የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን Harari Prison Commission

  • Home
  • Ethiopia
  • Harar
  • የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን Harari Prison Commission

የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን Harari Prison Commission የሀረሪ ማረሚያ ኮሚሽን የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለህግ ታራሚዎች የመስረታዊ ፍላጎት የታሃድሶ እና ልማት የጥበቃ እና ደህንነት አገልግሎት ይስጣል።

የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና አመራሮች በማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የመስክ ምልከታና የድጋፍ መርሃ ግብር አካሄዱ​የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ሰላሃዲን እና የጠቅላ...
22/08/2026

የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞችና አመራሮች በማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የመስክ ምልከታና የድጋፍ መርሃ ግብር አካሄዱ

​የሀረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ሰላሃዲን እና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች በሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በመገኘት የክረምት በጎ መርሃ ግብርን ምክንያት በማድረግ ለህግ ታራሚዎች ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን፣ የኮሚሽኑን ሁለንተናዊ የስራ እንቅስቃሴም የመስክ ምልከታ አድርገዋል።

​በዚህ የመስክ ምልከታ ወቅት የሁለቱ ተቋማት የቅርብ ቅንጅታዊ አሰራር ውጤታማነት እና የታራሚዎች የእርምት ሁኔታ በስፋት ተገምግሟል።

​የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አድናን አህመድ እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል በፍርድ ቤቶች በኩል በወንጀል ጥፋተኛ ተብለው ወደ ማረሚያ ኮሚሽኑ በሚላኩ የህግ ታራሚዎች ላይ ያለቀጠሮ እና የፍርድ ሂደት መዘግየት ምክንያት በርካታ ክፍተቶች ይታዩ ነበር።

​ሆኖም በሁለቱ ተቋማት መካከል በተፈጠረው በጎና የቅርብ የጋራ ስራ ላለፉት ጊዜያት በተደጋጋሚ ሲነሱ የነበሩ አቤቱታዎችንና ጥያቄዎችን ሙሉ በሙሉ ለመፍታት መቻሉን ገልፀው፣ ይህ ቅንጅት የፍትህ ሂደቱ ፈጣንና ቀልጣፋ እንዲሆን ማድረጉን አስረድተዋል።

​የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ሙራድ አብዱላሂ በበኩላቸው፤ የጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራሮች እና ዳኞች ያካሄዱት የክረምት በጎ መርሃ ግብር እንዲሁም የተደረገው የመስክ ምልከታ ከፍተኛ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዳለው ገልጸዋል።

​ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም፤ የፍርድ ቤት አካላት በማረሚያ ቤት በአካል በመገኘት የታራሚዎችን የእርምት፣ የሙያ እና የስነ-ልቦና ማነፅ ሁኔታ በቅርበት መመልከታቸው ለፍትህ ስርአቱ መሻሻል እና ለህግ ታራሚዎች ሰብአዊ መብት አያያዝ መጎልበት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

​በተጨማሪም የጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራሮችና ዳኞች በህግ ታራሚዎች የማሳያ እርሻ ልማት ቦታ በመገኘት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ያካሄዱ ሲሆን፣ በዚህም የአካባቢ ጥበቃና የአረንጓዴ ልማት ጥረቱን ደግፈዋል።

​መርሃ ግብሩ የተጠናቀቀው የጠቅላይ ፍርድ ቤት አመራሮችና ዳኞች ለህግ ታራሚዎች ያዘጋጁትን ልዩ ልዩ ድጋፎች በማስረከብ እና በቀጣይም በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው አጋርነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በማረጋገጥ ነው።

ዘጋቢ :- ኮማንድር መህዲ

የሀረሪ ክልል የሽንኮር ወረዳ የሴቶች ክንፍ ለሴት የሕግ ታራሚዎች የ150 ሺህ ብር የአልባሳት ድጋፍ አደረገ።​ የሀረሪ ክልል የሽንኮር ወረዳ የሴቶች ክንፍ በክረምት በጎ ተግባር መርሃግብር ...
10/08/2026

የሀረሪ ክልል የሽንኮር ወረዳ የሴቶች ክንፍ ለሴት የሕግ ታራሚዎች የ150 ሺህ ብር የአልባሳት ድጋፍ አደረገ።

​ የሀረሪ ክልል የሽንኮር ወረዳ የሴቶች ክንፍ በክረምት በጎ ተግባር መርሃግብር አማካኝነት ለሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የሴት ሕግ ታራሚዎች የዋጋ ግምታቸው 150,000 (መቶ ሃምሳ ሺህ) ብር የሚያወጡ ልዩ ልዩ አልባሳት ድጋፍ አደረገ።

​በድጋፍ መርሃግብሩ ወቅት የኮሚሽኑ የሕግ ታራሚዎች መሰረታዊ ፍላጎት ዳይሬክተር ኮማንደር ዳንኤል ታምሩ ለሽንኮር ወረዳ የሴቶች ክንፍ አባላት ለተደረገው መልካም አጋርነትና ድጋፍ በሕግ ታራሚዎቹ ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

​የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሙራድ አብዱላሂ በበኩላቸው፤ የተደረገው ድጋፍ ኮሚሽኑ ታራሚዎችን የማረምና የማነፅ ተልእኮውን በውጤታማነት እንዲወጣ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

