SNNPR Health Bureau

SNNPR Health Bureau This is our Official page. We hope that you will get Updated Health and Health related information.

በሀዲያ ዞን አንዳንድ  ወረዳዎች ላይ ለተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ ምላሽ አሰጣጥ ሂደት ማጠናከሪያ መድረክ ተካሄደበማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን በ5 ወረዳዎች ላይ የተከሰተውን የኩፍኝ ...
14/02/2024

በሀዲያ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ላይ ለተከሰተው የኩፍኝ ወረርሽኝ ምላሽ አሰጣጥ ሂደት ማጠናከሪያ መድረክ ተካሄደ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን በ5 ወረዳዎች ላይ የተከሰተውን የኩፍኝ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ባለፉት ሁለት ወራት ከክልል ጤና ቢሮ፣የህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት አመራርና ባለሙያዎች ጀምሮ እስከዞን በተደረገው የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ተግባር፣የግብአት አቅርቦት እና በተደረጉ ልዩ ልዩ ድጋፎች በሽታውን በፍጥነት ከመዛመት በመከላከል ሊከሰት የሚችለውን ሞት መከላከል የተቻለ ቢሆንም ወረርሽኙን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ባልቻሉ አንዳንድ ወረዳዎች ላይ የቅኝት እና ምላሽ አሰጣጥ ተግባራትን ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ በውይይት መድረኩ ላይ ተገልጿል ፡፡
በተለየ መልኩ የባለሙያና የአመራር ትኩረት ይሻሉ የተባሉ ወረዳዎች ተለይተው በቀጣይ ትኩረት አድርገው በሚሰሩባቸውን ሂደቶች ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

የኩፍኝ በሽታ በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው በፍጥነት የሚዛመትና ህፃናትን ለከፋ ጉዳትና ከፍ ሲልሞ ለሞት የሚዳርግ አደገኛ በሽታ በመሆኑ የክልል ጤና ቢሮና የህ/ብ ጤና ኢኒስቲትዩት ችግሩ በተከሰተባቸው መዋቅሮች የማኔጅመንት አካላትና ከፍተኛ ባለሙያዎችን በማቀናጀት ረዘም ላለ ጊዜ ቦታው ድረስ ወርደው እንዲደግፉ በማድረግ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶችን በማስቀጠል ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ለመግታት መረባረብ ይገባል ተብሏል ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሽመልስ ዋንጉሮ እና የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም መጫ በጋራ ባስቀመጡት አቅጣጫ የወረዳ አስተዳዳሪዎች ፣የጤና ጽ/ቤት ሃላፊዎች፣የፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊዎች የፖሊቲካና ርዕዮተ አለም ዘርፍ ሃላፊዎች እንዲሁም የዞን ጤና መምሪያ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተቀናጅተው በመስራት የተከሰተውን የኩፍኝ ወረርሽኝ በጥቂት ቀናት ውስጥ ማቆምን ጨምሮ በወባ መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም በሌሎች ጤና ነክ ተግባራት ላይ ተጨባጭ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በአፅንኦት አሳስበዋል፡፡

የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህንን አገልግሎት መዋል የሚችሉ የግብዓቶችን  ለማቅረብ የሚያስችል የውል ስምምነት መፈራረሙን የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ አስታውቋል በጌዴኦ ዞን የሚገኙ ሁሉም ወረዳ...
14/02/2024

የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህንን አገልግሎት መዋል የሚችሉ የግብዓቶችን ለማቅረብ የሚያስችል የውል ስምምነት መፈራረሙን የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ አስታውቋል

በጌዴኦ ዞን የሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች እና የከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤቶች የውል ስምምነት ከዲላ አጠቃላይ ሆስፒታል ኮሚኒቲ ፍርማሲና ከቀይ መስቀል ጋር መፈራረማቸው የማዕበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አባላትም በውል ስምምነቱ መካተታቸው ተገልጿል ።

የውል ስምምነቱ የማዕበረሰብ አቀፍ የጤና መድዕን ታካሚዎች ከመድዓኒት ጋር በተያያዘ የሚያጋጥማቸውን ተግዳሮት ከበመቅረፍ ባሻገር የአገልግሎት አለሟላትን አስመልክቶ ሚያነሡት ቅሬታዎችን እንደሚቀንስ ተመላክቶበታል።

