Harari Police Commission

Harari Police Commission Harari Police Commission
(1)

1.1 የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን አመሰራረት /Establishemnt/

በአዋጅ ቁጥር 38/1996 አንቀጽ 26 ንዑስ አንቀጽ (2)(ረ) መሰረት የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በደንብ ቁጥር 38/1996 ለሀረሪ ክልል ፕሬዝዳንት ተጠሪ ሆኖ የተቋቋመ የሀረሪ ክልላዊ መንግስት መስሪያ ቤት ነዉ፡፡ ኮሚሽኑ አንድ ዋና ኮሚሽነር እና ሁለት ምክትል ዋና ኮሚሽነር የሚመራ ነው።

1.2.የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ራእይ፤ ተልእኮ እና እሴት

ራዕይ /vision

ክልላችን ሠላምና ደህንነት የሠፈነባትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ክልል ሆና ማየት ነው

ተልእኮ /mission

የሀገሪቱንና የክልሉን ህገ-መንግስትና ሌሎች ህጎችን አክብሮ በማስከበ

ርና የህብረተሠቡን ተሳትፎ በማሳደግ ወንጀልንና የትራፊክ አደጋን መከላከል፤ ተፈፅሞም ሲገኝ በህግ አግባብ አጣርቶ አጥፊዎች ተገቢውን የህግ ውሳኔ እንዲያገኙ በማድረግ የክልሉን ህብረተሰብ ሠላምና ደህንነት ማረጋገጥ፤

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በCCTV ካሜራ የተደገፈ የፀጥታ ክትትል ሥርዓት እያስጠበቀ ነው።   7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሐረሪ ክልል በሰላምና በተረጋጋ ሁኔታ እየተካሄደ...
01/06/2026

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በCCTV ካሜራ የተደገፈ የፀጥታ ክትትል ሥርዓት እያስጠበቀ ነው።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሐረሪ ክልል በሰላምና በተረጋጋ ሁኔታ እየተካሄደ ሲሆን፣ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የምርጫውን ሰላምና ደኅንነት ለማስጠበቅ በCCTV ካሜራዎች እና በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓቶች የተደገፈ የፀጥታ ክትትል ተግባራዊ አድርጓል።
ኮሚሽኑ በምርጫ ጣቢያዎች፣ በድምፅ ቆጠራ ማዕከላት እና በሌሎች ወሳኝ ቦታዎች የተዘረጉ የፀጥታ አውታሮችን በማስተባበር የምርጫውን ሂደት በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ገልጿል።
በተለይም በCCTV ካሜራዎች የተደገፈው የክትትል ሥርዓት የፀጥታ ሁኔታዎችን በእውነተኛ ጊዜ ለመከታተል እና ለሚከሰቱ የፀጥታ ክስተቶች ተገቢና ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ ያስችላል።
የኮሚሽኑ ስትራቴጂክ አመራሮችም በተቀናጀ የትዕዛዝና ቁጥጥር ማዕከል በመገኘት የምርጫውን የፀጥታ ሁኔታ በቀጥታ እየተከታተሉ ሲሆን፣ በየደረጃው የተሰማሩ የፖሊስ አባላትም በከፍተኛ ዝግጁነት ሕዝቡ የዴሞክራሲያዊ መብቱን በነፃነት እንዲጠቀም አስፈላጊውን የፀጥታ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።
የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የምርጫው ሂደት በሰላም፣ በሕግ የበላይነት እና በሕዝብ እምነት እንዲጠናቀቅ ከማኅበረሰቡ እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት በመተባበር መስራቱን ገልጾ፣ ሕዝቡም የሰላም እና የሕግ የበላይነት ጥረቶችን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርቧል።
ዘጋቢ፡
ሳጅን ዮሐንስ መካ

በሐረር ከተማ ግንቦት 24ቀን 2018 ዓ/ም ብቻ ለተወሰነ ሰአታት ባጃጅ ማሽከርከር እንደማይቻል የተነገረ መሆኑ ይታወቃል ነገረ ግን ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ tvsእና ፎርስ አገልግሎት...
01/06/2026

በሐረር ከተማ ግንቦት 24ቀን 2018 ዓ/ም ብቻ ለተወሰነ ሰአታት ባጃጅ ማሽከርከር እንደማይቻል የተነገረ መሆኑ ይታወቃል ነገረ ግን ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ tvsእና ፎርስ አገልግሎት መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን
የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን።

