Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone.

Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone. የአንሌሞ ወረዳ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ማህበረዊ ሚዲያ
Anlemo Woreda Government Communication Affairs Office in Hadiya zo

ያሆዴ ከዘመን መለወጫ በዓልነት ባሻገር የማህበራዊ ካፒታል፣ የሰላምና የባህላዊ ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑ ተገለጸፎንቆ:- ነሓሴ 24/2018 (የአንሌሞ ወረዳ ኮሙኒኬሺን)የሀድያ ብሔር የዘመን መለ...
30/08/2026

ያሆዴ ከዘመን መለወጫ በዓልነት ባሻገር የማህበራዊ ካፒታል፣ የሰላምና የባህላዊ ኢኮኖሚ መሠረት መሆኑ ተገለጸ

ፎንቆ:- ነሓሴ 24/2018 (የአንሌሞ ወረዳ ኮሙኒኬሺን)

የሀድያ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ያሆዴ የማህበረሰቡን ማህበራዊ ካፒታል ጠብቆ ለማቆየት፣ ሰላምና እርቅን ለማስፈን እንዲሁም ባህላዊ እሴቶችን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ የጎላ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝ ተገለጸ።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም «ያሆዴ የሀድያ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል» መጽሐፍ አዘጋጆች አንዱ የሆኑት መምህር መለሰ አቢዴ ከሀድያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በዓሉ በዘመናዊነትና በለውጥ ሂደት ውስጥ በሚገኝ ማህበረሰብ ውስጥ ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።

መምህር መለሰ እንዳብራሩት፤ ያሆዴ ሰዎች በጋራ እንዲሰበሰቡ፣ እንዲገናኙና እንዲጠያየቁ በማድረግ የመረዳዳትና የመተማመን እሴቶችን ያስቀጥላል።

ይህም ሃይማኖት፣ ዘመናዊነትና ስደት በባህል ላይ የሚያመጡትን ተጽዕኖ በመቋቋም ማህበራዊ ካፒታሉ ሳይሸረሸር እንዲጸና እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

ባህል የአንድ ማህበረሰብ የማንነት መገለጫ መሆኑን ያነሱት ተመራማሪው፤ ያሆዴ ለአዲሱ ትውልድ «እኛ ማን ነን?» የሚለውን የማንነት ጥያቄ በተግባር የሚመልስና ባህል፣ ቋንቋ፣ ልማድና ታሪክ የሚገለጽበት ትልቅ የትምህርት መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል።

በዓሉ ከተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር ያለውን ማህበራዊ መስተጋብር በማጠናከር ረገድ ስላለው ፋይዳ ሲያብራሩም፤ በያሆዴ ላይ አጎራባች ብሔረሰቦች መሳተፋቸው የተሳሳቱ ግንዛቤዎችን በመቀነስ የመከባበር፣ የሰላምና የማህበራዊ ውህደት መድረክ እንዲሆን ማስቻሉን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ያሆዴ የእርቅና የስነ-ልቦና እፎይታ የሚገኝበት መሆኑን የጠቀሱት መምህር መለሰ፤ ተጣልተው የቆዩ ወገኖችና በተለይም የተፋቱ ባልና ሚስት ተመልሰው የሚገናኙበት መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ መምህር መለሰ ማብራሪያ፤ በበዓሉ ወቅት የሚተገበረው ባህላዊ የማህበረሰብ እርቅ ጥፋተኛውን በማግለልና በመቅጣት ፋንታ በምክርና በይቅርታ ወደ ማህበረሰቡ በመመለስ የሰዎችን የስነ-ልቦና እርካታና ማህበራዊ መረጋጋት የሚያረጋግጥ ነው።

በዓሉ በሚከበርበት ወቅት የገንዘብም ሆነ የዕቃ ዱቤ ወይም ብድር (Aabba) ሙሉ በሙሉ እንዲከፈል የሚደረግበት ባህላዊ መመሪያ መኖሩን ተናግረዋል።

