Harari Police Commission

Harari Police Commission Harari Police Commission
(1)

1.1 የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን አመሰራረት /Establishemnt/

በአዋጅ ቁጥር 38/1996 አንቀጽ 26 ንዑስ አንቀጽ (2)(ረ) መሰረት የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በደንብ ቁጥር 38/1996 ለሀረሪ ክልል ፕሬዝዳንት ተጠሪ ሆኖ የተቋቋመ የሀረሪ ክልላዊ መንግስት መስሪያ ቤት ነዉ፡፡ ኮሚሽኑ አንድ ዋና ኮሚሽነር እና ሁለት ምክትል ዋና ኮሚሽነር የሚመራ ነው።

1.2.የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ራእይ፤ ተልእኮ እና እሴት

ራዕይ /vision

ክልላችን ሠላምና ደህንነት የሠፈነባትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ክልል ሆና ማየት ነው

ተልእኮ /mission

የሀገሪቱንና የክልሉን ህገ-መንግስትና ሌሎች ህጎችን አክብሮ በማስከበ

ርና የህብረተሠቡን ተሳትፎ በማሳደግ ወንጀልንና የትራፊክ አደጋን መከላከል፤ ተፈፅሞም ሲገኝ በህግ አግባብ አጣርቶ አጥፊዎች ተገቢውን የህግ ውሳኔ እንዲያገኙ በማድረግ የክልሉን ህብረተሰብ ሠላምና ደህንነት ማረጋገጥ፤

ብቁና ተወዳዳሪ የፖሊስ ሰራዊት ለመገንባት በትኩረት መሰራት እንደሚገባ ተገለፀ የሐረሪ ፖሊስ ወና ጠቅላይ መምሪያ ከሐረሪ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋር በመተባበር በ27ኛው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ...
02/09/2026

ብቁና ተወዳዳሪ የፖሊስ ሰራዊት ለመገንባት በትኩረት መሰራት እንደሚገባ ተገለፀ

የሐረሪ ፖሊስ ወና ጠቅላይ መምሪያ ከሐረሪ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋር በመተባበር በ27ኛው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ምዝገባ ዙሪያ ውይይት አካሂዱ

በውይይቱ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶፊቅ መሐመድ እንደገለፁት፣ ብቁና ተወዳዳሪ የፖሊስ ሰራዊት እንዲገነባ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ህዝብን የሚያገለግል ፖሊስ ብቁና ታማኝ የሐገር ፍቅር ስሜት ኖሮት የህግ የበላይነትን በቁርተኝነት የሚያስከብር መሆን እንዳለበት ገልፀዋል።

ስለዚህ የሚመለመሉ የፌድራል ፖሊስ አባል ሆነው መስፈርቱ የሚጠይቀውን መመዘኛ የሚያሟሉ እና የሚሰጠውን ስልጠና በብቃት የሚወጣ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።

የሐረሪ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር አህመድ አብዲ በበኩላቸው፣ የፌደራል ፖሊስ ለሐረሪ ክልል የሰጠው ኮታ ተቀብሎ ወደ ምዝገባ ስራ መገባቱን ገልፀዋል።

የምዝገባው ሂደት ውጤታማ እንዲሆንም በጋራ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ምልመላው ሲካሄድ በጥንቃቄና ሐላፊነት በተሞላበት ሁኔታ መካሄድ እንዳለበት ገልፀዋል።

በውይይቱ የየወረዳዎቹ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎችና የሐረሪ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘገባ
አዳሱ በፍቃዱ

ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት  ለመንገድ መሠረተ ልማት የሚውል ንብረት በመሸጥ ተሰውሮ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ክትትል ተያዘ። በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የሐኪም ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ፣ ከ1.3...
31/08/2026

ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ለመንገድ መሠረተ ልማት የሚውል ንብረት በመሸጥ ተሰውሮ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ክትትል ተያዘ።

በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የሐኪም ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ፣ ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያለውን ለመንገድ መሰረተ ልማት ሥራ የሚውል በእምነት የተሰጠውን የውሐ ፍሳሽ ቱቦ ማምረቻ ላሜራ በመሸጥ ከሐረር ከተማ ተሰውሮ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተገለጸ።

የሐኪም ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ም/ኢ/ር ጀማል ሱፊያን እንደገለጹት፣ ግለሰቡ ለመሰረተ ልማት ሥራ አገልግሎት የሚውሉ የውሐ ፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦ ማምረቻ ላሜራ ብረቶችን በእምነት በአደራ የተሰጠውን በመሸጥ እና ከዚያም ከሐረር ከተማ ተሰውሮ ነበር ይላሉ ሐላፊው።

ፖሊስ ከማህበረሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪው በኦሮሚያ ክልል ወሊሶ ከተማ መሸሸጉን መረጃ በመድረሱ
የሐኪም ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በማውጣት ተጠርጣሪውን በወሊሶ ከተማ ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ም/ኢ/ር ጀማል ሱፊያን ገልጸዋል።

ፖሊስ የተሰረቀውን ንብረት ለማስመለስና በጉዳዩ የተሳተፉ ሌሎች ግለሰቦች ካሉ ለመለየት የምርመራ ሥራውን በማጠናከር ላይ መሆኑ ታውቋል።

የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ማህበረሰቡ ከወንጀል መከላከልና ህግን ማስከበር ሂደት ጎን ለጎን አጠራጣሪ ድርጊቶችን ሲመለከት በአፋጣኝ ለፖሊስ እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርቧል።

ዘጋቢ
ሳጅን አዲሱ በፍቃዱ

የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የአሽከርካሪዎች ስነ-ምግባርና የህግ ተገዢነት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ‎‎የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የአሽከርካሪዎች ስነ-ምግባር የትራፊክ ህጎችን ማክበርና ሙያዊ ግዴታን...
30/08/2026

የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የአሽከርካሪዎች ስነ-ምግባርና የህግ ተገዢነት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

‎የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የአሽከርካሪዎች ስነ-ምግባር የትራፊክ ህጎችን ማክበርና ሙያዊ ግዴታን በኃላፊነት መወጣት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

‎የሐረሪ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ ቁጥጥር ክፍል ከሐረሪ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር በሐረር ከተማ ከሚገኙ የባጃጅ ማህበር ኃላፊዎችና አሽከርካሪዎች ጋር በትራፊክ አደጋ መከላከል የትራፊክ ህግና ደንብ አክብሮ መንቀሳቀስ የመንገድ ላይ ምልክቶችን መጠበቅ በባጃጅ የሚፈጸሙ ስርቆቶችን መከላከልና ከአደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።

‎በመድረኩ ላይ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ነገራ ዱፌራ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

‎ምክትል ኮሚሽነር ነገራ ዱፌራ በንግግራቸው የትራፊክ አደጋ በሰው ህይወት በአካልና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርስ ጠቁመው የአደጋውን መጠን ለመቀነስ ከፖሊስ አካላት ብቻ ሳይሆን

‎ከአሽከርካሪዎችና ከሁሉም የመንገድ ተጠቃሚዎች የሚጠበቅ ኃላፊነት መኖሩን አስገንዝበዋል።
‎የትራፊክ አደጋ ጉዳትን ስንመለከት ማዘን ብቻ በቂ አይደለም አደጋዎችን ከመከሰታቸው በፊት በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል።

‎በተለይም አሽከርካሪዎች ፍጥነትን መቆጣጠር የመንገድ ምልክቶችንና የትራፊክ ህጎችን ማክበር ተገቢውን የመሳፈሪያና የማውረጃ ቦታ መጠቀም እና ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎችን ማክበር እንዳለባቸው አሳስበዋል።

‎የክልላችንን ለውጥ ለማፋጠን የሁላችሁም ትብብር ያስፈልጋል። ህግን የማያከብሩ አሽከርካሪዎች ህጉን እንዲያከብሩ በማድረግ በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት በጋራ መከላከል አለብን ሲሉ ገልጸዋል።

