04/06/2026
በኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ላይ ለኮሚሽኑ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
ግንቦት 27/9/2018
ሀረር
የሀረሪ ክልል የስነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
ስልጠናው ከሀረሪ ክልል ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ተሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ ኤች አይ ቪ የሚተላለፍባቸው መንገዶች፣ የመከላከያ ዘዴዎች፣ የቅድመ ምርመራ አስፈላጊነት እና አለም አቀፍ፣ ሀገር አቀፍና እንደ ድሬደዋ የስርጭት መጠን እና ይበልጥ ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ስልጠናውን ከሀረሪ ክልል ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት የኤች.አይ.ቪ ኤድስ መከላከል ይበልት ተጋላጭ አስተባባሪ ባለሞያ ወ/ሪት ምህረት ገ/ወልድ የሠጡ ሲሆን የመንግስት ሰራተኞች በስራ ቦታቸው እና በማህበረሰቡ ውስጥ ትክክለኛ መረጃን በማስተላለፍ በበሽታው መከላከል ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።
በኮሚሽኑም የሴቶች:ህፃናት ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ነጀሓ አህመድም ሰራተኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት በስራ ቦታቸውና በማህበረሰብ ውስጥ በማጋራት
የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።