የመንግስት፣ የባለሀብቱና የህብረተሰቡ ቅንጅት አስፈላጊ መሆኑ ተስመሮበታል።

በመሆኑም መሰል የወገን አለኝታነትን የሚያሳይ የበጎ አድራጎት ስራዎች በቀጣይም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ቢሮው ጥሪውን አስተላልፏል።

www.hararibof.gov.et
[email protected]
F.b.www.facebook.com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

12/08/2026

ደም በመለገሳችንና ህይወት በመታደጋችን ታላቅ ደስታ ይሰማናል" — የቢሮ የበጎ ፍቃድ ደም ለጋሾች

በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር ታቅፎ በተካሄደው የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ላይ የተሳተፉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በጎ ፍቃደኞች ደም በመለገሳቸውና የሰዎችን ህይወት በመታደጋቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገለጹ።

በልገሳው ላይ የተሳተፉት የቢሮ ሰራተኞች እንደተናገሩት ደም መስጠት ለሌላው ህይወት ከማዳኑ ባሻገር ለሰጪው አካልና ጤናም ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ገልጸዋል።

ለአራተኛ ጊዜ ደም የለገሱት በጎ ፍቃደኛ እንዳሉት በክረምት ወቅት በልዩ ልዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ማለትም በጽዳት እና በደም ልገሳ ላይ በንቃት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

"በተለይም በወሊድ ምክንያት በደም እጥረት ለሚሞቱ እናቶች፣ በአደጋና በግጭት ከፍተኛ የደም መፍሰስ ለገጠማቸው ወገኖቻችን ህይወት ለመታደግ በማሰብ ነው ደም የለገስነው" ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላኛዋ ደም ለጋሽ በበኩላቸው፣ የደም ልገሳን ዘወትር እንደሚያከናውኑና በተለይም በወሊድ ወቅት የሚከሰተውን የደም እጥረት ችግር በቅርበት እንደሚያውቁት ተናግረዋል።

"ደሜ ለአንድ ህይወት መዳን ምክንያት በመሆኑ ትልቅ ደስታ ይሰማኛል፤ የክረምት ወቅት በመጣ ቁጥር ሁልጊዜም ደሜን እለግሳለሁ" ብለዋል።
ለጋሾቹ አክለውም ደም መስጠት አሮጌ ውን በማስወገድ በአዲስ ደም ሴሎች እንዲተኩ እንደሚያደርግና የሰውነት ንቃትን (ኤነርጂን) እንደሚጨምር በመግለጽ ህብረተሰቡ ስለ ደም ልገሳ ያለው ፍርሃትና የተሳሳቱ አመለካከቶች ተወግደው ሁሉም በግንባር ቀደምትነት ደም በመለገስ የዜግነትና የሰብአዊነት ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም በጎ ፍቃደኞቹ በአካባቢ ጽዳት፣ በችግኝ ተከላ፣ በደም ልገሳ፣ በማዕድ ማጋራት ፣በትምህርት ቁሳቁሶች እና ለአቅመ-ደካሞች አዲስ ቤት በመገንባትና በማደስ በኩል ሰፊ የበጎ አደራጎት ስራዎችን በቢሮ በኩል እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

ምንለግሰው አነስተኛ ደም ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ይታደጋል!ነሐሴ 5/2018*              *                    *                *    የገንዘብና ኢ...
11/08/2026

ምንለግሰው አነስተኛ ደም ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ይታደጋል!

ነሐሴ 5/2018

* * * *

የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች የክረምት በጎ አድራጎት አካል የሆነውን የደም ልገሳ መርሃ-ግብር አካሄዱ።

የቢሮው አባላት «ከስጦታዎች ሁሉ የላቀውን ደም በቋሚነት በየሦስት ወሩ መለገስ፣ በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰትን የእናቶችና የዜጎችን ሞት ይከላከላል» በሚል እምነት ነው ደሙን የለገሱት። በተለይም በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ህይወታቸው ለአደጋ የሚጋለጡ ወገኖችን ለመታደግ ደም መለገስ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለውም ደም መለገስ ለለጋሹ ምንም ዓይነት የጤና ችግር የማያሳይና ይልቁንም በርካታ የጤና ጥቅሞች ያሉት በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት በቋሚነት ደም በመለገስ የወገኖቹን ህይወት እንዲታደግ ጥሪ አቅርበዋል።

www.hararibof.gov.et
E-mail:[email protected]
Facebook:-www.facebook.com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

ዘመናዊ ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓት (DPMS Software System) የባለሞያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተከናወነ::ከሀምሌ 29- ነሀሴ2 /2018 ዓ.ምበገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ...
08/08/2026