‎ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ ቁጥጥር ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ሙክታር አብዶሽ አሽከርካሪዎች ሙያዊ ግዴታቸውን በኃላፊነት በመወጣት የትራፊክ ህጎችን በተግባር ማክበር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

‎አሽከርካሪዎች ህጋዊ የሆኑ የመሳፈሪያና የማውረጃ ፌርማታዎችን ብቻ በመጠቀም ለትራፊክ ፍሰት መስተካከልና ለመንገድ ተጠቃሚዎች ደህንነት የራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጠይቀዋል።

‎ከዚህ ባለፈ በባጃጅ የሚፈጸሙ ስርቆቶችንና ሌሎች ወንጀሎችን ለመከላከል አሽከርካሪዎች ከፖሊስ ጋር በቅርበት በመስራት በጥርጣሬ የሚያዩዋቸውን ጉዳዮች በወቅቱ ለፖሊስ እንዲያሳውቁ ተናግረዋል ።

‎በመድረኩ የሐረሪ ክልል መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች የባጃጅ ማህበር ኃላፊዎችና የባጃጅ አሽከርካሪዎች ተሳትፈዋል።

‎ውይይቱ በከተማው የሚሰጠውን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ጥራት ማሻሻል የትራፊክ ህጎችንና ደንቦችን በአግባቡ ማስከበር የትራፊክ ፍሰትን ማስተካከል የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ማረጋገጥ እና በባጃጅ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በጋራ መከላከል ላይ ትኩረት አድርጓል።

‎በመጨረሻም ከተሳታፊዎች በተነሱ ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ላይ ምላሽ በመስጠት በቀጣይም በትብብር መስራትና የትራፊክ አደጋንና ተያያዥ ወንጀሎችን በጋራ ለመከላከል ቃል በመግባት ውይይቱ ተጠናቋል።

‎ዘጋቢ
‎ሳጅን ዩሐንስ መካ

ማህበረሰቡ ለቅድመ ወንጀል መከላከል እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንዳለበት ተጠቆመ።ማህበረሰቡ ለቅድመ ወንጀል መከላከል እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ በማጠናከር ከፖሊስ ጎን በመሰ...
30/08/2026

ማህበረሰቡ ለቅድመ ወንጀል መከላከል እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንዳለበት ተጠቆመ።

ማህበረሰቡ ለቅድመ ወንጀል መከላከል እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ በማጠናከር ከፖሊስ ጎን በመሰለፍ ለወረዳውና ለክልሉ ሰላምና ደህንነት የበኩሉን ሚና ማበርከት እንዳለበት ተጠቆመ።

የሸንኮር ወረዳ ፖሊስ በማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት ለሚሳተፉ የማህበረሰቡ አካላት የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጅቷል።

በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሐረሪ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር አህመድ አብዲ፣ ማህበረሰቡ በተለይም ቅድመ ወንጀል መከላከልን በተመለከተ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ ማጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል።

ኮሚሽነር አህመድ አብዲ አክለውም፣ ማህበረሰቡ በቀጣይም ከወረዳው ፖሊስ ጎን በመሰለፍ የወረዳውን ብሎም የክልሉን ሰላምና ደህንነት በተጠናከረ መልኩ ሊያስቀጥል ይገባል ብለዋል።

በዕለቱ በማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት ላይ የላቀ ተሳትፎ ላስመዘገቡ የማህበረሰቡ አካላት እና ለኮሚኒቲ ኦፊሰሮች የዋንጫ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቷል።

የምስጋና ፕሮግራሙ በወንጀል መከላከልና በሰላም ማስጠበቅ ረገድ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማበረታታት፣ በፖሊስና በማህበረሰቡ መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር እንዲሁም በቀጣይ የተሻለ የሰላምና ደህንነት ስራ ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ዘጋቢ
ሳጅን አዲሱ በፍቃዱ

የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች የ27ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ ምልመላ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠አዲስ አበባ፣ ነሐሴ...
28/08/2026

የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች የ27ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ ምልመላ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)፦ የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ27ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ ምልመላ ዕቅድ ላይ በዋና መሥሪያ ቤት ውይይት አካሂደዋል፡፡

በውይይቱ ዘመኑን የዋጀ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀም የሚችልና የማድረግ አቅሙ ያደገ ኢትዮጵያን የሚመስል የፖሊስ ሠራዊት የመገንባት ጉዞን በስኬት ለማስቀጠል ከሁሉም ክልሎች ሕብረ-ብሔራዊ ተዋፅኦንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ያደረገ የተሻለ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን ወጣቶች በመመልመል፣ በማሰልጠንና ስምሪት በመስጠት የተቋሙን የሰው ኃይል ፍላጎት ማሟላት አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል፡፡

በማሰልጠኛ ተቋማት ብዝሃነትን፣ አካታችነትን እንዲሁም ቁጥርና ጥራትን ባገናዘበ መልኩ፤ የተሟላ ጤንነትና የአካል ብቃት ያላቸው፤ የሚሰጣቸውን መሠረታዊ ፖሊሳዊ ሥልጠና በብቃት ወስደው ሀገራቸውን በፖሊስ ሙያ ለማገልገል የተዘጋጁ፣ ለሕገ-መንግሥቱ ታማኝ የሆኑ፣ ከዘር፣ ከሃይማኖት፣ ከፖለቲካና ከሌብነት የፀዱ፣ ማኅበረሰቡን በእኩልነት የሚያገለግሉ እና በሥነ-ምግባራቸውም የተመሰገኑ ወጣቶች ተመልምለው ወደ ማሰልጠኛ እንዲገቡ በከፍተኛ ትኩረት እየተሠራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የ27ኛ ዙር መደበኛ ምልምል ፖሊሶችን በጥራት ለመመልመልና ወደ ማሰልጠኛ ለማስገባት የተዘጋጀው ዕቅድ ከክልል አስተዳደር አካላት ጋር በመቀናጀት ለመተግበር አስፈላጊው ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን የክልል ፖሊስና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎችም ለምልመላው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ትብብርና ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ተቀጥረው ለማገልገል መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶች፣ በየክልሉ በሚገኙ ዞኖች፣ ወረዳዎችና የምልመላ ጣቢያዎች ከጳጕሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምረው መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

28/08/2026
“ትውልድን እንገንባ” በሚል መርህ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።የሐረሪ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት፣ ከሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ...
28/08/2026

“ትውልድን እንገንባ” በሚል መርህ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

የሐረሪ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት፣ ከሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮና ከፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የስልጠና መድረክ ነው።

ስልጠናውን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮማንደር ግሩም ውብሸት የሰጡ ሲሆን፣ በስልጠናው የየወረዳው ፖሊስ ጣቢያ አዛዦችና በሐረሪ ክልል የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰ መምህራን ተሳትፈዋል።

በተለይም ወጣቶች እና ተማሪዎች ለአደገኛ እፅ እና ሀሺሽ አጠቃቀም በመጋለጥ በትምህርታቸው፣ በጤናቸው፣ በቤተሰብ ግንኙነታቸውና በማህበራዊ ሕይወታቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስ እንደሚችል በስልጠናው ላይ ተብራርቷል።

አደገኛ እፅ እና ሀሺሽ ወጣቱን ትውልድ ከትምህርትና ከስራ እንዲርቅ፣ ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮችና ወንጀሎች ተጋላጭ እንዲሆን ሊያደርጉ ስለሚችሉ፣ ችግሩን ከመከላከል አንፃር ትምህርት ቤቶች፣ ፖሊስ፣ ቤተሰብና ማህበረሰብ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ በመድረኩ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም የሙስና አደጋ፣ የህግ ታዛዥነት፣ የሰላምና የማህበራዊ ኃላፊነት ጉዳዮች ላይ ተሳታፊዎቹ ግንዛቤ እንዲያገኙ ትኩረት ተሰጥቷል።

