08/04/2026
በዛሬው እለት እሮብ የሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአካዳሚክ ኮሚሽን ስብሰባ አካሄደ። ኮሌጁ ተጠሪነቱ ለክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ እንደሆነ ይታወቃል እናም ለረጅም አመታት ተቋርጦ የነበረው የጤና ቢሮው በአካዳሚክ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ተሳትፎ ዛሬ በጤና ቢሮው ኃላፊ ክቡር ዶ/ር አብዲ አሚን ዳግም ነፍስ ዘርቶ ተመልሷል። ይህ ደግሞ ቢሮዉ ለኮሌጁ ምን ያክል ትኩረት እንደሰጠ ማሳያ ነው። በኮሌጁ ምቹ የስራ ከባቢን ለመፍጠርና ኮሌጁ የነበረውን ስመ ገናና ለመመለስ የታሰበና በቀጣይም የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ የታለመ ነው። ኮሌጁ ለ ዶ/ር አብዲ አሚንም ጊዜያቸውን አጣበዉ በመሃላችን በመገኘታቸውና ወደፊትም ከኮሌጁ ጎን እንደሚቆሙ ለሰጡን ቃል ያመሰግናል።
መጋቢት 29,2018 ዓ.ም