ዘመናዊ ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓት (DPMS Software System) የባለሞያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተከናወነ::

ከሀምሌ 29- ነሀሴ2 /2018 ዓ.ም

በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ለአራት ቀናት ከክልሉ ለተውጣጡ 16 ተቋማት ለግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ኃላፊ እና ለንበብረት እና IT ባለሙያዎች ተግባር ተኮር DPMS ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓት ተግባር ተኮር ላይ ስልጠና ተሰጠ::

የስልጠናው ዋንኛ ዓላማ ዘመናዊ የንብረት አስተዳደር DPMS በተመረጡ 16 ቢሮዎች ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የመጀመሪያ ተግባር ተኮር ስልጠና ስሆን::

ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ለመንግስት ንብረት አስተዳደር በዚህ ልክ ትኩረት መሰጠቱ እጅግ እንዳስደሰታቸው ለአሰራር አመቺ እና ግልጽ በመሆኑ በቀላሉ ወደ ትግበራ ምእራፍ መሻገር የሚያስችል መሆኑ በተጨማሪ ሲፈልጉት የነበረ ምርጥ ሶፍትዌር ሲስተም ላይ እውቀት እንዳገኙ የገለፁ ሲሆን ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ ይህን ሲስተም መዘረጋቱ መመሰገን እንዳለበት ገልጾ::

ስልጠና ማዘጋጀቱ የሚታየውን የአሰራር ክፍተት ለማጥበብ የሚያግዝ በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሻሽል አንስተው ሲስተሙን ለመልመድ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ቀጣይነት ቢኖራቸው የባለሞያውን የመስራት አቅም እና የአሰራር ክፍተትን የሚያጠብ መሆኑንን ተናግረዋል።

www.hararibof.gov.et
E-mail:[email protected]
Facebook:-www.facebook.com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የዘመናዊ ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓት (PMS Software System) ይፋዊ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ::ሐምሌ 28/2018*         *               *         ...
04/08/2026

የዘመናዊ ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓት (PMS Software System) ይፋዊ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ::

ሐምሌ 28/2018

* * * *

የመንግሥትን የንብረት አስተዳደር ሥርዓት ለማዘመንና አሰራሩን ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ የዘመናዊ ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓት (PMS Software System) ይፋዊ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ ያህያ የክልሉ መንግሥት በንብረት አስተዳደር ሂደት ላይ የሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችንና መንስኤዎቻቸውን በዝርዝር በመለየት፣ ዘመናዊና ቀልጣፋ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል አዲስ ምዕራፍ መጀመሩን ገልጸዋል።

ቢሮ ኃላፊው አክለውም በአሁኑ ወቅት ዲጂታላይዜሽን ለመንግሥት ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸው አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ የሁሉም የመንግሥት ንብረቶች መረጃ በአንድ ማዕከላዊ ዲጂታል መዝገብ (Database) ስር እንዲካተት ማድረግ ዋነኛ ዓላማ መሆኑን አብራርተዋል።

ቢሮ ሀላፊው አጠቃለው ሲናገሩ ሁላችንም የተሰጠንን ኃላፊነት በጥራት በመወጣት እና አስፈላጊውን ቅድመ-ዝግጅት በማጠናቀቅ የዚህ ዘመናዊ ሥርዓት ስኬታማ ትግበራ አካል እንድንሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ በማለት ሥርዓቱን በይፋ አስጀምረዋል።

በመድረኩ ላይ ስለ ዘመናዊ ዲጂታል የንብረት አስተዳደር ሥርዓቱ (PMS) በባለሙያዎች ዝርዝር የቴክኒክ ገለጻ የቀረበ ሲሆን፣ በተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም በሚመለከታቸው ባለሙያዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ያህያ አብዱረሒም በሰጡት ሐሳብ፣ የተለዩት መሥሪያ ቤቶችም ሆኑ ሌሎች አጋር አካላት ወደ ዲጂታል አሰራር ለመግባት የሚያስፈልገውን ቅድመ-ዝግጅት በፍጥነት እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

በተጨማሪም የመንግሥት ሀብትን በአግባቡ ለማስተዳደር ለሚደረገው ጥረት የሴክተር መሥሪያ ቤት እና የወረዳ መስተዳድር ኃላፊዎች በባለቤትነት ስሜት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ምክትል ቢሮ ኃላፊው ተሳታፊዎች ላሳዩት ንቁ ተሳትፎ እና ላነሷቸው ጠቃሚ ሐሳቦች ምስጋና አቅርበው፣ በቀጣይም ተከታታይነት ያለው ስልጠና እንደሚሰጥ በመግለጽ የመድረኩን ፍጻሜ አብስረዋል።

