Harari Regional State Innovation and Technology Agency

Harari Regional State Innovation and Technology Agency Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Harari Regional State Innovation and Technology Agency, Government Organization, Harar.

መላ: በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ የመረጃ ሉዓላዊነትን የሚያፋጥን ሀገር በቀል የቋንቋ ሞዴል!
19/05/2026

መላ: በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ የመረጃ ሉዓላዊነትን የሚያፋጥን ሀገር በቀል የቋንቋ ሞዴል!

📢 የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!ዲጂታል ኢትዮጵያን በሳይበር ደህንነት እና በቴክኖሎጂ እውቀት ለመገንባት ራዕይ ላላቸው ወጣቶች የተዘጋጀው 5ተኛው ዙር የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ የዕጩ ...
19/05/2026

📢 የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!

ዲጂታል ኢትዮጵያን በሳይበር ደህንነት እና በቴክኖሎጂ እውቀት ለመገንባት ራዕይ ላላቸው ወጣቶች የተዘጋጀው 5ተኛው ዙር የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ የዕጩ ሰልጣኞች ምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!

ባለፉት ዙሮች በካምፑ አልፈው ዛሬ ላይ የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ስታርት-አፕ የመሰረቱ፣ በድሮን ቴክኖሎጂ፣ በኢምቤድድ ሲስተምስ እና በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ሀገራዊ ችግር ፈቺ ስራዎችን እየሰሩ ያሉ የካምፑ ፍሬዎችን ተመልክተናል።
እርስዎስ የዚህ ጉዞ አካል ለመሆን ምን ይጠብቃሉ?

📅 የምዝገባ ማጠቃለያ ቀን፦ እስከ ግንቦት 17 / 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ!
የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ተሰጥኦ ያላቸው፣ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶች የተራዘመውን እድል ተጠቅማችሁ ፈጥናችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።

🔗 የምዝገባ ሊንክ፦ https://ctc.insa.gov.et/registration
ፈጠራችሁን ወደ ተግባር ቀይራችሁ የሀገራችሁን የሳይበር ሉዓላዊነት የምታስከብሩበት መድረክ ይጠብቃችኋል!


INSA- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር

16/05/2026
16/05/2026
16/05/2026
16/05/2026
ባሉበት ሆነው የሚወስዱት ነፃ የኦንላይን ስልጠና በአምስት ሚልዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደሮች ኢንሼቲቭ በመሰጠት ላይ የሚገኙትን🌐 በዌብ -ፕሮግራሚንግ 🤖 በአንድሮይድ ማበልፀግ 📊 ዳታ ሳይንስ እን...
15/05/2026

ባሉበት ሆነው የሚወስዱት ነፃ የኦንላይን ስልጠና

በአምስት ሚልዮን ኢትዮጵያዊያን ኮደሮች ኢንሼቲቭ በመሰጠት ላይ የሚገኙትን

🌐 በዌብ -ፕሮግራሚንግ
🤖 በአንድሮይድ ማበልፀግ
📊 ዳታ ሳይንስ እንዲሁም
🧠 አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎች ዙርያ ያተኮሩ የኮዲንግ መሠረታዊ ክህሎትን ለማዳበር የማያስችሉ ነጻ የኦንላይን ሥልጠናዎችን https://ethiocoders.et/ በዚህ ሊንክ ላይ ያገኟቸዋል፡፡

15/05/2026
15/05/2026

📣 ተራዘመ!

በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለስታርታፖች የቀረበው ታላቅ እድል የምዝገባ ጊዜ እስከ ግንቦት 21፣2018 ዓ.ም ተራዘመ!

በበርካታ የእድሉ ፈላጊዎች ጥያቄ መሰረት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የስታርታፕ ድጋፍ ሁለተኛ ዙር መርሓ-ግብር የምዝገባ ጥያቄ ተራዝሟል፡፡

በመጀመሪያው ዙር ሁሉን አቀፍ የድጋፍ መርሓ-ግብር ከ200 በላይ የቴክኖሎጂ አፍላቂዎች፣ ተመራማሪዎች እና የዘርፉ ባለሙያዎች የእድሉ ተጠቃሚ ሆነዋል። እነዚህ ወጣቶች በነበራቸው ቆይታ ድንቅ የፈጠራ ሃሳቦቻቸውን ወደ ተግባራዊ የንግድ ሞዴል እና ምርት በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ስኬት አስመዝግበዋል። ኢንስቲትዩቱ ይህንን ተሞክሮ መሰረት በማድረግ አሁን ደግሞ ይበልጥ ሰፊ እና አዳዲስ ድጋፎችን በማካተት ሁለተኛ ዙር ዕድል አመቻችቷል።

🎯በግብርና፣ በጤና፣ በደህንነት፣ በትምህርት፣ በፋይናንስ፣ በሮቦቲክስ፣ በኤ.አይ ኤጀንት፣ በቨርችዋል እና ኦግመንትድ ሪያሊቲ ዘርፎች ላይ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ሁሉ መሳተፍ ይችላሉ፡፡

⏰ የምዝገባ ጊዜ፡- እስከ ግንቦት 21፣ 2018 ዓ.ም

🔗ለማመልከት፡- aistartup.aii.et ይጠቀሙ!

📌በዚህ ታላቅ እድል የፈጠራ ሃሳብዎን ወደ ተጨባጭ ምርት እና አገልግሎት፤ ህልምዎን ወደ እውነታ እንዲቀይሩ ተጋብዘዋል!

11/05/2026

🚀 የኢመደአ የ2018 ዓ.ም የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ ፕሮግራም ምዝገባ ተጀመረ!

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ላለፉት 4 ተከታታይ ዓመታት በሳይበር ደህንነትና ተዛማጅ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች በመለየትና በማሰልጠን ወደ ሳይበር ኢንዱስትሪው እንዲቀላቀሉ፣ ወደ ተቋሙ እንዲገቡ እንዲሁም የራሳቸውን ስታርታፕ እንዲጀምሩ አስችሏል።

በ2018 ዓ.ም ደግሞ ከቀደሙት ዓመታት በተሻለ አቅምና ዝግጅት 5ኛውን ዙር የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል። ፕሮግራሙ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት እስከ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ድረስ ያሉ ልዩ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸውን ታዳጊ ወጣቶች ያካትታል።
📌 ምዝገባው ከሚያዚያ 29/2018 እስከ ግንቦት 10/2018 ዓ/ም ድረስ ይቆያል!
📌 ለመመዝገብ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ያስፈልጋል!

💡 በሚከተሉት ዘርፎች ላይ ልዩ ፍላጎትና ተሰጥኦ ካላችሁ፦

🔹 ሳይበር ደህንነት

🔹 ዴቨሎፕመንት

🔹 ኢምቤድድ ሲስተም

🔹 ኤሮስፔስ

🔹 ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ

የሰመር ካምፕ ፕሮግራሙ በሚከተሉት ዩኒቨርሲቲዎች ይካሄዳል

1. አዲስ አበባ ሳይንሳን ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

3. ጅማ ዩኒቨርሲቲ

4. ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ

5. ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ

ይህ እድል ለእናንተ ነው!
📌 ስለ ፕሮግራሙ ዝርዝር መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን ይመልከቱ፦
https://t.me/insactc
📝 ለመመዝገብ፦
https://ctc.insa.gov.et/registration

Address

Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Regional State Innovation and Technology Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share