Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone.

Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone. የአንሌሞ ወረዳ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ማህበረዊ ሚዲያ
Anlemo Woreda Government Communication Affairs Office in Hadiya zo

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ፦***********************1. የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር፣2. የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ፣3....
29/05/2026

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ፦
***********************

1. የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር፣
2. የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ፣
3. አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ መታወቂያውን ማሳየት፣
4. የምርጫ ሕጉን ማክበር፣
5. የምርጫውን ሂደት የመከታተል ተግባሩን ሲያከናውን መራጮች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው አስተያየት ከመስጠት ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር የለበትም፣
6. የምርጫ ቁሳቁሶችን መያዝ፥ ማንሳት፤ መነካካት ወይም በቁሳቁሶቹ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ተግባራትን መፈጸም የለበትም፣
7. የምርጫ ጣቢያውን ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ከማስፈራራት ወይም ሥራውን ከሚያደናቅፉ ተግባራት መቆጠብ፣
8. ወደ ድምፅ መስጫ ክፍሎች መግባት የለበትም፣
9. ቦርዱ የሚያወጣውን የሥነ ምግባር ደንብ መፈረም እና ማክበር ይገባዋል፡፡

ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 121

ኢትዮጵያ ትመርጣለች!
29/05/2026

ኢትዮጵያ ትመርጣለች!

የፊታችን ሰኞ ግንቦት 24 ቀን ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ መደበኛ ስራ እንደማይኖር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ*****************የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምር...
27/05/2026

የፊታችን ሰኞ ግንቦት 24 ቀን ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ መደበኛ ስራ እንደማይኖር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
*****************

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊ እና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል።

በዚህም መሠረት:-

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤

- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።

- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #ኢትዮጵያ

ዜጎች ድምፅ መስጠት እንዲችሉ ለሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መደበኛ  ስራን በተመለከተ ምን የተመቻቸ ነገር አለ? #የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት፣ በፌዴራል እና በክልሎች ...
27/05/2026

ዜጎች ድምፅ መስጠት እንዲችሉ ለሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መደበኛ ስራን በተመለከተ ምን የተመቻቸ ነገር አለ?

#የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት፣ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት ዝግ ይሆናሉ።

#የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።

#የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

#

1447ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በአል በአንሌሞ ወረዳ በድምቀት ተከበረፎንቆ:-ግንቦት 19/2018(የአንሌሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሺን)1ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በ...
27/05/2026

1447ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በአል በአንሌሞ ወረዳ በድምቀት ተከበረ

ፎንቆ:-ግንቦት 19/2018(የአንሌሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሺን)

1ሺህ 447ኛው የዒድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ እስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ተከብሯል።

የአንሌሞ ወረዳ ም/ አስተዳደርና የት/መ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደገፈ ሉብሶ በበዓሉ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ለመላው የወረዳው ህዝበ ሙስሊምና ለእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በአል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

አቶ ደገፈ አክለውም ኢድ አል አድሃ (አረፋ) በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩ በዓላት ትልቅ ቦታ የሚሰጠውና በልዩ ድምቀት የሚከበር በዓል መሆኑንም አስታውሰዋል።

ኢድ አል አድሃ(አረፋ) በአለም ዙሪያ ያሉ ሙስሊሞች በተመሳሳይ እና ወጥ በሆነ ጊዜና ስርዓት የሚያከብሩት ትልቅ በዓል መሆኑንም ተናግረዋል።

ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩትን በማገዝ፣ አቅመ ደካሞችን በመርዳትና እርስ በርስ በመተሳሰብ ሊሆን ይገባል ሲሉ አቶ ደገፈ ተናግረዋል።

የዘንድሮው የኢድ አል አድሃ (አረፋ)በዓል በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ የሚከበር በመሆኑ ህዝበ ሙስሊሙ በበዓሉ አከባበር ሳይዘናጋ በምርጫው ሂደት በንቃት እንዲሳተፍና ለሀገርና ለእምነቱ የሚጠቅመውን ፓርቲ እንዲመርጥ አቶ ደገፈ አሳስበዋል።