የወጣቱ ትውልድ የሀገር ነገ ተስፋ በመሆኑ፣ ከአደገኛ እፅና ከሌሎች ጎጂ ልማዶች ለመጠበቅ በቅድመ መከላከልና በግንዛቤ ሥራ ላይ በትኩረት መስራት የሁሉም ኃላፊነት መሆኑ ተገልጿል።

“ትውልድን እንገንባ” የሚለው መርህም ወጣቱን ትውልድ ከወንጀል፣ ከአደገኛ እፅ፣ ከሙስናና ከሌሎች ጎጂ ተፅዕኖዎች በመጠበቅ ለሀገር የሚጠቅም ትውልድ ለመገንባት የጋራ ትብብር እንዲጠናከር የሚያስገነዝብ መሆኑ ተጠቁሟል።

ዘጋቢ
ሳጅን አዲሱ በፍቃዱ

‎በመደመር እሳቤ የሚከናወነው ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ነው‎‎ሐረር፣ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም.‎በመደመር እሳቤ የሚከናወነው ሰው ተኮር የበጎ ፈ...
28/08/2026

‎በመደመር እሳቤ የሚከናወነው ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ነው

‎ሐረር፣ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም.
‎በመደመር እሳቤ የሚከናወነው ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የጎላ ሚና እየተወጣ መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
‎በክልሉ የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ ግብር በአቅመ ደካሞችና በአነስተኛ ገቢ ባላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ በማተኮር ተለያዩ የበጎ ተግባራት እየተከናወኑ ሲሆን፣ በዚህ ዕለትም ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።በድጋፍ መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዋና መርህ “ከእኔ በፊት ለእኛ” የሚለውን እሳቤ በመከተል አንዳችን ለአንዳችን በመቆም ሁላችንም ተጠቃሚ የምንሆንበትን ማህበራዊ ሥርዓት መገንባት መሆኑን ገልጸዋል።የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ሰው ተኮር በሆነ አሠራር የኢኮኖሚ ፍትሕን ማረጋገጥና የህብረተሰቡን እኩል ተጠቃሚነት ማሳደግ ያለመ መሆኑንም አቶ ኦርዲን ጠቁመዋል።በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት የተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትም የአንድ ወቅት ተግባር ብቻ ሳይሆን፣ የህይወት መርሕና የዕለት ተዕለት ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።የሐረሪ ክልል ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ክብርት ወ/ሮ ረምዚያ አብዱልወሀብ በበኩላቸው፣ የ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ ግብር በ14 የተለያዩ ዘርፎች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።በዋናነትም የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ የማዕድ ማጋራት፣ የደም ልገሳና የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ሃላፊዋ ጠቁመዋል።በዛሬው ዕለትም በመጀመሪያው ዙር ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማግኘታቸውን ወ/ሮ ረምዚያ ገልጸዋል።በመርሐ ግብሩ ላይ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ጠቅላይ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በመገኘት በመርሐ ግብሩ የተደረገውን የበጎ ፈቃድ ተግባር በመደገፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።ዳይሬክተሩ በማህበረሰቡ ውስጥ የበጎ ፈቃድን፣ የመተጋገዝንና የማህበራዊ ኃላፊነትን ባህል ለማጠናከር የሚደረጉ ተግባራት የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዓላማዎችንም የሚያጠናክሩ መሆናቸውን ገልጸው፣ ለተግባሩ ያሳዩትን ተሳትፎ አስመልክቶ እውቅና ተሰጥቷቸዋል።በበጎ ፈቃድ መርሐ ግብሩ ከፍተኛ ተሳትፎ ላደረጉ ሌሎች አካላትም እውቅና ተሰጥቷል። የድጋፉ ተጠቃሚ ወላጆችና ተማሪዎችም ያገኙት ድጋፍ የወላጆችን ኢኮኖሚያዊ ጫና ከማቃለሉ በተጨማሪ ለመጪው የትምህርት ዘመን በትጋት እንዲዘጋጁ አቅምና መነቃቃት እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የድጋፉ ተጠቃሚ ተማሪዎችና ወላጆች ተገኝተዋል