ይህም ዕዳ ለቀጣይ ዓመት እንዳይሸጋገር በማድረግ በማህበረሰቡ መካከል የቃል ኪዳን ታማኝነትንና የንግድ ኃላፊነትን ያጠናክራል።

በሌላ በኩል በበዓሉ ወቅት የሚቀርቡ የዕደ-ጥበብ ውጤቶች፣ ባህላዊ አልባሳትና የኪነ-ጥበብ ዝግጅቶች ባህሉ እንዳይጠፋ ከማድረግ ባሻገር ለአካባቢው አምራቾችና አርቲስቶች የገቢ እድል በመፍጠር ለባህላዊ ኢኮኖሚው እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አብራርተዋል።

በመጨረሻም ያሆዴ «ምንም ለሌለው የሚሰጥበትና ሰዎች በእኩልነት የሚያከብሩት» መሆኑን የገለጹት መምህር መለሰ አቢዴ፤ ሀብት ያለውና የሌለው በእኩል የሚስተናገዱበት፣ ከሰው ባሻገር የቤት እንስሳት እንኳ የሚንከባከቡበት የደግነትና የተካፋይነት በዓል መሆኑን አብራርተዋል።

በስራና በስደት ርቀው የቆዩ የቤተሰብ አባላት ተገናኝተው የጋራ ትውስታቸውን የሚያድሱበት፣ ወጣቶችም ጥንድ የሚሆኑበትና የመተጫጨት እድል የሚያገኙበት ትልቅ ማህበራዊ ተቋም መሆኑን አብራርተዋል።

በመሆኑም ወጣቶች እሴቶቹን የባህሉን ቀጣይነት ማረጋገጥ እንዳለባቸው ተናግረዋል።

#ሀዲያ ቴሌቬዥን #

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 590.08 ውጤት ያስመዘገበው ሌላኛው የኢትዮጵያ ተስፋ - ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ***** በአንድ ሀገር የዕድገት ጉዞ ውስጥ ትልቁ ካፒታል የነገን ራዕይ ሰንቀ...
29/08/2026

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 590.08 ውጤት ያስመዘገበው ሌላኛው የኢትዮጵያ ተስፋ - ተማሪ ሮቤል ጌታቸው
*****

በአንድ ሀገር የዕድገት ጉዞ ውስጥ ትልቁ ካፒታል የነገን ራዕይ ሰንቀው የሚነሡ ምጡቅ አዕምሮ ያላቸው ወጣቶች ናቸው።

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሲገለጽም፣ ኢትዮጵያ መፃኢ ጊዜዋን በልበ ሙሉነት ልታስረክባቸው የምትችላቸውን ብሩህ ተስፋዎች ተመልክታለች።

ከእነዚህ ሀገር አኩሪ ኮከቦች መካከል ደግሞ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ሀድያ ዞን፣ ሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው ሮቤል ጌታቸው አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል።

በሀገር አቀፍ ፈተናው ከፍተኛው ውጤት 591.6 ሆኖ በተመዘገበበት በዚህ ዓመት፣ ተማሪ ሮቤል ከ600 ውስጥ 590.08 ውጤት በማስመዝገብ በሀገር ደረጃ ሁለተኛውን ከፍተኛ ደረጃ ተቆናጥጧል።

ይህ አኩሪ ስኬት በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን በዓላማ፣ በጠንካራ የጥናት ስልት እና በማያወላውል ትኩረት የተገነባ፣ የለፋበትን እና የደከመበትን እልህ አስጨራሽ ጉዞ የሚያሳይ የድካም ፍሬ ነው።

የሮቤል ስኬት ከኋላው ብዙ የሚነገሩ ትምህርት ሰጪ ታሪኮች አሉት። ይህም የንባብ ጊዜውን በከፍተኛ ትኩረት ማሳለፍ፣ ማስታወሻ የመያዝ እና በርካታ ጥያቄዎችን የመሥራት የዳበረ ልምድ ያለው መሆኑ ነው።

ሮቤል ለ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የተዘጋጀበት መንገድ ውጤታማ እንዳደረገው ይናገራል። ከምንም በላይ ደግሞ ለደረሰበት ከፍታ የወላጆቹ ዐሻራ ጎልቶ ይታያል። እናት እና አባቱ መምህራን መሆናቸውን እና እነሱ በትምህርት ዘርፍ ውስጥ መሆናቸው እርሱም ሙሉ ትኩረቱን ትምህርቱ ላይ እንዲያደርግ አስችሎታል።

