15/08/2014
እነሆ 2006 ዓ.ም ማብቂያ ለይ ደርሰናል፡፡ የክረምቱ ወቅትም ብዙ ሳናስተውለው እያለቀ ነው፡፡ ለምን ብዬ ሳስብ የብራዚሉ የዓለም ዋንጫ ደህና ሳያዘናጋን አልቀረም፡፡ አሁን ደግሞ ከአንድ ቀን በኋላ አብዛኛዎቻችን የምንዝናናበት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድሮች ይጀመራሉ፡፡ የዘንድሮውን ውድድር ቼልሲ ያሸንፋል የሚል ቅድመግምት በ ጎል/goal.com/ ድረ ገጽ ለይ አንብቢያለሁ፡፡ ለማንኛውም ለኛ ለወጣቶች አሪፍ መዝናኛ እንደሚሆን እጠብቃለሁ፡፡
ከዚህ ባሻገር በአገራችን ፖለቲካ ላይም ከፍተኛ የሆነ የስርዓት ለውጥ የምናካሄድበት ጊዜ እንደሚሆን አምናለሁ፡፡ እድሜ ለቴክኖሎጂ ሁላችንም አገራችን ስላለችበት የእድገት ደረጃ ወያኔ እንደሚነግረን ከ ደርግ አንጻር ሳይሆን ከዓለም አገሮች አንጻር እጅግ ኋላ ቀር እንደሆንን ተረድተናል፡፡ ሲጀመር በግሎባላይዜሽን ዘመን እና የአንድ አገር እድገት በወጪ ገቢ ንግድ ለይ መሰረት ያደረግ መሆኑ ግልጽ ሆኖ ሳለ እንዴት ወያኔ እራሱን ከሞተ ስርዓት ከደርግ ጋር እንደሚያወዳድር ሁላችንንም ግራ አጋብቶናል፡፡ ለማንኛውም አሁን አውቀናል ነቅተናልም፡፡ በወያኔ ስርዓት አይደለም የዛሬ 20 ዓመት የዛሬ 200 ዓመትም አናድግም፡፡ ምክንያቱም ከሌላው ዓለም አንጻር የአገራችን እድገት ባለህበት እርገጥ እንደሚባለው ነው፡፡ እኛ ወጣቶችም ይህንን በሚገባ ተረድተናል/ለአንድ አመት ያክል ባደረኩት ጥናት/፡፡
በመሆኑም ይህን ሊሞት እያጣጣረ ያለ እና አገርን የመምራት እውቀቱም ሞራሉም የሌለውን የወንበዴዎችና አገር ቦጥቧጮች/ዘራፊዎች/ ቡድን ታግለን የምናስወግድበት ዓመት ይሆናል፡፡
ድል ለሰፊው የኢትዮጲያ ሕዝብ!!!!!!!!!!!!