30/09/2022
የሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ ለሀኪም ወረዳ መስተዳድር አራተኛ ጤና ጣቢያ ከግማሽ ሚሊዬን በላይ የሚገመት የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ አደረገ።
የሀኪም ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ቶፊቅ መሀመድ በቦታው በመገኘት የተደረገውን ድጋፍ ከክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ያሲን አብዱላሂ እጅ በተቀበሉበት ወቅት ለተደረገው ድጋፍ የክልሉን ጤና ቢሮ በራሳቸውና በወረዳው ስም አመስግነዋል።