ሐረር፣ ግንቦት 24/2018 ዓ.ምበሐረሪ ክልል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰላማዊ፣ ሥርዓታማ እና አስተማማኝ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን፣ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንም የምር...
01/06/2026

ሐረር፣ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም
በሐረሪ ክልል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰላማዊ፣ ሥርዓታማ እና አስተማማኝ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን፣ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንም የምርጫውን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ያደረገውን ዝግጅት እና ስምሪት በተሳካ ሁኔታ እያከናወነ መሆኑ ተገለጸ።

በክልሉ የተቋቋሙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች አስፈላጊውን የሰነድ ርክክብ እና የማረጋገጫ ሥርዓት ካጠናቀቁ በኋላ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በይፋ ተከፍተው መራጮችን ማስተናገድ ጀምረዋል። በዚህም ሂደት የፖሊስ አባላት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች እና አካባቢዎቻቸው በመሰማራት የፀጥታ ጥበቃ ሥራቸውን በከፍተኛ ኃላፊነት እየተወጡ ይገኛሉ።

መራጮችም በሥርዓት በመሰለፍ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን እየተጠቀሙ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ በክልሉ የምርጫ ሂደትን የሚያውክ ወይም የፀጥታ ስጋት የሚፈጥር ክስተት አለመከሰቱ ተገልጿል።

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት እና ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅት በመስራት የምርጫው ሂደት ነፃ፣ ሰላማዊ እና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ የሆኑ የፀጥታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታውቋል።

ዘጋቢ፡
ሳጅን ዮሐንስ መካ

ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በፀጥታ ስራ ላይ የሚሰማሩ የፖሊስ አባላት የስምሪት አቅጣጫና የአፈፃፀም መመሪያ ተሰጠ። የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ ሁኔታ እንዲካሄድ...
31/05/2026

ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በፀጥታ ስራ ላይ የሚሰማሩ የፖሊስ አባላት የስምሪት አቅጣጫና የአፈፃፀም መመሪያ ተሰጠ።

የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አስተማማኝ ሁኔታ እንዲካሄድ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከሐረሪ ማረሚያ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በምርጫው ሂደት በተለያዩ የፀጥታ ስምሪት ቦታዎች ላይ የሚሰማሩ የፖሊስ አባላትን የስራ ስምሪት አቅጣጫና የአፈፃፀም መመሪያ ሰጥቷል።

መድረኩ ላይ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ነገራ ዱፌራ የስራ መመሪያ ሰጥተው፣ ምርጫ የዴሞክራሲ መገለጫና የሕዝብ ፈቃድ የሚንፀባረቅበት ሕገ-መንግሥታዊ ሂደት በመሆኑ የፀጥታ አካላት ኃላፊነታቸውን በከፍተኛ ሙያዊ ብቃት፣ በገለልተኝነትና በተጠያቂነት መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ኮሚሽኑ ከማረሚያ ፖሊስ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የጋራ የፀጥታ ዕቅድ በማጠናከር በምርጫው ቅድመ ዝግጅት፣ በምርጫ ቀን እና ከምርጫው በኋላ የሚከናወኑ የፀጥታ ተግባራት በተቀናጀ፣ በተሳለጠና በተጠናከረ መልኩ እንዲፈፀሙ አቅጣጫ መቀመጡ ተገልጿል።

በተሰጠው መመሪያ መሰረት የፖሊስ አባላት በምርጫ ሂደቱ ውስጥ ሙሉ ገለልተኝነታቸውን በመጠበቅ፣ የሕግ የበላይነትን በማስከበር፣ የዜጎችን ሕገ-መንግሥታዊ መብቶችና ነፃነቶች በማክበር እንዲሁም ማንኛውንም የፀጥታ ስጋት በፍጥነት እና በሙያዊ ብቃት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያዎች መተላለፋቸው ታውቋል።
ምክትል ኮሚሽነር ነገራ ዱፌራ በመግለጫቸው፣ በምርጫ ወቅት የሚከሰቱ ማናቸውም የፀጥታ ችግሮች ሕግን መሰረት ባደረገ፣ የሰብአዊ መብት መርሆዎችን ባከበረ እና በሙያዊ አሰራር በተደገፈ መንገድ መፍትሄ እንዲያገኙ የፀጥታ አካላት ዝግጁ ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም ሁሉም የፀጥታ አካላት በቅንጅት፣ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እና በሙያዊ ሥነ-ምግባር ተግባራቸውን እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀርቧል። በተጨማሪም የክልሉ ሕዝብ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር የምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደት እንዲሳካ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ ተላልፏል።
ዘጋቢ፡
ሳጅን ዮሐንስ መካ

