Harari Government communication affairs Office

Harari Government communication affairs Office ይህንን ፔጅ ላይክ በማድረግ ስለ ክልላችን ወቅታዊ የሆኑ መረጃዎችን ያግኙ።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን ህይወት ለማሻሻል እያገዘ ይገኛልየበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም በመንቀሳቀስ የዜጎችን ህይወት በማሻሻል ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በብ...
07/08/2026

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን ህይወት ለማሻሻል እያገዘ ይገኛል

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም በመንቀሳቀስ የዜጎችን ህይወት በማሻሻል ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ፡፡

በሀረሪ ከልል በክረምት በጎ ፍቃድ እየተከናወኑ በሚገኙ ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

በዚህ ወቅትም በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም ዜጎችን በማገዝና ሃብትን አቀናጅቶ በመምራት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

በተለይም በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ አቅመ ደካሞችንና አረጋዊያንን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ስራዎች እውን ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።

በዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

በመርሃግብሩም በ14 መስኮች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በዚህም በአሁኑ ወቅት የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና መልሶ ግንባታ፣ የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ፣ ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ የማጠናከሪያ ትምህርት የመስጠትና ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል

ከዚህ በተጨማሪም ማዕድ ማጋራት፣ አዳዲስና ነባር የመማሪያ ክፍል ግንባታ እና እድሳት ፣ የትምህርት ቤቶች የተማሪ ወንበሮች ጥገና፣ ጽዳትና ውበት ስራዎችን ጨምሮ የማጣቃሻ መጽሀፍት የማሰባሰብ ስራ በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ መደጋገፍ፣ የመተጋገዝና አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመው የዜጎችን እውቀት፣ ገንዘብ፣ ጉልበት እና ሌሎች ምቹ ሁኔታዎችን በሚገባ መጠቀምና ከድህነት መላቀቅ እንደሚያስፈልግ ነው የጠቆሙት።

አመራሩም በመርሃግብሩ የታቀዱ እቅዶች ወደ ተግባር ለመቀየር በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንዳለበት አሳስበዋል።

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትበኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ...
06/08/2026

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።

እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።

በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።

በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።

ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።

በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።

በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።

በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።

በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በሐረሪ ክልል 47 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ገብተዋል - ቢሮውበሐረሪ ክልል በ2018 በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ኢንተርፕ...
06/08/2026

በሐረሪ ክልል 47 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ ገብተዋል - ቢሮው

በሐረሪ ክልል በ2018 በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ወደ ስራ የገቡ ኢንዱስትሪዎች ለዜጎች የስራ እድል እየፈጠሩ መሆኑም ተገልጿል።

የክልሉ ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሃምዲ ሰለሃዲን እንደገለጹት በክልሉ በተለይም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም ከማጎልበት ባለፈ በዘርፉ መነቃቃት እንዲፈጥር እያስቻለ ነው።

በክልሉ ወደ ስራ የገቡት ኢንዳስትሪዎች ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶችን በማጎልበትና ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጪ ምንዛሬን እያስቀሩና ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 47 መካከለኛ እና አነስተኛ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደሥራ እንደገቡ ገልጸው፣ ተጨማሪ 16 አዳዲስ ኢንዲስትሪዎች ደግሞ የግንባታ ሥራቸውን አጠናቀው ወደማሽነሪ ተከላ ሥራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

እንደ ምክትል ቢሮ ሀላፊው ገለጻ በክልሉ ወደሥራ የገቡት ኢንዱስትሪዎች ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጪ ምንዛሬን ከማስቀረት አንጻር ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።

አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ከሃይል አቅርቦት፣ ከመሰረተ ልማት ጋር በተያያዘ ያሉባቸውን ችግሮች ለመፍታት መሰራቱን ገልጸው፣ ዘንድሮ በኢንዱስትሪ ዘርፉ ብቻ 3 ሺህ 935 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ እድል ተፈጥሯል ብለዋል።