የምናልመው ነገር ትልቅ ከሆነ የሚመጣው ውጤትም በተመሳሳይ ከፍተኛ እንደሚሆን ጽኑ እምነት አለው፤ ይህንንም በተግባር አሳይቷል።

በዚህ አስደናቂ ውጤቱ ምክንያት የክልሉ መንግሥት እና የትምህርት ቢሮ ከፍተኛ ኩራት እንደተሰማቸው በመግለጽ፣ ልዩ የማበረታቻ ሽልማት አበርክተውለታል።

ሮቤል ጌታቸው፣ ቀጣይ ጉዞው ሰማየ ሰማያትን ሰንጥቆ መብረር ነው። ከልጅነቱ ጀምሮ በልቡ ያሳደገውን የአውሮፕላን አብራሪነት (ፓይለት) ሕልሙን እውን በማድረግ፣ በአቪዬሽኑ ዘርፍ ጥሩ ቦታ የመድረስ ጽኑ ራዕይ እንዳለው አጽንኦት ሰጥቶ ይናገራል።

በእርግጥም የሮቤል ታሪክ የውጤት ብቻ ሳይሆን፣ የትልቅ ሕልም፣ የዓላማ ጽናት፣ እና የትኩረት ማሳያ ነው። እሱ ለትውልዱ አብነት፣ ለሀገሩም ሌላኛው ብሩህ ተስፋ ነው!

በዮናስ በድሉ

#

በአንሌሞ ወረዳ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ  አገልግሎት ተግባራት በሁሉም ዘርፎች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።ፎንቆ:- ነሐሴ  21/2018 (የአንሌሞ ወረዳ ኮሙኒኬሺን) በሀዲያ ዞን በአንሌሞ ወ...
27/08/2026

በአንሌሞ ወረዳ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በሁሉም ዘርፎች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ፎንቆ:- ነሐሴ 21/2018 (የአንሌሞ ወረዳ ኮሙኒኬሺን)

በሀዲያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ በሆማ አገራ ቀበሌ ለይ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ይህ የበጎ አድራጎት በፎንቆ መጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት አጋርነት አቅመ ደከመ ለሆነችው ለወ/ሮ ቡዙነሽ በየነ የ40 ቅጠል ቆርቆሮ ቤት የሁለቱም ቀበሌ ወጣቶች አደረጃጀት እንድሁም የበጎ ተግባር አርበኛ የሆኑት የከቤቾ ከተማ መቴዮማ ማህበር እና የአከባቢው ማህበረሰብ ሁሉም አንድ ላይ በመሆን ሥራውን እያካሄዱ ይገኛል።

በማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ለይ የተገኙት የአንሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ኢያሱ ኤርዳዶ በቦታው ላይ በመገኛት ወጣቶችን አበረታትተዋል።

የእንስሳትን ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት የማይተካ ሚና ነው፦ ዶ/ር  ሀብታሙ ታደሰሆሳዕና ነሐሴ 15/2018 ዓ/ም (የሀዲያ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ)በሀዲያ ዞን...
21/08/2026

የእንስሳትን ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት የማይተካ ሚና ነው፦ ዶ/ር ሀብታሙ ታደሰ

ሆሳዕና ነሐሴ 15/2018 ዓ/ም (የሀዲያ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ)

በሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ የእንስሳትና አሳ ሀብት ልማት ዘርፍ የ2018 አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ ውይይት አካሂዷል።

ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ የቀረበ ሲሆን ሰነዱም የእንስሳት ሀብት ምርታማነትን ለማሳደግ በ2018 የተከናወኑ ተግባራት እና የተገኘው ውጤት ቀርቧል።

በተሰሩ ሥራዎች የወተት፣ የእንቁላል እና የማር ምርት አቅርቦት መጨመሩንና መሻሻል የተስተዋለ መሆኑ ተገልጿል። ከዚህ በፊት ከሌላ አከባቢ ይገባ የነበረው የአንድ ቀን ጫጩት ማሟላት መቻሉንም ጠቁመዋል።

