02/08/2026
የክልሉ ህዝብ ነገ በሚካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር በንቃት እንዲሳተፍ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ጥሪ አቀረቡ
በነገው እለት በሚካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ ህዝቡ በንቃት እንዲሳተፍ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ጥሪ አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከአካባቢ ጥበቃና የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለሀገራዊ መግባባት፣ ለአብሮነትና ለማህበራዊ መስተጋብር መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኝ የተከላ ጥሪ ተከትሎ ሐምሌ 27 በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ ተጠናቋል ብለዋል።
በመርሃግብሩ መሳተፍ ሀገርን መውደድ አንዱ የተግባር ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።
የክልሉ ህዝብ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ነገ በሚካሄደው በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርlሃ ግብር በነቂስ በመውጣትና በመሳተፍ ሀገራዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይገባል ሲሉ ነው የተናገሩት።