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ትግበራ መጎልበት የጤና አገልግሎት ውጤታማነትን ለማጠናከር እንደሚረዳም ተገልጿል

በተለይም የ2016 በጀት አመት አፈፃፀምን በማላቅ ስምምነቱ በወረዳዎች እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ ከእቅድ የተቀመጠውን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ትግበራ ውጤታማነት ለማረጋገጥ ያስችላል ያሉት የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዷለም ማሞ ጥያቄ ሆስፒታሉና ቀይ መስቀሉ በመመለሱ በማመስገን በዞኑ በቀጣይ የማህበረሰብ መድሃኒት ቤት በየወረዳው ለመክፈት አቀዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የዲላ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንሰ ኮሌጅና የዲላ General ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈፃ አቶ ትዕዛኝ ተሰፋዬ በበኩላቸው ሆስፒታሉ በልዩ ትኩረት የማዕበረሰብ አቀፍ አባላት እርካታ ላይ እየሰራ መሆኑን ገልፀው በቀጣይነት ከዞን ጤና መምሪያ ጋራ በቅንጅት የሚሰሩ ስራዎች ዉጤታማነታቸው የላቀ መሆኑን አመላክተዋል ።

በስምምነቱ ወቅት የህዝቡን ጤና አገልግሎት ለማስጠበቅ የጤና መድህን ትግበራን ማጎልበት እንደሚገባ መልዕክቶች ተደምጠዋል ።

የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ጤና ቢሮ

የቲቢ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የማህበረሰብ ተሳትፎ ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀባለፉት 6 ወራት ከ4 ሺህ በላይ ናሙና በመውሰድ የቲቢ ምርመራ መከናወኑም ተገልጿል። ባለፉት 6 ወራት ከ4 ሺህ...
14/02/2024

የቲቢ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የማህበረሰብ ተሳትፎ ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ

ባለፉት 6 ወራት ከ4 ሺህ በላይ ናሙና በመውሰድ የቲቢ ምርመራ መከናወኑም ተገልጿል።

ባለፉት 6 ወራት ከ4 ሺህ 261 የቲቢ በሽታ ምርመራ ለማድረግ ናሙና የተወሰደ ሲሆን 665 ሰዎች ላይ በሽታው መገኘቱ በሪፖርት ተመላክቷል።

የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በሚፈለገው ልክ የቲቢ በሽታ ምልክት የሚታይባቸውን በመለየት ወደ ጤና ተቋም ከመላክ አንፃር ውስንነት መኖሩም ተገልጿል ።

በሽታውን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የግብዓት እጥረት እና የማሽን መበላሸት ተግዳሮት መሆኑ ተጠቁሟል።

የቲቢ በሽታ ስርጭትን ለመግታት የማህበረሰብ ተሳትፎ ጉልህ ሚና እንዳለው የገለፁት አስተያየት ሰጪዎች ምርመራ ለማድረግ የሚያግዙ ግብዓቶች በወቅቱ ለመዋቅሮች ሊሟላ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በሽታውን ለመከላከል ተግባራትን በተቀመጠ ስታንዳርድ መሠረት ተግባራትን አለመፈፀም ተግዳሮት መሆኑን የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች ውስንነቶችን በማረም በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በበኩላቸው የታችኛው መዋቅሮች የቲቢ ፕሮግራምን በተመለከተ በየወሩ እየገመገሙ ከመምራት አንፃር የሚስዋልባተውን ውስንነት ሊቀርፉ ይገባል ብለዋል።

የቲቢ በሽታን ለመከላከል መምሪያው አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የገለፁት ኃላፊው ቁርጠኛ ሆኖ ተግባርን ከማከናወን አንፃር ባለሙያው አከባቢ ውስንነት አለ ብለዋል።

በጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የማህበራው ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳርዛ የጤና ሴክተር ተግባር ከሰው ልጅ ህይወት ጋር የሚያያዝ በመሆኑ ባለሙያው ሙያዊ ስነ ምግባርን አክብሮ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

መዋቅሮች ከቲቢ ፕሮግራም አንፃር ውጤታማ ተግባር ለማከናወን ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ አመላክተዋል።

