Harari Region Peace and Security Bureau

Harari Region Peace and Security Bureau Peace For Humanity

የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡************************ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም.በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳ...
02/09/2026

የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡
************************
ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም.

በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ እና በፌደራል ፖሊሲ 27 ዙር መደበኛ ምልመላ እቅድ ዙሪያ ከፀጥታ አካላት ጋር ውይይት የተካሄደ ሲሆን

በውይይቱ የክልሉን አንፃራዊ ሰላም ለማፅናት በፀጥታ አካላትና በማህበረሰቡ ቅንጅት እየተሰራ ያለው ሥራ ውጤታማ መሆኑ የተገኘውን ውጤት ለማጠናከርም በቀጣይ በተቀናጀ መልኩ መስራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

እንዲሁም የ2019 የ1ኛ ዙር የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምልመላ ክልላችን በሀገር ደረጃ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻላችን የቅንጅታችን ውጤት መሆኑን ገልፀው በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተቋምን በሰው ኃይል ለማጠናከር ያላችሁን ተሞክሮ በመጠቀም መስፈርቱን ተከትላችሁ በተለይ የብሔር ተዋፅኦ በጠበቀ መልኩ ለስራው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን እንድትወጡ ሲሉ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ ገልፀዋል፡፡

የሐረሪ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር አህመድ አብዲ በበኩላቸው የ27ኛው ዙር መደበኛ ምልመላ በተሳካ ሁኔታ ለመፈፀም በመቀናጀት በተገቢው የሙያ መስፈርት የተሰጠውን ኮታ በቁጥር ብቻ ሳይሆን በጥራት መፈፀም ተቋሙን በብቁ የሰው ኃይል ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑም ገልፀዋል ።

በመርሃ ግብሩ የዘጠኙም ወረዳ የሰላምና ፀጥታ አስተባባሪዎች፣ የጣቢያ አዛዦችና የሰው ኃይል ዳይሬክተሮች ተሳትፈዋል።
ሰላም ለሁሉም!!!!
ሁሉም ለሰላም!!!!

01/09/2026

የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ በኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝተው ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ...

“የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለሀገር እና ለሕዝብ አለኝታነቱን በተግባር እያስመሰከረ ነው።”

ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

01/09/2026
01/09/2026

ሳምንታዊ መልዕክት

እንደ አዲስ የተሰጠን ህዝባዊ አደራ እና ቀጣዮቹ የትኩረት አጀንዳዎች

በቅርቡ በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ለብልፅግና ፓርቲ በድጋሚ የሰጠው ድምፅ፣ ሀገራችንን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የያዝነውን ራዕይ ከዳር ለማድረስ የተሰጠ ታሪካዊ አደራ ነው። እንደ ፓርቲ፤ በምርጫዉ የተገኘዉ ዘርፈ ብዙ ድል የምንዘናጋበት ሳይሆን የዜጎቻችንን የዕለት ተዕለት ህይወታቸዉ እንዲቀየርና የተሸለ ኑሮ የመኖር እንዲሁም የመልማት ፍላጎቶች እዉን ለማድረግ ለሚያስቸሉ ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት በትጋት እንድንሰራ የተሰጠንን ኃላፊነት የምናስታዉስበት ነው።

በመጪዉ መስከረም ወር የሚጀምረው የአዲሱ መንግሥት የሥራ ዘመን፣ የዜጎችን ህይወት የሚያሻሽሉና ሀገራዊ እድገትን የሚያፋጥኑ አበይት ስራዎች ቅድሚያ ተሰጥቶ ርብርብ የሚደረግባቸዉ ስራዎች ይሆናሉ። የምግብ ሉአላዊነትንና የግብርና ዘመናዊነትን በኩታ-ገጠም እርሻዎችና በቴክኖሎጂ አቅርቦት ማረጋገጥ፣ የታዳሽ ኃይልና የኢነርጂ አቅማችንን በማሳደግ የኢንዱስትሪ መደላድላችንን ማጠናከር፣ እንዲሁም በተፈጥሮ ጋዝ እና የኒዩክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አገራዊ አቅምን ማጎልበት የትኩረት ማዕከል ናቸው። በተጨማሪም፤ በአዲስ አበባ የተገኘውን አበረታች የከተማ መሰረተ-ልማትና የኮሪደር ስራዎች ተሞክሮ ወደ ሁሉም የክልል ከተሞች በማስፋት የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ ማሻሻል፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በስፋት በመጠቀም ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን የሚቀንስ እንዲሁም የተቀላጠፈ የህዝብ አገልግሎት ማቅረብ፣ ስኬታማ በነበረዉ የሀገራዊ ምክክር ሂደት በመታገዝ ዘላቂና የተረጋጋ ፖለቲካዊና ማህበራዊ መስተጋብርን እውን ማድረግ የሚሉትም ዋነኛ አጀንዳዎች ተደርገዉ የተያዙ ናቸው።