ለበዓሉ አከባበር ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ወደ ወረዳችን የመጡ ተወላጆች የመራጭነት ከርድ በወሰዱበት ቦታ በዕለቱ በመገኘት በምርጫው እንዲሳተፉም ም/አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

በመጨረሻም በዓሉ ለመላው የወረዳችን ህዝበ ሙስሊምና በአለም ዙሪያ ለሚገኙ ሙስሊሞች በሙሉ የጤና የፍቅር የመተሳሰብና የበረካ እንዲሆን አቶ ደገፈ ሉብሶ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ጥሞና ወቅት (ከምርጫው አራት ቀናት በፊት) በጥብቅ የተከለከሉ ተግባራትምርጫ ቦርድ
26/05/2026

ጥሞና ወቅት (ከምርጫው አራት ቀናት በፊት) በጥብቅ የተከለከሉ ተግባራት

ምርጫ ቦርድ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)ለ1ሺ 447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ የመልዕክቱ ሙሉ ቃል...
26/05/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)ለ1ሺ 447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል

ለ1ሺ 447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል እንኳን በሠላም አደረሳችሁ! ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፣ እንኳን ለ1 ሺ 447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ! እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

ዒድ አል-አድሃ ሙባረክ!

በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች በድምቀት ከሚከበሩት በዓላት መካከል አንዱ የሆነዉ ፣የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል ከሃይማኖታዊ አስተምህሮቶቹ ባሻገር፣ማህበራዊ መስተጋብሮች እንዲነቃቁ፣ የመረዳዳትና የመደጋገፍ እሴቶችና ትዉፊቶች እንዲጠናከሩ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል፤ ተካፍሎ የመብላትን ፣ለተቸገሩ የመድረስን፣ የሌሎችን ችግር ለማቃለል የመነሳሳት ሥነ ልቦናን ከፍ ያደርጋል።

በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች፣በተለያዩ የሕይወት መስኮች ተሰማርተው የሚገኙ የክልላችን ተወላጆች፣ ወላጆቻቸውን፣ ቤተዘመዶቻቸውን የሚጠይቁበት፣ የሐሴትና የፍቅር መንፈስ የሚጎላበት፣ ልጆች በወላጆቻቸው ምርቃት በረከትን የሚላበሱበት፣ ተስፋቸውም የሚለመልምበት ነው _የዓረፋ በዓል።

ይህን የአብሮነትና የመደጋገፍ እሴት ሕዝበ ሙስሊሙ አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።

የዘንድሮው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል እየተከበረ የሚገኘው፣ ሀገራችን _ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ እያከናወነች በምትገኝበት እና ለድምፅ መስጫው ዕለትም በጣት የሚቆጠሩ ቀናት በቀሩበት ዋዜማ ላይ ነው።
ስለሆነም መላው ሕዝበ ሙስሊም እና መላው የክልላችን ሕዝቦች ፣ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላችሁን ከመወጣት ባሻገር፣ በድምፅ መስጫው ዕለት ማልዳችሁ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ እንድትዘጋጁ ጥሪ አቀርባለሁ !

መልካም የዒድ አል-አድሃ ( ዓረፋ ) በዓል!
አመሠግናለሁ !

"ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው፥ ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ በመጓዝ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
26/05/2026

"ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው፥ ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ በመጓዝ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለየዒድ አል አድሐ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል የእንኳ...
26/05/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለየዒድ አል አድሐ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!

ስለዒድ አል-አድሐ “ዐረፋ” በዓል ስናስብ ሦስት ነገሮች ቀድመው ይታወሱናል። መስዕዋትነት፣ መታዘዝ እና መተጋገዝ። አባት ልጁን ለመስዕዋት ያቀረበበት፤ ልጅ የአባቱን ትዕዛዝ የፈጸመበት፤ ሙስሊሞች የመተጋገዝን እሴት ለዓለም የገለጡበት በዓል ስለሆነ “ዐረፋ” በሕዝበ-ሙስሊሙ ዘንድ ትልቅ ትርጉም አለው።