አክለውም፣ እንዲህ ባሉ በጎ ተግባራት ላይ የባለድርሻ አካላት ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ለተቋሙ ተልእኮ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ የሴቶች ክንፉ ላሳየው ቅንነቱና አርአያነት ያለው ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

​ይህ የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ድጋፍ የማህበረሰብ አባላትና ባለድርሻ አካላት በማረም ሂደቱ ውስጥ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑ ተመልክቷል።
ዘጋቢ:- ኮማንደር መህዲ

የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን እና የክልሉ ጠቅላይ አቃቢ ህግ ቢሮ የ2019 የበጀት ዓመት የጋራ ዕቅድ ተፈራረሙ።​የሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ከሀረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ቢሮ ጋ...
10/08/2026

የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን እና የክልሉ ጠቅላይ አቃቢ ህግ ቢሮ የ2019 የበጀት ዓመት የጋራ ዕቅድ ተፈራረሙ።

​የሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ከሀረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ቢሮ ጋር በ2019 የበጀት ዓመት የህግ ታራሚዎችን ሰብአዊ መብት ለመጠበቅ እና የማረምና የማነፅ ተልዕኮን ለማሳካት የሚያስችል የጋራ ትብብር ዕቅድ ተፈራረሙ።

​በስምምነት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የሥራ መሪዎች እና የማኔጅመንት አባላት በተገኙበት፣ የሀረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ለታ በዳዳ እና የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሙራድ አብዱላሂ የጋራ ዕቅድ ሰነዱን ተፈራርመዋል።

​በመርሐግብሩ ላይ ሁለቱ ተቋማት በ2019 የበጀት ዓመት የህግ ታራሚዎችን ሰብአዊ መብቶች በማስከበር፣ የባህሪ ለውጥና የማነፅ ስራዎችን በላቀ ደረጃ በማሳካት እንዲሁም የፍትህ ሥርዓቱን በማጠናከር የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ በቅንጅት እንደሚሰሩ መተማመናቸውን ገልጸዋል።

ዘጋቢ:- ኮማንደር መህዲ

10/08/2026
በሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በግል ወይዘሮ አልማዝ የማአድ ማጋራት ለ50 የህግ ታራሚዎች ድጋፍ አድርገዋል ። ወይዘሮ አልማዝ ላደረጉት ድጋፍ የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን  የመስረታዊ ፍላጎ...
10/08/2026

በሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በግል ወይዘሮ አልማዝ የማአድ ማጋራት ለ50 የህግ ታራሚዎች ድጋፍ አድርገዋል ።
ወይዘሮ አልማዝ ላደረጉት ድጋፍ የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የመስረታዊ ፍላጎትዳይሬክተር ኮማንደር ዳኔኤል በህግ ታራሚዎች ስም በድጋፉ አመስግነው ሌሎችም መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ በጎ ስራ የሚሰሩ ማህበራት ጠያቂ የሌላቸውን የህግ ታራሚዎች ይደግፉ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።

06/08/2026
የሀረር ከነማ እግርኳስ ደጋፊዎች ማህበር ለሴት ህግ ታራሚዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ​ሀረር — የሀረር ከነማ እግርኳስ ደጋፊዎች ማህበር የመንግስታችንን የክረምት በጎ ድጋፍ ...
06/08/2026

የሀረር ከነማ እግርኳስ ደጋፊዎች ማህበር ለሴት ህግ ታራሚዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

​ሀረር — የሀረር ከነማ እግርኳስ ደጋፊዎች ማህበር የመንግስታችንን የክረምት በጎ ድጋፍ መርሃግብር መነሻ በማድረግ በሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለሚገኙ ሴት የህግ ታራሚዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
​በድጋፍ መረከብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የሀረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ሙራድ አብዱላሂ የማህበሩ አመራሮችና አባላት ላደረጉት በጎ ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም የማህበሩ ይህ መልካም እንቅስቃሴ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችና ተቋማትም ተመሳሳይ ድጋፍ ለማድረግ እንዲነሳሱ መንገድ የሚከፍት መሆኑን ገልፀዋል።

​የማህበሩ አመራር አቶ ፈትሁረህማን ፈቂ በበኩላቸው፤ ማህበሩ የመንግስታችንን የክረምት በጎ ድጋፍ መርሃግብር መነሻ በማድረግ ይህንን የበጎ አላማ እንቅስቃሴ ማዘጋጀቱን ገልፀዋል።

​አቶ ፈትሁረህማን አያይዘውም ማህበሩ ከዚህ ቀደም የህክምና እርዳታ ለሚሹ የስፖርቱ ቤተሰቦች የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ መስራቱን አስታውሰው፤ በዛሬው እለት የሴት ህግ ታራሚዎችን መኖሪያ ክፍል በመጎብኘት ያደረጉት የንፅህና እቃዎች ድጋፍ የመጨረሻ እንዳልሆነና ወደፊትም የክረምት በጎ አደራጎት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

​በስነ-ስርዓቱ ማጠቃለያ ላይ የሀረር ከነማ እግርኳስ ደጋፊዎች ማህበር አባላትና አመራሮች የሴት ህግ ታራሚዎችን በአካል ተገኝተው በመጎብኘት ያዘጋጁትን የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ አስረክበዋል።
ዘጋቢ :-ኮማንደር መህዲ

04/08/2026

Address

አው ኢዚን
Harar
6827

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀረሪ ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን Harari Prison Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share