ዘመናዊ የእርባታ ቤት አሰራር እና የምርጥ መኖ አቅርቦት ላይ መሻሻል እንደሚያስፈልግ አንስተው በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግም ተነስቷል።

የሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ታደሰ እንደገለፁት የእንስሳትና አሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሰራቸው ሥራዎች የሌማት ትሩፋት ላይ የተሻለ ውጤት የተመዘገበበትና ተጨባጭ ለውጥ የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።

የግብርና ተቋም የዜጎችን ፍላጎት ለማሟላት ዋና ዋና ተግባራት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ሲሆን የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ ትልቁን ድርሻ የሚወስድ መሆኑንም ጠቁመዋል።

አያይዘውም ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ ከሚያከናውናቸው ተግባራት ውስጥ

👉 በማህበረሰብ ደረጃ የምግብና ሥነ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ።
👉 የገቢ ምርትን መተካትና የወጪ ምርትን በአይነትና በጥራት ማሳደግ።
👉 የሥራ ዕድል መፍጠር።
👉 የግብርና ግብአትን ለኢንዱስትሪዎች ማቅረብ።
👉 የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥና ድህነትን ማሸነፍ ላይ ዓላማ አድርጎ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።

ተሳታፊዎችም በቀረበው ሪፖርት የታዩትን ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል የተስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረምና በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው የሚሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በመጨረሻም የሚሰሩ ሥራዎች ላይ የተሻለ ውጤት ለማምጣት በቅንጅት፣ በትጋትና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚያስፈልግ መልዕክት ተላልፏል።

#ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሺን.

በአንሌሞ ወረዳ የገበያ ቦታዎችን ከህገወጥ የመሬት ወረራ መከላከልና ማረጋገጫ ሰነድ እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ እንደቀጠለ ነው።ፎንቆ:-ነሓሴ 13/2018 (የአንሌሞ ወረዳ ኮሙኒኬሺን)በማዕከላዊ...
19/08/2026

በአንሌሞ ወረዳ የገበያ ቦታዎችን ከህገወጥ የመሬት ወረራ መከላከልና ማረጋገጫ ሰነድ እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ እንደቀጠለ ነው።

ፎንቆ:-ነሓሴ 13/2018 (የአንሌሞ ወረዳ ኮሙኒኬሺን)

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ የገበያ ቦታዎችን ከህገወጥ የመሬት ወረራ መከላከልና ማረጋገጫ ሰነድ እንዲኖራቸው የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በየአከባቢው አርሶ አደሩ ከተግባር ሳይነጠልና ለትራንስፖርት ወጪ ሳይዳረግ በቅርበት እንዲገበያይ የገበያ መሰረተ ልማትን ማጠናከር እና ማስፋፋት እንደሚገባ የወረዳው ን/ገ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አቤል ሙጎሮ ገልጸዋል።

ጽ/ቤቱ ይህንን ሥራ ከወረዳው መሬት አስ/አጠ/ጽ/ቤት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንዳለ ጠቅሰው ተግባሩ ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሆም ገልጸዋል።

በዛሬው ዕለትም በዳርሻ ክላስተር በምሥ/ኣና ሌሞና በምዕ/ሆማ ቀበሌያት ላይ የሚገኘውን የጌሮ እና የግዶ የዘልማድ ገበያ ቦታዎችን ህጋዊ ማረጋገጫ እንድያገኙ ለማድረግ የልኬት ስራው መሠራቱንገልጸው በወረዳው በሌሎች አከባቢዎች የምገኙ የዘልማድ ገበያ ቦታዎችን በቀጣይ ቀናት ውስጥ ህጋዊ የሰነድ ማረጋገጫ እንድያገኙ ለማድረግም ጽ/ቤቱ በትኩረት ይሠራል ብለዋል።

Address

Hosanna

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Anlemo Woreda Government Communication affairs Office in Hadiy zone.:

Shortcuts

Share