ለሰላማዊ ምርጫ በትጋት እየሰሩ እንደሚገኙ የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን አባሎች ገለፁ። ኢ/ር አሸብር ሰቦቃ በተመደበበት የሸንኮር ወረዳ ፍፁም ሰላማዊና የተረጋጋ ምርጫ እዲኖር ከተመደበበት ጊዜ አን...
31/05/2026

ለሰላማዊ ምርጫ በትጋት እየሰሩ እንደሚገኙ የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን አባሎች ገለፁ።

ኢ/ር አሸብር ሰቦቃ በተመደበበት የሸንኮር ወረዳ ፍፁም ሰላማዊና የተረጋጋ ምርጫ እዲኖር ከተመደበበት ጊዜ አንስቶ ምርጫዉ እስኪጠናቀቅ ድረስ በትጋት እንደሚሰራ ገልጿል ።

ኮማንደር ኡመር አሜ የአባድር ወረዳ ምርጫ አሰተባባሪ ሲሆኑ በወረዳቸዉ የተመደቡ አባሎችን በማሰማራት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ እንደሆነና እስካሁን ያለዉ እንቅስቃሴ ሰላማዊ መሆኑን ተናግረዋል።

ሳጅን ፍላጎት በቀለ በበኩሏ በሐኪም ወረዳ እንደተመደበች ገልፃ በተመደበችበት ቀጠና ከሌሎች የፀጥታ ሐይሎች ጋር በመቀኛጀት ከበላይ አመራሮች በተሰጡ መመሪያዎች መሰረት የተሰጣትን ሐላፊነት በትጋት እየተወጣች እንደምትገኝ ገልፃለች።

ኮ/ባል አንዋር ወረብ በበኩሉ ከኮሚሽኑ በተሰጡ መመሪያዎችና አቅጫጫ የተጣለበትን ሐላፊነት ቀን ከለሊት በትጋት እየፈፀመ እንደሚገኝ ተናግሯል።

ረ/ኢ/ር ሙሔዲን መሐመድ በተመደበበት አሚር ኑር ወረዳ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲያልፍ በወሰደዉ ስልጠና መሰረት የጥበቃ ስራዉን እያከናወነ እንደሚገኝና ችግርች በሚኖሩበት ሰአት ከአመራሮች ጋር ግንኙነት በማድረግ የተሰጠዉን ሐላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጿል።

ዘጋቢ
ሳጅን አዲሱ በፍቃዱ

በሐረሪ ክልል በሁሉም ወረዳ ፖሊስ ጣቢያዎች ለሰላማዊ ምርጫ የፀጥታው ስራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ። በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ስር የሚገኙ የየወረዳዎቹ ፖሊስ ጣቢያ አዛዦች ለ7ኛ...
30/05/2026

በሐረሪ ክልል በሁሉም ወረዳ ፖሊስ ጣቢያዎች ለሰላማዊ ምርጫ የፀጥታው ስራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ።

በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ስር የሚገኙ የየወረዳዎቹ ፖሊስ ጣቢያ አዛዦች ለ7ኛዉ ሐገራዊ ምርጫ በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

አዛዦቹ እንደገለፁት የ7ኛዉ ሐገዊ ምርጫ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ እቅዶችን በማዉጣትና ወደ ተግባር በመቀየር እየሰሩ እንደሚገኙ የገለፁ ሲሆን በተለይ የፖሊስ አባላት በምርጫ ወቅት ሊኖራቸዉ በሚገባ ስነ-ምግባር ላይ ስልጠና በመስጠት በፖሊሳዊ ዲሲፒሊን እንዲመሩ መደረጉን ገልፀዋል።

በጥበቃ ሰበካ ቦታዎች ላይ በቋሚና ተንቀሳቃሽ ጥበቃዎችን በመመደብና በስራዎቹ ላይ የቅርብ ክትትል ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ የገለፁ ሲሆን እስካሁን ባለዉ ሁኔታ ላይ ምንም አይነት ችግር አለመኖሩን ገልፀዋል።

ምርጫዉ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲያልፍ በሁሉም ወረዳዎች ድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ላይ የፖሊስ አባላት መመደባቸዉን የየወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አዛዦች ገልፀዋል ።

ዘጋቢ
ሳጅን አዲሱ በፍቃዱ

30/05/2026
29/05/2026
በሀረሪ ክልል 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል፦ ኮሚሽነር አህመድ አብዲ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና በስኬት እንዲጠናቀቅ ...
29/05/2026