በቀጣይም የኢንዱስትሪ ዘርፍ የማጎልበት ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ አቶ ሀምዲ አያይዘው ገልጸዋል።

በፋብሪካዎቹ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች እንደሚናገሩት የስራ እድል ተፈጥሮላቸው እራሳችውንና ቤተሰባቸውን ከመደጎም ባለፈ ልምድ እየቀሰሙና በትርፍ ጊዜያቸውም የኮሌጅ ትምህርት እንዲከታተሉ እድል እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

በሐረሪ ክልል 196 ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ አምራች ኢንዳስትሪዎች በማምረት ስራ ላይ ናቸው።

ሐረር ከተማ በኮሪደር ልማት መድመቋን ቀጥላለችሐረር ከተማ የትላንት ከፍታዋን በሚመጥን ደረጃ በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ በከተማዋ በተለያዩ  አካባቢዎች ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስራዎች...
05/08/2026

ሐረር ከተማ በኮሪደር ልማት መድመቋን ቀጥላለች

ሐረር ከተማ የትላንት ከፍታዋን በሚመጥን ደረጃ በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተከናውነዋል።

የኮሪደር ልማት ስራዎቹም ትላንትን ከዛሬ የሚያስተሳስሩ ነገንም ታሳቢ ያደረጉ ናቸው።

የገናና ስልጣኔ መነሻ የታሪክ ሃብታሟ የምስራቋ ፈርጥ ሐረር ከተማ በየቀኑ ገናናነቷንና እድሜዋን በሚመጥን ደረጃ ከፍታዋን እያረጋገጠች ትገኛለች።

በከተማው የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ሌሎች የቅርስ ከተሞችም ተሞክሮ በሚሆን ደረጃ የቀደምት አባቶችን አሻራ ሳያደበዝዙ ይልቁንም ተጠብቆ እንዲቆይ በሚያስችልና ተጨማሪ ውበት በሚሆን መልኩ እውን ማድረግ ተችሏል።

በየእለቱ እየፈካች የምትገኘው ሐረር ከተማ ዛሬ ላይ ለመጎብኝት የምታጓጓ ለመኖር የምትመረጥ ነዋሪዎቿም የተመቸች ከተማ ሆናለች።

ታሪካዊቷ ሐረር ከተማ ዛሬም አዳዲስ ታሪክ እየሰራች ትገኛለች።

ከአዲስ አበባ የመጡ የኪንግደም መዘምራን ህብረት አባላት በሀረር ከተማ የተለያዩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን ጎበኙ።ከአዲስ አበባ የመጡ የኪንግደም መዘምራን ህብረት አባላት በሀረር ከተማ የተ...
05/08/2026

ከአዲስ አበባ የመጡ የኪንግደም መዘምራን ህብረት አባላት በሀረር ከተማ የተለያዩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን ጎበኙ።

ከአዲስ አበባ የመጡ የኪንግደም መዘምራን ህብረት አባላት በሀረር ከተማ የተለያዩ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

የህብረቱ አባላት በተለይም የሀረሪ ባህል ቤት፣ የአርተር ራንቦ ሙዚየምና በተለምዶ አስታራቂ መንገድ ተብሎ የሚጠራው መንገድን ጨምሮ የጁገል ኮሪደር ልማት ስፍራዎችን ተመልክተዋል።

ጎብኝዎቹ በወቅቱ እንዳሉት በከተማው ያሉ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች በእጅጉ አስደናቂ ሆነው እንዳገኟቸው ገልጸዋል።

ሐረር ከተማ እምቅ የቱሪዝም ሀብት መኖሩን እንደተመለከቱ ጠቅሰው በከተማው የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችም ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት አስተዋጽኦ እንዳለው አንስተዋል።

በሐረር ከተማ ያየናቸው የመስህብ ስፍራዎች አግራሞት የሚፈጥሩና የሚደነቁ ናቸው ብለዋል።

ማህበረሰቡም እንግዳ ተቀባይ መሆኑን በተግባር ማረጋገጣቸውን ያነሱት አባላቱ ከቤተሰቦቻችን ጋር ተመልሰው በመምጣት ተጨማሪ ጉብኝት ለማድረግ እንዳቀዱም ገልፀዋል።