አስገድዶ የደፈረ ግለሰብ በ23 ዓመት እስራት ተቀጣ በሐረሪ ክልል ድሬ-ጠያራ ወረዳ፣ በልዩ ስሙ ገንደ አሌሌ በሚባል ስፍራ አንዲትን ግለሰብ አስገድዶ የደፈረ ተከሳሽ በ23 ዓመት እስራት መቀ...
27/08/2026

አስገድዶ የደፈረ ግለሰብ በ23 ዓመት እስራት ተቀጣ

በሐረሪ ክልል ድሬ-ጠያራ ወረዳ፣ በልዩ ስሙ ገንደ አሌሌ በሚባል ስፍራ አንዲትን ግለሰብ አስገድዶ የደፈረ ተከሳሽ በ23 ዓመት እስራት መቀጣቱ ተገለጸ።

የግል ተበዳይዋ ዕድሜዋ 30 ዓመት ገደማ ሲሆን፣ ተከሳሹ ሸሪፍ መሐመድ አብደላ ከምሽቱ 5፡00 አካባቢ ወደ መኖሪያ ቤቷ በር ሰብሮ በመግባት በተኛችበት ዱላና ሜንጫ በመጠቀም ጉዳት ካደረሰባት በኋላ በግድ እንደደፈራት ተገልጿል።

በድርጊቱ ምክንያትም የግራ ጉልበቷ መሰበሩን የተገለጸ ሲሆን፣ ጉዳዩ በሕግ አግባብ ተጣርቶ ተከሳሹ ሸሪፍ መሐመድ አብደላ በሐረሪ ከፍተኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርቦ ጥፋተኛ መሆኑ በመረጋገጡ በ23 ዓመት እስራት እንዲቀጣ መወሰኑ ተገልጿል።

የሐረሪ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሴቶችና ሕፃናት መርማሪ ሳጅን አዜብ ደመላሽ እንደገለጹት፣ የወንጀል ድርጊቶችን በሕግ ለማስጠየቅ በተለይም በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን ለመከላከልና ወንጀለኞችን በሕግ ለማስጠየቅ ምርመራዎች በሕግ መሠረት ይካሄዳሉ ብለዋል።

ሐረሪ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ
ለሰላምና ደህንነት በጋራ!

የአፋልጉኝ ማስታወቂያከዚህ በላይ የምትመለከቷት ወጣት መብሩክ በሀር መሐመድ የተባለችው የ17 አመት ልጅ እለተ ቅዳሜ በቀን ነሐሴ 16/12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰአት አካባቢ ላይ በ...
27/08/2026

የአፋልጉኝ ማስታወቂያ

ከዚህ በላይ የምትመለከቷት ወጣት መብሩክ በሀር መሐመድ የተባለችው የ17 አመት ልጅ እለተ ቅዳሜ በቀን ነሐሴ 16/12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰአት አካባቢ ላይ በሱማሌ ክልል ጂግጅጋ ከተማ ወረዳ ቀበሌ 01 ልዩ ስሙ ሐረር ኬላ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ላይ እንደወጣች አልተመለሰችም።
በመሆኑም የሐረሪ ክልል ነዋሪዎች ይችህ ወጣት ዛሬ ማለትም ሰኞ ነሐሴ 18/12/2018 ዓ.ም ሐረር ከተማ እዳለች ከመኪና ረዳት ጥቆማ የተሰማ ስለሆነ ይችን ወጣት ያየና ያለችበትን ቦታ ያየ
በ 09 10 19 28 84 ወይንም በ 09 15 74 93 29 በመደወል እንዲያሳውቁን እጠይቃለን ቤተሰቦቻ።

Address

Near 847J+M43, Awzin Street, 9°18'50"N 42°07'48"E • 1. 86 Km
Harar
3200

Telephone

+251256667537

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Police Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Harari Police Commission:

Shortcuts

Share