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ጤና ቢሮ

በጋሞ የወባ በሽታ ጫና ከፍተኛ በሆነባቸው ወረዳዎች የተደረጉ የድጋፍ ክትትል ስራዎች በውጤት ተገምግመዋል የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ላለፋት ሁለት ሳምንታት የወባ በሽታ ጫና ከፍተኛ በሆነባቸው ...
14/02/2024

በጋሞ የወባ በሽታ ጫና ከፍተኛ በሆነባቸው ወረዳዎች የተደረጉ የድጋፍ ክትትል ስራዎች በውጤት ተገምግመዋል

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ላለፋት ሁለት ሳምንታት የወባ በሽታ ጫና ከፍተኛ በሆነባቸው ወረዳዎች ከዞኑ ጤና መምሪያ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዳይሬክቶሬት፣ ከዞኑ ጤና መምሪያ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ዳይሬክቶሬት፣ ከዞኑ ጤና መምሪያ ፋርማሲ ባለሙያ እንዲሁም ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ላቦራቶሪ ኢንስቲትውት አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ የተወጣጡ ባለሙያዎች ሲያደርጉ የቆዩትን የድጋፉዊ ክትትል ግብረ-ምልስ የዞኑ ጤና መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያዎች በተገኙበት ማቅረባቸው ታውቋል፡፡

በግምገማውም የሁሉም ወረዳዎች የድጋፋዊ ክትትል ሪፖርት ቀርቦ የተገመገም ሲሆን በእያንዳንዱ ወረዳዎች ጠንካራና መሻሻል የሚገባቸው ተግባራት ተለይቶ መቅረቡና ለቀጣይም በየትኛው ወረዳ ትኩተር ሰጥቶ መደገፍ እንደሚገባ መለየት ተችሏል፡፡

በቀረበው ሪፖርት መነሻ ሰፋ ያለ ውይይት እና አስተያዬት ከተሳታፊዎች ተነስቶ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በመጨረሻም የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ በአጠቃላይ በግምገማው ወረዳዎች የወባ በሽታ ጫናን ለመቀልበስ ያላቸውን ዝንባሌና ቁመናን መለየት መቻሉን ጠቅሰው በዚህ መነሻ በድክመት የተገመገሙ ጉዳዮች እንዲሻሻሉ እና በጥንካሬ የተገመገሙ ጉዳዮች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ በአንክሮት አሳስበዋል፡፡

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ

የጤና ሚኒስቴር ለፌደራል ተጠሪ ተቋማትና ለክልል ጤና ቢሮዎች የተሸከርካሪና ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ድጋፍ አደረገ_____________ከጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ደረ...
14/02/2024

የጤና ሚኒስቴር ለፌደራል ተጠሪ ተቋማትና ለክልል ጤና ቢሮዎች የተሸከርካሪና ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ድጋፍ አደረገ
_____________

ከጤና ኬላ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ ድረስ ያለውን የጤና አገልግሎት ለማሳለጥና አገልግሎቶቹን ለማቀላጠፍ ይረዳ ዘንድ የተሸከርካሪና የላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ድጋፍ ለክልል ጤና ቢሮዎች፣ ለፌደራል ሆስፒታሊችና ተጠሪ ተቋማት ተደረገ፡፡

በድጋፍ ርክክቡ ወቅት ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ እንዳሉት በጤናው ዘርፍ የተያዘውንና በትኩረት እየተሰራበት የሚገኘውን የመካከለኛ ዘመን ኢንቨስትመንት ዕቅድን ከግብ ለማድረስ የክልል ጤና ቢሮዎች፣ የፌደራል ተጠሪ ተቋማት እና ሆስፒታሎች ያላቸው ድርሻ ጉልህ ነው ያሉ ሲሆን በተለይ የማህበረሰቡን የጤና ፍላጎት ለማርካትና ጥራት እና ፍትኃዊነት ያለው የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚደረጉ ድጋፎች የሚኖራቸው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም ብለዋል፡፡

በርክክቡ ወቅትም በዓለም ባንክ ድጋፍ አንድ መቶ ስልሳ (160) የሚሆኑ ተሸከርካሪዎችን መገዛታቸውንና በአሁኑ ወቅት የደረሱትን ስልሳ (60) ተሸከርካሪዎች በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት ለደረሰባቸው ክልሎች ቅድሚያ በመስጠት እንዲሁም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀመር መሰረት በማድረግ አበርክተናል ያሉት ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ የክልል ጤና ቢሮዎች እና የፌደራል ተጠሪ ተቋማት የተደረገላቸውን ድጋፍ ለጤና ስራ ብቻ እንዲያውሉት አደራ ብለዋል፡፡