በዚህ የይፋዊ ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የሴክተር መሥሪያ ቤቶች፣ የወረዳ መስተዳድሮች እና በየደረጃው የሚገኙ የስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረሪ  ክልል  የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ  የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር አካሄደ::ሐምሌ 27/2018*            *            *      *በሀረሪ ክል...
03/08/2026

የሀረሪ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር አካሄደ::

ሐምሌ 27/2018

* * * *

በሀረሪ ክልል በአንድ ጀምበር የ800 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃግብር ተካሄደ የሀረሪ ክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞችም በመርሀግብሩ ላይ በመሳተፍ የችግኝ ተከላ አካሄዱ።

በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት የተቋሙ ኃላፊ አቶ መሀመድ ያህያ ችግኝን ተክሎ መሄድ ብቻ ሰይሆን እንደ ከዚህ በፊቱ የተተከለውን ችግኝ ታንከባክቦ ቦታ እስከደርስ ድረስ መከታተል እንዲሁም የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመያዝ እንክብካቤ መደረግ እንዳለበት ገለጹ::

በማስቀጠልም ይህ እየተደረገ ያለው የችግኝ ተከላ ብዙ ጥቅም የለዉ ሲሆን ንፁህ አየር ለመውሰድ የተለየዩ ስራዎች በትኩረት ለመስራት የአካባቢ ጽዳትን ለመጠበቅም ትልቅ ፋይዳ የለው ነው በለዋል::

በመጨረሻም በተቋመችን የተተከሉ ችግኞች የጽድቀትን መጠን ከፍ ለማድረግ ሁሉም የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች የመንከባከብ ስራ በተጠናከረ መልኩ እንደሚከናወን አመላክተዋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሀረር ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ  ዘመናዊ ዲጂታል የመንግስት ንብረት አስተዳደርን PMS customization ስራ ገመገመ።ሐምሌ 22/2018*               *       ...
29/07/2026

የሀረር ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ዘመናዊ ዲጂታል የመንግስት ንብረት አስተዳደርን PMS customization ስራ ገመገመ።

ሐምሌ 22/2018

* * * *

የሀረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ በመንግስት ተቋማት የሚገኙ ንብረቶችን በዘመናዊ የዲጂታል ስርዓት ለመምራትና ለማስተዳደር የሚያስችል የሶፍትዌር ለማስለማት ከአፍሮኔክስ ቴክ ሀብ (Afronex Tech Hub) ጋር በትብብር ለመስራት የስራ ስምምነት ማከናወኑ ይታወቃል።

ሶፍትዌሩን ከክልሉ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር የማስማማት (Customization) ስራዎች በውሉ መሰረት በጥራትና እና በፍጥነት የተከናወነ ሲሆን ወደትግበራ ምእራፍ ለመሸጋገር ዝግጁ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል።

የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ ያህያ እንደገለጹት ይህ ስራ በጥራትና በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት በማከናወን የዲጂታል አሰራሩ በመተግበር የክልሉን የንብረት አያያዝ ወደ ላቀ ዘመናዊነት የሚያሸጋግርና ግልጽነትን የሚፈጥርና የመንግስት ሀብትን ከብክነት ይጠብቃል ብለዋል።

ኃላፊው አክለውም ሲስተሙን ለመተግበር የተመረጡ ተቋማትን በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንዲሁም በስልጠና የማብቃት ስራ በአፋጣኝ ተጠናቀው፣ በተመረጡት ተቋማት ውስጥ ስርዓቱ በመዘርጋት ወደ ስራ እንዲገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሶስተኛ ዙር የአካባቢ ፅዳት ዘመቻ አካሄደ::ሐምሌ 18/2018*         *          *        *የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብ...
25/07/2026

የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሶስተኛ ዙር የአካባቢ ፅዳት ዘመቻ አካሄደ::

ሐምሌ 18/2018

* * * *

የሐረሪ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የዜንድሮ 2019 የክረምት በጎ ፊቃድ አገልግሎት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ::

‎የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መረሃ ግብር የአካባቢ ፅዳት ዘመቻ ስራ አካሄዱ።


‎ይህ ዘመቻ አካባቢን ፅዱ ከማድረግ ባለፈ ማህበረሰባዊ እሴቶችን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል።


Website:- www.hararibofed.gov.et
E-mail:- [email protected]
Facebook:- www.facebook,com/HBoFED
TikTok:- https://www.tiktok.com/.bofec
T.me:- https://t.me/HBoFEC

Address

Jinella
Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Finance & Economic Cooperation Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Harari Finance & Economic Cooperation Bureau:

Shortcuts

Share