በሀረሪ ክልል 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል፦ ኮሚሽነር አህመድ አብዲ

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተማማኝ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አህመድ አብዲ በሰጡት መግለጫ ምርጫው ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲካሄድና የክልሉ ነዋሪዎች ያለምንም ስጋት ወጥተው ድምጻቸውን መስጠት እንዲችሉ የፀጥታ አካላት በቂ ስልጠና በመውሰድ አካላዊና አእምሮዊ ቅድመ ዝግጅት አጠናቅቀው ወደ ስምሪት ገብተዋል።

ፖሊስ የምርጫ ጣቢያዎችንና ቁሳቁሶችን ደኅንነት ከመጠበቅ ጀምሮ መላው የምርጫ ሂደት በፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን የጸጥታ መዋቅሩ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫና በድህረ ምርጫ ሂደት በትጋት እንደሚሠራም አረጋግጠዋል።

ይህንን ታላቅ አገራዊና ክልላዊ ኩነት በስኬት ለመወጣት የሐረሪ
ፓሊስ ከፌደራል ፖሊስ፣ ከመከላከያ ሰራዊት፣ ከሚሊሻ እና ከሌሎች አጋር የጸጥታ አካላት ጋር የጋራ እቅድ ተዘጋጅቶ በቅንጅት እየተሠራ እንደሚገኝም ኮሚሽነሩ በሰጡት መግለጫ ጠቁመዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በምርጫው ሂደት ላይ ሁከት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ ማናቸውንም ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ለመከላከል የሚያስችል ጠንካራ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋቱንም አብራርተዋል።

በመጨረሻም ኮሚሽነር አህመድ የክልሉ ሕዝብ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ወጣቶችና የሚዲያ አካላት የምርጫው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከጸጥታ አካላት ጎን በመቆም የተለመደውን ቀና ትብብር እንዲያደርጉና ጥቆማዎችን በመስጠት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በምርጫ ወቅት በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ። የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን በምርጫ ወቅት በሴቶችና ህፃናት ላይ ሊፈፀሙ የሚችሉ ጥቃቶችን ለመከላከል...
28/05/2026

በምርጫ ወቅት በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ።

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን በምርጫ ወቅት በሴቶችና ህፃናት ላይ ሊፈፀሙ የሚችሉ ጥቃቶችን ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ከሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያዘጋጀው ስልጠና መሠጠቱ ተገለፀ።

የስልጠናው መድረክ በሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ነገራ ዱፌራ ተከፍቷል።
ምክትል ኮሚሽነሩ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት፣ በምርጫ ሂደት ወቅት ሴቶችና ህፃናት ለተለያዩ ጥቃቶች ተጋላጭ ሊሆኑ ስለሚችሉ ተቋማት በቅንጅት በመስራት ቅድመ መከላከልና ፈጣን ምላሽ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

በስልጠናው ላይ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ግሩም ዉብሸት በምርጫ ወቅት በሴቶችና ህፃናት ላይ ሊፈፀሙ የሚችሉ ጥቃቶችን እንዴት መከላከል እንደሚቻል፣ ለተጎጂዎች የሚሰጥ ድጋፍና የህግ ከለላ እንዲሁም ተቋማት በጋራ የሚሰሩበትን አሰራር በተመለከተ ስልጠና ሰጥተዋል።

ስልጠናው በምርጫ ሂደት ወቅት በሴቶችና ህፃናት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ጥቃቶችን አስቀድሞ መከላከል፣ የተፈጠሩ ችግሮችን በህጋዊ አግባብ መፍታት እና ተጎጂዎች ተገቢ ድጋፍና ከለላ እንዲያገኙ የሚያስችሉ አሰራሮች ላይ ትኩረት ተሰጥቶበታል።
በስልጠናው ላይ ከፖሊስ፣ ከፍትህ ተቋማት፣ ከሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮዎች እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎች በቀጣይ በጋራ በመስራት በምርጫ ሂደት ወቅት የሚከሰቱ የፆታ ተኮር ጥቃቶችን ለመከላከልና ለተጎጂዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ቁርጠኝነታቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡
ሳጅን ዮሐንስ መካ

Address

Near 847J+M43, Awzin Street, 9°18'50"N 42°07'48"E • 1. 86 Km
Harar
3200

Telephone

+251256667537

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Police Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Harari Police Commission:

Share