የጤናውን ዘርፍ ከማዘመን ጋር ተያይዞ በዓለም ባንክ ድጋፍ ሰማንያ (80) የዲጂታል ጤና ባለሙያዎችን በመቅጠርና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በመሰማራት በርካታ ስራዎች እየተሰራ ነው ያሉት በጤና ሚኒስቴር የፋይናንስ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ሰለሞን እጅጉ ሲሆኑ ከዚህ ጋር ተያይዞ ከሁለት መቶ ሃምሳ አምስት (255) በላይ የላፕቶፕ ኮምፒውተሮች መገዛታቸው እና የርክክቡ አንድ አካል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ አቶ ሰለሞን አክለው እንደገለጹት የሚደረጉ ማናቸውም ድጋፎች በምንም መልኩ ከጤና ስራ ውጪ መዋል የሌለባቸው መሆኑን ገልጸው ይህ ሳይሆን ቢቀር ለወደፊቱ ሊያስከትል የሚችለው ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የክልል ላብራቶሪዎችን የስራ ጫና ከመቀነስና የተገልጋይን እርካታን ከመጨመር ረገድ ትልቅ አበርክቶ የሚኖራቸውን ከአራት መቶ ሃምሳ (450) በላይ የሚሆኑ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን እና ስምንት (8) የላብራቶሪ ናሙና ማድረስና የምርመራ ውጤት መመለስ የሚያስችሉ ተሸከርካሪዎችን በግሎባል ፈንድ በመግዛት ያስረከቡት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ሲሆኑ በተለይ እንደዚህ አይነት ድጋፎች በላብራቶሪ ናሙና ምልልስ ወቅት የሚያጋጥመውን ተግዳሮት በእጅጉ ይቀንሳል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ምግብ መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን አንድ መቶ ሰማንያ አምስት (185) የላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን ለተቆጣጣሪ አካላት ድጋፍ ያበረከተ ሲሆን የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ም/ል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስዩም ወልዴ በበኩላቸው ድጋፉ በቁጥጥር ስራው ላይ የሚኖረው እገዛ እና የቁጥጥርና ክትትል ስራዎችን ከማዘመን ረገድ የሚኖረው አበርክቶ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል ሲል መዘገቡን ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ማሆበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

በጤና ጣቢያ ደረጃ የሚሰጡ አገልገሎቶችን ማሻሻል የህብረተሰብን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንደሚያግዝ የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ አስታውቋል በደቡብ ኦሞ ዞን በማሌ ወረዳ የዶይሶ ጤና ጣቢያ በ...
14/02/2024

በጤና ጣቢያ ደረጃ የሚሰጡ አገልገሎቶችን ማሻሻል የህብረተሰብን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንደሚያግዝ የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ አስታውቋል

በደቡብ ኦሞ ዞን በማሌ ወረዳ የዶይሶ ጤና ጣቢያ በጤና ተቋማት የቦርድ ሰብሳቢዎች ተጎብኝቷል ።

የጤና ተቋማት የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጳውሎስ ጎዳና በዶይሶ ጤና ጣቢያ ከቦርድ አባላቶች ጋር በመሆን የጤና ጣቢያውን የውስጥ ክፍሎች ተዟዙረው በመመልከት በታዩ ጠንካራ ጎኖችና ደካማ ጎኖች ላይ ውይይት አካሂደዋል።