በክልሉ የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር እና አቅርቦት እንዲጎለብት በማድረግ የኑሮ ጫናን ለማቃለል በትኩረት ይሰራል- ሸሪፍ ሙሜበክልሉ በተያዘው የበጀት ዓመት የገበያ የክትትልና...
05/08/2026

በክልሉ የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር እና አቅርቦት እንዲጎለብት በማድረግ የኑሮ ጫናን ለማቃለል በትኩረት ይሰራል- ሸሪፍ ሙሜ

በክልሉ በተያዘው የበጀት ዓመት የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር እንዲሁም የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦትን እንዲሻሻል በማድረግ የኑሮ ጫናን ለማቃለል በትኩረት እንደሚሰራ የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል።

የሐረሪ ክልል ንግድ ልማት ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ ሸሪፍ ሙሜ በበጀት አመቱ በሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ላይ
መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በያዝነው የበጀት አመት በክልሉ የኑሮ ጫናን ለማቃለል የሚያስችሉ ስራዎች በተጠናከረ መልኩ ይከናወናሉ ብለዋል።

በተለይም የገበያ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በማጠናከር የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦት እንዲሻሻል የማድረግ ስራዎች የላቀ ትኩረት ይሰጣል ብለዋል።

ሸማቹን ማህበረሰብ ለአላስፈላጊ ወጪና ለእንግልት የሚዳርጉ ሰው ሰራሽ የዋጋ ጭማሪዎች የሚያደርጉ ነገዴዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።

ከዚህ በተጨማሪ ምርትን በመደበቅ፣ እንዲሁም ከባዕድ ነገር ጋር መቀላቀልና ሌሎች ችግሮች እንዲፈጠር ምክንያት የሆኑ ነጋዴዎች ላይም እየተደረገ የሚገኘው ክትትልና ቁጥጥር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የምርት አቅርቦትን በማሻሻል፣ የገበያ ሰንሰለት ማነቆዎችን በመፍታትና ህገ-ወጥ ንግድን የመቆጣጠር ስራዎችም ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የቅዳሜና እሁድ ገበያን በማጠናከር የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችና የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በቀጥታ ለሸማቹ በማቅረብ የኑሮ ጫናን ለማቃለል እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ከዚህ ባሻገርም ቀልጣፋና ዘመናዊ የንግድ አሰራር መዘርጋት ሌላው ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን አስረድተዋል።

በመሆኑም ነጋዴው ማህበረሰብ ህዝቡን በቅንነት፣ በታማኝነት እንዲሁም ፍትሐዊ በሆነ ዋጋ ማገልገል እንዳለበት ያሳሰቡት አቶ ሸሪፍ ገበያው ሰላማዊና ሸማቹን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ እንዲከናወን ህዝቡ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚ...
04/08/2026

በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - ወይዘሮ ሮዛ ኡመር

በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ የስራ እድል ፈጠራ ም/ቤት ሰብሳቢ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ገለጹ።

የክልሉ የስራ እድል ፈጠራ ም/ቤት የ2018 በጀት አመት የስራ እድል ፈጠራ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት አመት እቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ የስራ እድል ፈጠራ ም/ቤት ሰብሳቢ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በክልሉ የስራ አጥነት ችግርን ለመፍታትና አዳዲስ ቋሚ የስራ እድሎች ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራን በማጎልበት እንዲሁም የስራ ፈላጊዎችን የስራ ባህልና ግንዛቤ ማስፋት ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መካከል መሆኑን ነው ወይዘሮ ሮዛ የተናገሩት።

በተለይ ገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ የክህሎት ስልጠናዎችን ከመስጠት ጀምሮ የዜጎችን የስራ ባህል በማሳደግ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ መስራት እንደሚያስፈልግ ነው የጠቆሙት።