አዲሱ የመንግሥት አስተዳደር በመጪው መስከረም ወር ተመስርቶ ወደ ስራ ሲገባም እነዚሁ አጀንዳዎች የቀን ተቀን የትኩረት አቅጣጫዎች በመሆን ይተገበራሉ። ይህ ምዕራፍ፤ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በተካሄደዉ የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ በወጣዉ የአቋም መግለጫ በ3ኛነት ከሰፈረዉ “አገራዊ አቅማችንን በማጎልበት፣ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠር እና የፈጠራ ኢኮኖሚን በመገንባት የኢኮኖሚ ብልፅግና ግቦቻችንን ማሳካት” ከሚለው ነጥብ ጋር በቀጥታ የሚሰናሰን ነው። በጉባኤው የተያዘው አገራዊ አቅምን የማጎልበት ውሳኔ፣ በእነዚህ አበይት አጀንዳዎች ትግበራ አማካኝነት የዜጎችን ህይወት በተጨባጭ መለወጥ ወደምንችልበት ምዕራፍ እናሸጋግረዋለን፡፡

የዚህ ጉዞ መነሻም ሆነ መድረሻ የመደመር አገራዊ ዕሳቤ ሲሆን፤ የተያዙትን አጀንዳዎች መሬት ለማውረድ ደግሞ የመላዉ ኢትዮጵያዊያንን በሀብት ፈጠራ ላይ መትጋት እንዲሁም ፖለቲካዊ ብስለትን በማዳበር የራስን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችል ጽናት እና ቁርጠኝነት መላበስ መቻል እጅግ አስፈላጊ ነው።

አሁን ባለንበት ወቅት አበይት ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት እንዲሁም ኃያላን ሀገራት፣ የብልፅግና ፓርቲን ተቋማዊ ጥንካሬ፣ የአመራር ብስለትና ራዕይ፣ እንዲሁም የፖሊሲዎቻችንን ትክክለኛነት በግልጽ ተረድተዉ እውቅና እየሰጡ ይገኛሉ። የጀመርናቸው ሁለንተናዊ የልማት እና የዲፕሎማሲ ስራዎች ፍሬ ማፍራታቸው፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት ከፍ አድርጎታል።

የቀጣይ ጉዟችን መዳረሻ የሚሆነዉም 2023 ዓ.ም ላይ ሀገራችን ኢትዮጵያን "አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት" ማድረግ ነው። በ7ኛዉ ሃገራዊ ምርጫ ለህዝብ የገባናቸዉን ቃልኪዳኖች ሰንቆ መስከረም 2019 ዓ.ም የሚመሰረተዉ አዲሱ የመንግስት አስተዳደር፤ ይህን ግዙፍ ራዕይ ለማሳካት ይቻል ዘንድ በተሰጠው ህዝባዊ ይሁንታ እና በመደመር እሳቤ አጋዥነት የዜጎችን ህይወት ወደሚያሻሽልበት አዲስ የትግበራ ምዕራፍ ይገባል። ፓርቲያችን ብልፅግና፤ እንደ ሁልጊዜዉም የህዝብን አስተያየቶች እያዳመጠ፣ እንቅፋቶችን በድል እየተሸገረ፣ ችግሮችን እየፈታ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እና ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ያደርጋል!

ብልፅግና ፓርቲ

ነሐሴ 24፤ 2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ

የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከክልል ፀጥታ ተቋማትና ከፌደራል ፀጥታ ተቋማት የክልላችንን ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ በመገምገም በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ መክሯል፡፡ ⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳ነሀሴ...
31/08/2026

የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከክልል ፀጥታ ተቋማትና ከፌደራል ፀጥታ ተቋማት የክልላችንን ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ በመገምገም በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ መክሯል፡፡
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳
ነሀሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም.

በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ላይ በማተኮር በክልላችን ያለውን አንፃራዊ ሰላም ለማፅናት የፀጥታው አካል በቅንጅት መስራት እንዳለበት በተለይ ከአጎራባች ወረዳዎች እስከ ቀበሌ ድረስ በመቀናጀት በጋራ እየተሰራ ያለው ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ እንዲሁም የ2019 የ1ኛ ዙር የመደበኛ ሰራዊት ምልመላ ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻላችን የቅንጅታችን ውጤት ነው ሲሉ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ በውይይቱ ገልፀዋል፡፡

በክልሉ በመከናወን ላይ የሚገኙ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን መጠበቅ እንደሚገባ የፀጥታው አካል በመቀናጀት ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ጥበቃን በማጠናከር የአካባቢውን ሰላም እንዲጠበቅ በማድረግ ኃላፊነታችንን መወጣት ይገባል ፡፡

በቀጠይም የፌደራል ፖሊስ ተቋምን በሰው ኃይል ከማጠናከር አንፃር የተሰጠንን ኮታ በጥራት መፈፀም እንደሚገባ ፡፡ ጳጉሜ 3 የፅናት ቀንን ለማክበር በሚሰሩ ዋና ዋና ኹነቶች ጥቅል እቅድ ላይ በመወያየት በቀጣይም ከሚመለከታቸው የፀጥታ መዋቅር ጋር እለቱን በድምቀት ለማክበር ለመወያየተር አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
በውይይቱም የፌደራል ፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና የክልል ፀጥታ ተቋማት አመርሮች የተገኙ ሲሆን በተሠጠው የስራ መመሪያ በመግባባት ተጠናቋል፡፡

ሰላም ለሁሉም!!!!
ሁሉም ለሰላም!!!

28/08/2026
27/08/2026
የሀረሪ ክልል የ2019 1ኛ ዙር መደበኛና ሙያተኛ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምልምሎች የሽኝት መርሃ ግብር ተካሄደ።ነሀሴ ቀን 17/12/2018 የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በኩራት ለመቀላቀል ከ...
23/08/2026

የሀረሪ ክልል የ2019 1ኛ ዙር መደበኛና ሙያተኛ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምልምሎች የሽኝት መርሃ ግብር ተካሄደ።

ነሀሴ ቀን 17/12/2018 የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በኩራት ለመቀላቀል ከሀረሪ ክልል የተመለመሉ ጀግኖች ወጣቶች ወደ ማሰልጠኛ ማዕከል ቦታ ሽኝት ተደረገላቸው።

​በሽኝት መርሃ-ግብር ላይ የሀረሪ ክልል ምክረሸ ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ ሱልጣን አብዱሰላም በተገኙበት ለወጣቶቹ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ወጣቶቹ የሀገርን ሰላም፣ ጸጥታና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የሚያስችለውን ታሪካዊ አደራ ለመወጣት ወደ ማሠልጠኛ ማዕከል መሄዳቸው አርዓያነት ያለውና የሚያኮራ ተግባር መሆኑን በመግለፅ እንኳን ለዚህ ታሪካዊ እና ሀገራዊ ሃላፊነት ለመወጣት እድሉን ሥላገኛሁ እንኳን ደሥ አላችሁ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።

የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ተወካይና የሚሊሻ ጽ/በረት ሃላፊ አቶ ከማል ሻም በበኩላቸው ​ለሀገር ክብር ሲሉ ቃልኪዳናቸውን አክብረው ለተሰለፉት ጀግኖች ወጣቶቻችን የተሳካና ሰላማዊ የስልጠና ጊዜ ይሁንላቹሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በሽኝት መርሃ ግብሩ የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነሮች፣ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አመራሮች ፣ዳይረክሮረች የሁሉም ወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል ።

ሰላም ለሁሉም!!!
ሁሉም ለሰላም!!!

በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ለጀግናው ቤተሰብ የማዕድ ማጋራት መረሃ-ግብር ተካሄደ በሐረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ -ግብር ለጀግናው የሀገር መከላከያ...
21/08/2026

በሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ለጀግናው ቤተሰብ የማዕድ ማጋራት መረሃ-ግብር ተካሄደ

በሐረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ በክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ -ግብር ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቤተሰብ የማዕድ ማጋረት መርሃ ግብር ተካካሄዷል።

በማዕድ ማጋራት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ተወካይና የክልሉ የሚሊሻ ጉዳይ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ከማል ሻም እንደገለጹት መደጋገፍና መረዳዳት የሕሊና እረፍት ብቻ ሳይሆን ዘላቂ ሰላምን፣ ፍቅርንና ጠንካራ ህዝባዊ አንድነትን የሚገነባ ትልቅ ባህላዊና ሀገራዊ እሴታችን ነው ብለዋል።

Address

Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Region Peace and Security Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share