በመድረኩ የዶይሶ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ዳዊት ካሴ የ2016 በጀት ዓመት የስድስት/6/ ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ስያቀርቡ እንዳነሱት ከጠንካራ ተግባሮቻችን ባሻገር በጤና ጣቢያው የሠው ኃይል እጥረት ፣ የተሽከርካሪ ችግር፣የእናቶች በጀት እጥረት እንዲሻሻል ለቦርድ አባላቱ አንስተዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የቦርድ አባላቱ የጤና ጣቢያውን የወሊድ አፈፃፀም ፣የላብራቶሪ እና በፋርማሲ ክፍል የአገልግሎት አሠጣጥ መሻሻል አድንቀው ከባለሙያ ስነምግባር የፋይናንስ ስርዓት አያያዝ እና አሰራር መሻሻል ላይ ልዩ ትኩረት ልሰጥ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የጤና ጣቢያው ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጳውሎስ ጎዳና እንደገለፁት በጤና ጣቢያው በሁሉም ፕሮግራሞች ላይ አገልግሎቶችን ምቹ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ጥራት ላይ ሊሠራ እንደሚገባ ጠቅሰው የጤና ጣቢያ የውስጥ ገቢ ለማሳደግ ወቅቱን የጠበቀ ኦዲት በማድረግ ላይ ትኩረት እንደሚሠጥ አቅጣጫ አስቀምጧል ።

የማሌ ወረዳ ጤና ጥ/ጽ/ቤት ም/ ኃላፊ አቶ ማናአለ ማኮ በበኩላቸው በጤና ጣቢያ ደረጃ በአገልግሎት አሠጣጥ ጥራት ላይ ትኩረት መሠጠት እንዳለበት አንስተው ተላላፊ እና ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ፣በክትባት ተደራሽነት፣ ጥራት፣ የእናቶች እና ህፃናት ጤና አገልግሎት ላይ ከዚህ በላይ መሠራት እንዳለበት አብራርተዋል ።

ቦርዱ በአጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኃላ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ውይይቱን ቋጭተዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ

ብቁ ቀልጣፋና የሰለጠነ ፐብሊክ ሰርቫንት በማፍራት የተሻለች ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚገባ ተገለፀ፤በሀላባ ዞና ጤና መምሪያ እና በሀላባ ዞን ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መምሪያ ለ2 ተከታታይ ቀና...
13/02/2024

ብቁ ቀልጣፋና የሰለጠነ ፐብሊክ ሰርቫንት በማፍራት የተሻለች ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚገባ ተገለፀ፤

በሀላባ ዞና ጤና መምሪያ እና በሀላባ ዞን ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መምሪያ ለ2 ተከታታይ ቀናት "ከእዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሀሳብ ሲሰጥ የቆየው የመንግሰት መሠረተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ተጠናቀቀ።

በመድረኩም ብቁ ቀልጣፋና የሰለጠነ ፐብሊክ ሰርቫንት በማፍራት የተሻለች ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚገባ ተገልጿል።

ስልጠናው ከዕዳ ወደ ምንዳ ለመሸጋገር ያሉንን ሀብቶችና አቅሞች በመለየት በቀጣይ መከናወን በሚገቡ ጉዳዮችና ተገልጋይን እርካታ ያረጋገጠ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ፈጣን ልማት ለመረጋገጥ እንደ ሀገር በሚተገበሩ የመንግስት ሠራተኞች ተግባርና ሀላፊነት ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።

የስልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፈጻሚና አስፈጻሚውን የሰው ኃይል በተፈላጊው እውቀት፣ ክህሎት እና አስተሳሰብ በመገንባት ብቁ፣ ውጤታማ እና ቀልጣፋ ሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር ለህዝቡ ሙያዊ ስነ-ምግባርን በጠበቀ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጥ ማስቻል እንደሆነም አቶ አለማየሁ ጌታቸው በስልጠና ወቅት አንስተዋል።

በቀረቡት ሰነዶች ዙሪያ ሰፊ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው ዉይይት የተደረገ ስሆን ምላሽና ማብራርያ እንድሁም በቀጣይ በሚከናወኑ ነጥቦችና ሌሎች ተያያዥ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ በስፋት ዉይይት ተደርጓል በዛሬው እለት ተጠናቋል።

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሀሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር  የተጀመረዉ የመንግስት ሰራተኞች የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት ተጠናቀቀ፡፡"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ...
13/02/2024

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሀሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር የተጀመረዉ የመንግስት ሰራተኞች የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት ተጠናቀቀ፡፡

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሀሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር የተጀመረዉ የመንግስት ሰራተኞች የውይይት መድረክ "አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት በተደረገዉ ጥረት የመንግስት ሠራተኛዉ ሚና" በሚል ርዕስ የተዘጋጀን ሰነድ መሰረት በማድረግ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በአዲሱ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የመንግስት ሰራተኛው ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ አንተነህ ፍቃዱ የማጠቃለያ ውይይቱን በመሩበት ወቅት ተናግረዋል።

"ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሀሳብ ለመንግስት ሰራተኞች የተሰጠው ስልጠና የመንግስት ሰራተኛውን አቅም ከማጎልበት ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች የኢትዮጵያን ብሎም የክልሉን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነም ገልፀዋል።

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው የስልጠና መድረክ ላይ የተሳተፉ አስተያየት ሰጪዎች ስልጠናው እንደ ሀገር ያሉብንን እዳዎች ወደ ምንዳ እየቀየርን የሀገራችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የምናደርገውን ጉዞ የሚያቀላጥፍ ነው ሲሉ ገልፀው ከስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ ህዝባቸውን በላቀ ትጋትና ታማኝነት ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት ሲታሰብ ከዚህ ቀደም በአገልጋዩ በኩል ሲነሱ የነበሩ እና ዛሬም ድረስ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎችን በማረም ሊሆን እንደሚገባ የተጠቆመ ሲሆን በዋናነትም የረጅም ጊዜ ስልጠናና የትምህርት ዕድል በመስጠት ፣ የሰራተኞችን የአፈፃፀም ምዘና ተግባር ተኮር በማድረግ፣የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ማበረታቻና የማትጊያ ሽልማት በመሸለም እንደሚሆን ተብራርቷል።

ሊከሰቱ የሚችሉ ወረርሽኞችን ለቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች በዘላቂነት ሊሰራባቸው እንደሚገባ ተገልጿል የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሳምንታዊ የድንገተኛ ጊዜ አገልግሎት መስጫ ማዕከል (PHEOC) አፈ...
13/02/2024

ሊከሰቱ የሚችሉ ወረርሽኞችን ለቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች በዘላቂነት ሊሰራባቸው እንደሚገባ ተገልጿል

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሳምንታዊ የድንገተኛ ጊዜ አገልግሎት መስጫ ማዕከል (PHEOC) አፈጻጸም እና ወቅታዊ ተግባራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ገምግሟል፡

በመድረኩ ያለፈው ሳምንት የድረጊት መርሃ ግብር አተገባበርን አስመልክቶ ወደ ተግባር የተቀየሩ ገላጭ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን ሳምንታዊ ሪፖርት ከቀረበ በኋላ ለውይይት ጊዜ ተሰጥቶ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

በውይይቱ የወባ መጨመር፣ የምግብ ዕጥረት፣ TB ፤ Meningitis እና የሌሎች በሽታዎች መጨመር ትኩረት የተሰጣቸው ተግባራት መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ ተወካይ አቶ ኢዮብ ዳዊት እንዳሉት ሊከሰቱ የሚችሉ ወረርሽኞችን ከግንዛቤ በማስገባት ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን ጠቅሰው በተመሳሳይ መልኩ ወረዳዎች ላይ ከግብዓት ልየታ ጀምሮ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

አያይዘውም በተዋረድ ባሉ መዋቅሮች የአሰሳ ሥራዎችና የመከላከል ተግባራት ህዝቡን በማስተባበር የአካባቢ ጽዳትና ቁጥጥር መጠናከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል ፡፡

የአሪ ዞን ጤና መምሪያ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ጤና ቢሮ

የሐዘን መግለጫወንድማችን ዶ/ር አፈወርቅ ይመር ትላንት የካቲት 2, 2016 ከምሽቱ 4:30 በድንገተኛ ህመም በባቱ ከተማ ህይወቱ አልፏል።ዶ/ር አፈወርቅ የጠቅላላ ሐኪምነት ትምህርቱን በአርሲ...
12/02/2024

የሐዘን መግለጫ

ወንድማችን ዶ/ር አፈወርቅ ይመር ትላንት የካቲት 2, 2016 ከምሽቱ 4:30 በድንገተኛ ህመም በባቱ ከተማ ህይወቱ አልፏል።

ዶ/ር አፈወርቅ የጠቅላላ ሐኪምነት ትምህርቱን በአርሲ ዩኒቨርሲቲ ካጠናቀቀ በኋላ ለአመታት በሐኪምነት ሲያገለግል የቆየ ሲሆን ህይወቱ እስካለፈበት እለት ድረስ በባቱ አጠቃላይ ሆስፒታል ሲያገለግል ቆይቷል።

