Munib Hay

Munib Hay Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Munib Hay, Harar.

01/06/2026

ሀብታም ስትሆን

26/05/2026

عيد مبارك وكل عام وانتم بخير وصحه وسلامه يارب العالمين

25/05/2026

🦅 Intelligence my prime minister

21/05/2026
20/05/2026

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት 667 የፈተና ማዕከላት ተዘጋጁ።

------------------------ // -----------------------------

(ግንቦት 11/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነመሆኑን ገልጿል ።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልል ማዕከላት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።

ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡

ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።

በየክልሎች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል።

ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ብለዋል።

ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/-of-education-ethiopia
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ

የ6ተኛ እና 8ተኛ ክፍል ክልል  አቀፍ ፈተና መርሀ ግብር ይፋ ሆኗል::‎‎ግንቦት 12/2018 ዓ.ም የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ተኛ እና 8ተኛ ክልልና ሀገር ...
20/05/2026

የ6ተኛ እና 8ተኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መርሀ ግብር ይፋ ሆኗል::

‎ግንቦት 12/2018 ዓ.ም የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ተኛ እና 8ተኛ ክልልና ሀገር አቀፍ ፈተና መርሀ ግብርን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህ መሰረትም የ6ተኛ ክፍል ሰኔ 2, 3 እና 4/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል::

‎የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አርሰላን አብዲ እንደገለፁት፣ የክልሉ ተማሪዎች በፈተናው ወቅት በስነ-ልቦና ተዘጋጅተው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።

‎ክልል አቀፉን ፈተና 6418 የ6ተኛ ክፍል ተማሪዎች በ32 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም 4624 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በ20 የመፈተኛ ጣቢያዎች የሚወስዱ መሆኑን ሓላፊው ገልጸዋል::

‎ቢሮው ከተማሪዎች፣ ወላጆች እና መምህራን ጋር ውይይት በማድረግ እንዲሁም ማጠናከሪያ ትምህርቶችን እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

19/05/2026

روسيا الاتحادية العظمى روسيا 🦅
Russian Intelligence 🦅🇷🇺
Russian Federation the Great Russian Intelligence

Address

Harar

Telephone

+251915736636

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Munib Hay posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Munib Hay:

Share