በ2019 የበጀት አመት እቅድን ለማሳካት በሚከወኑ ስራዎች የሚገጥሙ ውስንነቶችን ለመቅረፍ በትኩረት መንቀሳቀስ ይገባል ብለዋል።

የሚመለከታቸው አካላት የስራ እድልን ለማጎልበት በቅንጅት መስራት እንደሚገ ነው ያመላከቱት።

በዚህም በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ለስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ ከእቅድ ጀምሮ እስከ አፈጻጸሙ ድረስ ቅድሚያ በመስጠት በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ወይዘሮ ሮዛ ተናግረዋል፡፡

የሀረሪ ክልል የኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢስማኢል ዩሱፍ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመላከቱት በስራ እድል ፈጠራና ስልጠና ከልማት አጋር አካላት፣ ከመንግስትና ከግል ሴክተሮች ጋር በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል።

በተጠናቀቀው የበጀት አመት 11 ሺ ቋሚ የስራ እድሎችን በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት በገጠርና በከተማ ለሚገኙ የክልሉ ዜጎች ማመቻቸት መቻሉን በሪፖርቱ ተመላክቷል።

በተፈጠረው የስራ እድል በዋናነት ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና ከስደት ተመላሽ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።

የገበያ ትስስርን በመፍጠርና በማዘመን የገበያ መረጃ አሰራርን በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል

በመድረኩ የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና ውስንነቶችን ለማረም የሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫስንትባበር ምን ማድረግ እንደምንችል ደጋግመን ለዓለም ያሳየንበት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬም በድል ተጠናቋል።ኢትዮጵያ ...
03/08/2026

ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ

ስንትባበር ምን ማድረግ እንደምንችል ደጋግመን ለዓለም ያሳየንበት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬም በድል ተጠናቋል።

ኢትዮጵያ የሚለው ስም በጋራ የመቻልና የጽኑ አቋም ተምሳሌት ነው። መንግሥት የሀገሪቱን ዘላቂ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን ሲያስቀምጥ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብም ሀገራዊ ፍላጎቱን በጋራ ተነሣሽነት እውን የማድረግ የዘመናት ልምምድ አለው። በተለይም መንግሥት ለአረንጓዴ ልማትና ሀገራዊ ከፍታ ለሚያቀርበው ጥሪ ሕዝቡ በላቀ ተሳትፎ ምላሽ የመስጠት ቁርጠኝነቱ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አብነት የሚሆን ነው።

መንግሥት በኢትዮጵያ የተራቆቱ አካባቢዎች በልጆቿ ብርቱ እጆች እንዲታከሙ፣ እየተስፋፋ የመጣው ድርቅና በረሃማነት በዘላቂነት እንዲገታ እና በአስተማማኝ መሠረት ላይ የተገነባ አረንጓዴ ኢኮኖሚ እውን እንዲሆን ግልጽና ጽኑ አቋም በመያዝ ጥሪ ሲያቀርብ ቆይቷል። በዚህም በላቀ የሕዝብ ተሳትፎና በመንግሥት መሪነት ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን ማድረግ ተችሏል፤ ኢትዮጵያዊያን ዛሬ ላይ ምድራቸውን አረንጓዴ ማልበስ ባህላቸው አድረገውታል ፤ባለፉት ሰባት ዓመታት ብቻ በአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለው ኢትዮጵያ አረንጓዴ ሸማ ለብሳለች። ዘንድሮም በንቅናቄው 8ኛው ዓመት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን፣ በክረምቱ ደግሞ በአጠቃላይ 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል መንግሥት ቁርጠኛ አቋሙን በይፋ አሳውቋል።

ለመንግሥት ሀገራዊ ጥሪ ቀናኢ የሆኑ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችም ይህንን ጥሪ በሙሉ ባለቤትነት ተቀብለው ለስኬቱ ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል። በዚህም በዛሬው ዕለት 26 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በአንድ ጀምበር ከ805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የተቀመጠውን ግብ ከዕቅድ በላይ አሳክተውታል። ይህ መንግሥትና ሕዘብ ሲተባበሩ ምን ማድረግ አንደሚችሉ የሚያሳይ፣ ማንም በዓለም ላይ ያለ ሀገር በቀላሉ ሊያሳካው የማይችል ድንቅ ስኬት ነው።

