02/06/2026
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጡ ሂደት በሰላም መጠናቀቁን በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የምርጫ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል።
የምርጫ ኮማንድ ፖስቱ የድምፅ መስጫ ሂደቱ እስከ ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ሲከናወን መቆየቱን በሶስቱም ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሠላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የምርጫ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል።
ድምጽ የመስጠት ስርዓቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ መራጩ ህዝብ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ዕጩዎች እና ታዛቢዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ እና ኃላፊነታቸውን በተገቢው ለተወጡ መላው የጸጥታ አካላት ኮማንድ ፖስቱ ምስጋናውን አቅርቧል።
ድምጽ ቆጠራው በአንዳንድ ጣቢያዎች እየተካሄደ ነው።
ድህረ ምርጫ ያለው ሂደት በተመሳሳይ በስኬት እንዲከናወን ባለ ድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የምርጫ ኮማንድ ፖስት ጥሪውን በድጋሚ አቅርቧል።
ሰላም ለሁሉም !!
ሁሉም ለሰላም!!