እስማኤል ለነብዩ ኢብራሂም የመጀመሪያ እና ተወዳጅ ልጃቸው ነው። አላህ (ሱ.ወ.) ይሄን ተወዳጅና የመጀመሪያ ልጅ እንዲሠዉለት ሲጠይቃቸው ታዘዙ እንጂ ወደኋላ አላሉም። ለመታዘዝ የሞከሩት ነገሩ ቀላል ሆኖ አይደለም።

ልጅን ያህል ነገር መስዕዋት ማድረግ ምኑ ይቀላል? የአባትነት ስሜት ይተናነቃል። የሰይጣን ሹክሹክታ ይፈታተናል። የቤተዘመድን ወቀሳ እና የጎረቤትን አስተያየት መቋቋምም ይከብዳል። ነብዩ ኢብራሒም፥ በዚህ ሁሉ አጣብቂኝ ውስጥ አንድ ሐቅ ተገልጦላቸዋል። ከራስ ስሜት፣ ከሰው ሐሜት እና ከወዳጅ ፍላጎት የሚልቅ ታላቅ ዓላማ እንዳለ አምነዋል። ስለዚህም በፈተና ውስጥ ጸንተው ቆሙ፤ ቆራጥነታቸውም በተግባር ታየ።

ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው። የሚወዱትን ነገር እንኳን ሳይቀር ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት ሀገር ትበረታለች። እስማኤላቸውን ለመስጠት የማያመነቱ ዜጎች የሞሉባት ሀገር ጽኑ ናት።

የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም “ሀገርነት እና ሉአላዊነት” ይሰኛል። ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው። ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል ነው።

የእውነት ኢትዮጵያ ሲያልፍላት ማየት የምንሻ ከሆነ ምኞታችን በተግባር ይገለጥ። የሀገር ኩስመና ካሳሰበን ለግዝፈቷ እንድከም። ያጎበጣትን የድህነት ቋጥኝ ለመሸከም ትከሻችንን እናመቻች። ጎተራዋ እንዲሞላ እጃችን አፈር ይንካ። የጠየመ ገጽዋ እንዲፈካ በሥራ ሌት-ተቀን እንሰለፍ። የተቀማ ክብሯ እስኪመለስ ድርሻችንን እንወጣ። ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዕዋት ለመሆን አናመንታ።

የዐረፋ በዓል የመታዘዝና የመስዕዋት ብቻ ሳይሆን የመደጋገፍና የመተጋገዝ በዓል ጭምር ነው። በዐረፋ ከሚከናወነው እርድ አንድ ሦስተኛው ለምስኪኖች እንዲሰጥ የእስልምና አስተምህሮ ያዛል። በዐረፋ ሕዝበ-ሙስሊሙ ደስታና ሐዘኑን እየተጋራ በዓሉን ያከብራል።

የዐረፋ እለት አንድም ሰው ተከፍቶ አያሳልፍም፤ በዐረፋ ሰሞን ማንም ሰው ተርቦና ተጠምቶ አያድርም። በዓሉ ትርጉም የሚሰጠው ሕዝበ-ሙስሊሙ ያለውን ተካፍሎ ሲያከብረው ነው። ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታን የሚሻገሩበት መፍትሄው መተሳሰብና መተጋገዝ እንደሆነ ከዐረፋ እንማራለን። ሀገርም ከፈተናዎችዋ በላይ እንድትሆን እኒህ እሴቶች ወሳኝ ናቸው።

ዐረፋ ማኅበረሰባዊ በዓል የሚባለው ለዚህ ነው። ሰዎች በግላቸው የሚያከብሩት አይደለም። ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ሠፈሩ፣ ከተማው የሚያከብረው በዓል ነው። ያላቸውና የሌላቸው፤ የሚችሉና የማይችሉ፤ ታላላቆችና ታናናሾች፤ ባለ ሥልጣናትና ተራ ዜጎች፣ በአንድነት የሚያከብሩት በዓል ነው። ሰው የሚኖረው በቤቱ ውስጥ አይደለም። በማኅበረሰቡ ውስጥ ነው።