ይህ ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና የመንግሥት ስትራቴጂካዊ አቋም በአንድ አቅጣጫ ላይ እንደሚገኙ ማረጋገጫ ነው። በዛሬው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 26 ሚሊዮን ኢትዮያውያን ብርድ፣ ዝናብና ፀሐይ ሳይበግራቸው መሬት ሲያለምዱ ውለዋል፤ በዚሁ ጽኑ እንቅስቃሴም የዘንድሮው ክረምት ከገባ ጀምሮ 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተክለዋል። ኢትዮጵያ በልጆቿ ኮርታለች፤ መንግሥትም የሕዝቡን ከፍተኛ ቁርጠኝነትና ባለቤትነት ባየበት በዚህ ታሪካዊ ክስተት ከፍተኛ ኩራትና ክብር ተሰምቶታል። ይህም መንግሥት ይህንን ታላቅ ሕዝብ በበለጠ ኃላፊነትና ታማኝነት የማገልገል ጽኑ አቋሙን እንዲያጠናክር ተጨማሪ ብርታት ሆኖታል።

ክቡራን ኢትዮያውያን፣ ክቡራን የኢትዮጵያ ወዳጆችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አካላት፤ ዛሬ ይኸንን አገራዊ ራዕይ በጋራ እውን ማድረግ እንድንችል ስላደረጋችሁት ከፍተኛ ርብርብ መንግሥት በኢትዮጵያ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀርባል። የክረምቱን አጠቃላይ የ8 ቢሊዮን ችግኞች ተከላ ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የተጀመረው አገራዊ ተሳትፎና ጽኑ አቋም ተጠናክሮ ይቀጠጥላል ።

ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

03/08/2026

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ላይ ያስተላለፉት መልዕክት

የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብሩ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው- አቶ ኦርዲን በድሪየአረንጓዴ አሻራ መርሃግብሩ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል፣ የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ፣ ምርትና ምር...
03/08/2026

የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብሩ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው- አቶ ኦርዲን በድሪ

የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብሩ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል፣ የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገግሙ፣ ምርትና ምርታማነትን እንዲያድግ እና የስራ እድልን በማሳደግ ረገድ ተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

በክልሉ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አየተከናወነ ይገኛል።

በመርሐ ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የምስራቅ እዝ ምክትል አዛዥ ሜጀር ጀነራል ፍቃዱ ፀጋዬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር፣ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሱልጣን አብዱሰላም፣ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወየሳ እና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም አርሶ አደሮች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንዳሉት አረንጓዴ ዐሻራ የአካባቢ ልምላሜን ለማሳደግና የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ አግዟል።

መርሐ ግብሩ መጪውን ትውልድ ታሳቢ ያደረገ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ መርሐ ግብሩን በቅንጅት በማሳካት ለመጪው ትውልድ ልምላሜን ለማስረከብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይም የተተከሉ ችግኞችን የጽድቀት መጠን ከፍ ለማድረግ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የመንከባከብ ስራ በተጠናከረ መልኩ እንደሚከናወን አመላክተዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ሃላፊ ሮዛ ኡመር በበኩላቸው፤ በክልሉ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች የአርሶ አደሩ የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

ተግባሩን በማስቀጠል በዘንድሮው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በማሳተፍ በከተማና በገጠር ቀበሌዎች በተዘጋጁ 14 ስፍራዎች የፍራፍሬ፣ የደንና የእንስሳት መኖ ችግኞች እየተተከሉ መሆኑን አስታውቀዋል።

Address

Ethiopia, Harari Peoples Regional State, Harar City
Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Government communication affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Harari Government communication affairs Office:

Shortcuts

Share