ዶ/ር አፈወርቅ በስራ ባልደረቦቹ በቤተሰቦቹ ፣ በጓደኞቹ ተወዳጅ ተግባቢ መልካም ስነ ምግባር የነበረው ሰው ነበር።

ዶ/ር አፈወርቅ ባለትዳርና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበር።

ለቤተሰብ : ታካሚዎቹ : ወዳጅ እና ጓደኞቹ ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን

የከምባታ ዞን ጤና መምሪያ  ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሐሳብ ለመንግስት ሰራተኞች የተዘጋጀውን የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት መጀመሩን ገለፀ =======================የካ...
12/02/2024

የከምባታ ዞን ጤና መምሪያ ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሐሳብ ለመንግስት ሰራተኞች የተዘጋጀውን የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት መጀመሩን ገለፀ
=======================

የካቲት 04/6/2016 ዓ.ም የከምባታ ዞን ጤና መምሪያ እንደ ሀገር ''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሐሳብ ለመንግስት ሰራተኞች የተዘጋጀውን የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመላው የመምሪያዉ ሰራተኞች በዱራሜ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።

ስልጠናዉን እየሰጡ የሚገኙት የዞኑ ጤና መምሪያ ሃላፊ የሆኑት አቶ ወንድሙ ዳንኤል ሲሆኑ በስልጠናው ላይ የተለያዩ የመወያያ ጽሑፎችን ለተሳታፊዎች ቀርበዉ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል።

በሥልጠናው ላይ በአጠቃላይ 56 የሚያህሉ መላዉ የመምሪያዉ ሰራተኞች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተገልጿል።

የከምባታ ዞን ጤና መምሪያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወላይታ ዞን ድጉና ፋንጎ ወረዳ በቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆሰፒታል አንዲት እናት ሶስት ልጆችን በአንዴ በሰላም ተገላገለች በወላይታ ዞን በድጉና ፋንጎ ወረዳ ...
12/02/2024

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወላይታ ዞን ድጉና ፋንጎ ወረዳ በቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆሰፒታል አንዲት እናት ሶስት ልጆችን በአንዴ በሰላም ተገላገለች

በወላይታ ዞን በድጉና ፋንጎ ወረዳ በብላቴ ጨርቾ ቀበሌ ዘጠኝ ቁጥር ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ፀሀይ ገበየሁ ሶስት ሜንቲያ ወንድ ልጆችን ያለምንም ጤና ችግር ሳያጋጥማት በሰላም ተገላግላለች።

የድጉና ፋንጎ ወረዳ የቢጠና መጀመሪያ ሆስፒታል ሥ/አስኪያጅ የሆኑት አቶ ጥጋቡ አዲሱ እንደገለፁት በፈጣሪ እገዛና በባለሞያዎች ጥረት ያለምንም የጤና ስህተት ሳይፈጠሪ በሰላም መገላገሏንም ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ ልጆቹና የልጆች እናት ፍፁም ጤነኛ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ከቢላቴ ጫርቾ ቀበሌ ወደ #ቢጠና መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከዲምቱ ጤ/ጣቢያ በሪፌር የመጣች እናት ሶስት ህፃናትን በከፍተኛ ባለሙያዎች እገዛ በሰላም መገላገሏን እና ሦስቱም ህፃን በመለካም ጤንነት ላይ ሲገኙ በጽኑ ጨቅላ ህጻናት እንክብካቤ ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ።

የተወለዱ ጨቅላ ሕፃናት ክብደታቸው በቅድመ ተከተል አንደኛው 2000 ግራም፣ ሁለተኛው 1600 ግራም እና ሦስተኛው 1600 ግራም መሆኑንም ተቁሟል ።

የሶስት ልጆች እናት ወ/ሮ ፀሀይ ገብየሁ ሶስት ወንድ ልጆችን በሰላም መገላገሏን ፈጣሪን አመሰግናለች።

እናትየውም ቤተሰቦቿም ጭምር በጤና ባለሙያዎች በተደረገላቸው እንክብካቤ እና አገልግሎት እጅግ መደሰታቸውን የወረዳው ሕዝብ ኮሙዩኒኬሽን መረጃው ይጠቁማል ።

Address

Hawassa
149

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:00
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251462206334

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SNNPR Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to SNNPR Health Bureau:

Share