ማኅበረሰባዊ ትሥሥርና ትብብር ለዜጎች እና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ናቸው። ማኅበረሰባዊ ትሥሥር ስለሌሎች እንድናስብ፣ ስለሌሎች እንድንሠራ እና ስለ ሌሎች ዋጋ እንድንከፍል ያደርገናል። ራሳችንን በሌሎች ጫማ ላይ አቁመን እንድናይ ያስችለናል።

የሁላችንም ሰላም፣ የሁላችንም ደኅንነት እና የሁላችንም ጥቅም ካልተከበረ በቀር የግላችንን ብቻ ልናስከብር እንደማንችል ያስገነዝበናል። ስለዚህም ማኅበራዊ ግዴታን እንደ ዜግነት ግዴታ ወስደን እንድንሠራ ያደርገናል።

ምርጫ ማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታዎችን ከምንወጣባቸው የዴሞክራሲ መገንቢያ መሳሪያዎች መካከል ዋነኛው ነው። ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም። የዴሞክራሲያችን መሰረት ጥንካሬው የሚለካው በተሳትፎአችን መጠን ነው።

የዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓታችን የሚጠነክርበት መሰረት ነው። የዴሞክራሲ ልምምዳችን አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት፤ የቀጣይ ዓመታት የሀገራችንን እጣ-ፈንታ የምንበይንበት፤ ከምንም በላይ ብዝሃ-ድምጽ የሚሰማበት የሕግ መወሰኛ ምክርቤት የምንመሰርትበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው።

በመሆኑም በዓሉን ስናከብር ዜግነታዊ ግዴታችንን ለመወጣት ብቻ ሳይሆን በካርዳችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በድጋሚ መልካም የዐረፋ በዓል እንዲሆን እመኛለሁ!
ዒድ ሙባረክ!!
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ግንቦት 18፣ 2018 ዓ.ም

ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ምአዲስ አበባ 55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎችየሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተ...
26/05/2026

ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው ለአርብቶ አደር ምግብና የኑሮ ዘይቤ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከአፍሪካ ልማት ባንክ የአርባ ስድስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺህ (46,300,000) የአሜሪካን ዶላር ብድር ስምምነት ነው፡፡

ሁለተኛው ለስድስተኛ ምዕራፍ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር የአንድ መቶ አርባ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ (146,100,000) ኤስ ዲ አር ብድር ስምምነት ነው፡፡ ምክር ቤቱ ሁለቱም የብድር ስምምነቶች ከአገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ የብድር ስምምነት ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጆቹ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ወጥቶ ሲሰራበት የቆየ ቢሆንም ባለፉት አመታት በሀገራችን በርካታ የኢኮኖሚ ለውጦች የተደረጉ በመሆኑ የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ከዘመናዊ ዓለም አቀፍ ልምዶች ጋር ለማጣጣም፤ የታክስ አለመግባባቶችን በፍትሐዊነት፣ በሰላማዊ መንገድና በቅልጥፍና ለመፍታትና የተጠያቂነትና ግልጸኝነት አሰራር ለማስፈንና የታክስ ሕጎችን በተጠናከረ መልኩ ለማስፈጸም እንዲያስችል ተደርጎ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የግብርና ዘርፍን ከተለምዶአዊ አሰራር ወደ ቢዝነስ መር ሥርዓት ለማሸጋር፤ አነስተኛ አምራቾችን የገበያ የመደራደር አቅም ለማሳደግ፣ የእሴት ጭማሪና የኢንዱስትሪ ግብዓት ትስስርን ለመፍጠር፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ወደ መካከለኛ አልሚነት የሚደርጉትን ሽግግር በሕግ ለመደገፍ፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የሥራ ዕድል ለመፍጠር የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየበት የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ነው፡፡ የኢትዮጵያን የካርበን ገበያ ስትራቴጂ ወደ ተግባር ለመለወጥ፣ ለአረንጓዴ ኢንቨስትመንት እና ለቴክኖሎጂ ሽግግር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር፣ የካርበን ግብይት አሰራሮችንና ሂደቶችን በግልፅ ለመደንገግ፣ በካርቦን ፕሮጀክት አካባቢ በሚኖረው ማህበረሰብና አካባቢው ላይ ጉዳት እንዳይደርስ አሰራሮችን ለመዘርጋት፤ ከካርበን ንግድ የሚገኘው ገቢ በመንግስት፣ በአልሚዎች፣ በአካባቢው ማህበረሰብ እና በባለድርሻ አካላት መካከል በፍትሃዊነት የሚከፋፈልበትን አሰራር ለመዘርጋት እና ኢትዮጵያ የፈረመቻቸውን ዓለም አቀፍ ውሎችና የገባቻቸውን የሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀት ቅነሳ ቃል ኪዳኖች ከሌሎች ጋር በትብብር እንድትወጣ የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

5. የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ የተወያየበት ሌላው አጀንዳ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ሞያዊ ነፃነትን ለማረጋገጥ፣ የተቆጣጣሪ እና የፈጻሚ አካላትን የቁጥጥር እና የአሠራር ተግባራትን ሚና በግልፅ ለመለየት፣ በሁሉም ኦፊሽያል ስታቲስቲክስ አመንጪዎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር፣ የመረጃ ምስጢራዊነትን ለመጠበቅ፣ የስታቲስቲክስ ውጤቶችን ጥራት ለማሻሻል፣ ተደራሽነታቸውን ለማረጋገጥ እና ሀገራዊ አሠራሮችን ከዓለም አቀፍ የስታቲስቲክስ መርሆዎች እና ደረጃዎች ጋር ለማጣጣም እንዲያስችል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

6.አስከትሎም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢነርጂ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ፖሊሲው ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ ከአሥር አመቱ የልማት ዕቅድ፣ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ፣ ከምዕተ አመቱ የልማት ግቦች እና ከሌሎች ፖሊሲዎች ጋር ተጣጥሞ የአገራችንን የኢነርጂ ሀብት በአነስተኛ ዋጋ በማልማት ዘላቂ፣ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ በዋጋ ተመጣጣኝና ተወዳዳሪ የኢነርጂ አቅርቦት እንዲኖርና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲያስችል ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

7. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው ብሄራዊ የሴቶች ማብቃት እና የስርዓተ ጾታ እኩልነት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ፖሊሲው ለስርአተ ጾታ መዛባት ስር ነቀል የሆኑ ጉዳዮች ላይ በቂ ትኩረት ለመስጠት፣ ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በአግባቡ ለመከላከል እና ጥበቃና ምላሽ ለመስጠት፣ ልዩ ትኩረት ለሚሹ ሴት አካል ጉዳተኞች እና ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች ምላሽ ለመስጠት እንዲያስችል ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ስርአተ-ጾታን መሰረት ካደረጉ አለም አቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶች ጋር በማጣጣም ረቂቁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

8. ቀጥሎም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢንሹራንስ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የኢንሹራንስ ገበያውን ተኣማኒነት የሚያጠናክር፣ ፍትሃዊ፣ ደህንነቱ ተረጋገጠ እና የተረጋጋ የኢንሹራንስ ገበያ እንዲኖር የሚያበረታታ፣ የመድን ገቢዎችን እና የመድን አገናኞችን ደንበኞች ጥቅም የሚያስጠብቅ፣ የኢንሹራንስ ገበያውን ለመቆጣጠርና ለመምራት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

9. በማስከተል ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ የንግድ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የንግድ ስርአትን በአግባቡ ለመምራት፣ በተመረጡ የገበያ ክፍተት ባለባቸው ዘርፎች ክፍተቶችን ለመሙላት የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር፣ የሀገራችንን የወጪ ንግድ በግብርና ምርቶች ያለውን ጥገኝነት በማላቀቅ የወጪ ምርትና አገልግሎት ብዝሃነትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ፣ የምርት ደህንነት መስፈርቶችን ለማውጣት እና ፍትሃዊ የንግድ አሰራርን ለመዘርጋት፣ የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች ተወዳዳሪነትን እንዲገነቡ፣ ምርታማነትን እንዲያሳድጉና የአካባቢ አቅምን እንዲያዳብሩ ድጋፎችን በመስጠት በዘርፉ ያሉ ተግዳሮችን ለመፍታት እንዲያስችል ረቂቅ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

10. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣንን አደረጃጀት፤ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የቀረበ ማሻሻያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ባለስልጣኑ በህግ የተሰጠውን ተግባርና ሃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንዲያስችለው ማሻሻያ ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

11. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው በህግ የሰውነት መብት የተሰጣቸው አካላት ተጠቃሚ የሚሆኑ ባለቤቶችን መረጃ ግልጸኝነት ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ በአግባቡ ለማስፈጸም እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

12. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የምግብ ስርዓት እና ስርዓተ ምግብ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ከሥርዓተ ምግብ መዛባት ጋር የተያያዙ በሽታዎች በጤና፣ በትምህርት፣ በአካባቢያዊ፣ በምርታማነትና በማህበራዊ መስተጋብር እና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድሩትን አሉታዊ ተጽእኖ ለመቀነስና ለማጥፋት የሚያስችሉ ተግባራትን ለማከናወን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ይህን ስራ የሚያስተባብር አደረጃጀት ለመፍጠር፤ ሀብት በዘላቂነት ለመመደብና የማህበረሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ሀገራችን የገባቻቸውን አለም አቀፍ ስምምነቶችና የተቀመጡ የምግብ ስርዓትና ሥርዓተ ምግብ ግቦችን ለማሳካት የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

13. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ አፈጻጸምን ለመደንገግ በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስት የሚሰጥ የበጀት ድጋፍ በታወቀ ጥቅል የበጀት ድጋፍ ስርዓት ላይ የተመሰረተ ለማድረግ፣ የፋይናንስ ተጠያቂነት፣ ፍትሃዊነት እና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ፣ የራስን ወጪ በራስ የመሸፈን ድርሻን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለማሳደግ፣ በተቋማቱ መካከል ተመጣጣኝ የመማር-ማስተማር፣ የአገልግሎት ጥራት እና ፍትሃዊነትን ባረጋገጠ ሁኔታ ሀላፊነት የተሞላበት ስራዎችን እንዲያከናውኑ ለማስቻል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
//

በአንሌሞ ወረዳ አጠቃለይ ወቅታዊ የምርጫ ተግባራት አፈጻጸም ተገመገመፎንቆ:- ግንቦት 17/2018 (የአንሌሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሺን )በአንሌሞ ወረዳ አጠቃለይ ወቅታዊ  የምርጫ ዝግጅት ተ...
25/05/2026

በአንሌሞ ወረዳ አጠቃለይ ወቅታዊ የምርጫ ተግባራት አፈጻጸም ተገመገመ

ፎንቆ:- ግንቦት 17/2018 (የአንሌሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሺን )

በአንሌሞ ወረዳ አጠቃለይ ወቅታዊ የምርጫ ዝግጅት ተግባራት ደርሶ ያለበት ደረጀ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የግምገማ መድረክ ተካሄዷል።

መድረኩን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ምክትል/ዋና ዳይሬክተር አቶ ከይረዲን ራመቶ እና የአንሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ዮሐንስ አበጋ በጋራ የመሩት ሲሆን የዞን ደጋፊ አመራር ፣የወረዳው አስተባባሪዎችና አመራር ፑል ተገኝተዋል።

በመድረኩ ቀጣዩን 7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሥራዎችን በተመለከተ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አፈጻጸም በዝርዝር ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

በመድረኩ የተገኙት ባለድርሻ አካላት ሀገራዊ የምርጫ ሥራውን ስኬታማ ለማድረግ የምርጫ ቦርዱን የምርጫ ህግና የፓርቲውን የምርጫ ማስፈጸሚያ መመሪያ በጠበቀ መልኩ የነበረውን ቁርጠኝነት በማስቀጠል መስራት እንደሚገባ ተግባቦት ተፈጥሮ መድረኩ ተጠናቋል ።

#የአንሌሞ ወረዳ ብ/ፓርቲ ኮሙኒኬሺን #

Address

Hosanna

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone.:

Share