ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ

ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ " ሁሉም ሰው የሚታወቅባት ኢትዮጵያ ! Ethiopia, Where Everyone Recognized !" አድራሻ፡-ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር ፅ/ቤት

🚨 ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት!የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ «ሁሉ ሰው የሚታወቅባት ኢትዮጵያን» እውን ለ...
03/09/2026

🚨 ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ «ሁሉ ሰው የሚታወቅባት ኢትዮጵያን» እውን ለማድረግ ዘርፈ-ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ኤጀንሲያችን የልደት፣ የሞት፣ የጋብቻ፣ የፍቺ እና የጉድፈቻ የምስክር ወረቀቶችን ከመስጠት ባለፈ፣ ወደ ውጭ አገር ለሚሄዱ ዜጎች በልደት የምስክር ወረቀታቸው ላይ የማረጋገጥ አገልግሎት ከሐምሌ 20 ቀን ጀምሮ በክልል ደረጃ እየሰጠ ይገኛል።

ሆኖም በሚከተሉት ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ላይ ጥንቃቄ እንዲደረግ እናሳስባለን፡

* ከመንግሥት የክፍያ ደንብ ውጭ ተጨማሪ ገንዘብ ማስከፈል እና ሕጋዊ ደረሰኝ አለመስጠት፤
* "የምስክር ወረቀት አልቋል" በማለት ተገልጋዮችን ወደ ሕገ-ወጥ መንገድ መምራት፤
* ሀሰተኛ ማኅተምና የባለሙያዎች ስም ያለበት ቲተር በማስቀረጽ ሕገ-ወጥ የማረጋገጥ ሥራ መሥራት፤
* "የዲጂታል መታወቂያ እንሰጣለን / እንለውጣለን" በማለት ሀሰተኛ ወይም የሌላ አሻራ ያለበትን ለውጦ ማዘጋጀት።

እነዚህን ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ሲፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በኅብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ሥር እየዋሉ ይገኛሉ።

📌 መልዕክታችን፡
ኅብረተሰቡ ከነዚህ አጭበርባሪዎች እራሱን እንዲጠብቅና የሚፈልገውን አገልግሎት ከሕጋዊ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ብቻ እንዲያገኝ እያሳሰብን፤ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙም ለሕግ አስከባሪ አካላት ጥቆማ እንድትሰጡ እንጠይቃለን።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ

በእምድብር ከተማ አስተዳደር ለአንድ አቅመ-ደካማ ቤተሰብ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ መኖሪያ ቤት ተመረቀነሐሴ 26/2018 ዓ.ም  ሆሳዕና "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ...
01/09/2026

በእምድብር ከተማ አስተዳደር ለአንድ አቅመ-ደካማ ቤተሰብ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ መኖሪያ ቤት ተመረቀ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም ሆሳዕና "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሚካሄደው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በጉራጌ ዞን በእምድብር ከተማ ለአንድ አቅመ-ደካማ ቤተሰብ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ መኖሪያ ቤት ተጠናቆ የቁልፍ ርክክብ ተደረገ።
ግንባታው በክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ እና በአመራር አካዳሚ አመራሮችና ሠራተኞች የተቀናጀ ጥረት የተካሄደ ሲሆን፤ ለቤቱ ግንባታ እንዲሁም እንደ አልጋ፣ ፍራሽ፣ ሶፋ እና የምግብ ማብሰያ ላሉ የቤት ውስጥ ቁሳቁሶች ማሟያ አጠቃላይ ከአንድ ሚሊዮን ክብር በላይ ወጪ መደረጉ ተገልጿል።
በስነ ስርዓቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእምድብር ከተማ አስተዳደር ምክትል ሀላፊና የፋይናንስ ሀላፊ የነበሩት አቶ ምትኩ ዘርጋ ስለተደረገው በጎ አገለግሎት ፓርቲውንና የሁለቱ የክልል ተቋማት አመስግነዋል ።
በመቀጠልም በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አበበ ከበደ እንደተናገሩት፤ በጎነት ለአቅመ-ደካሞች የሚደረግ ቅዱስ ተግባር እንደሆነ ገልጸዋል ።

አክለውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት ይህ መልካም ተግባር ብልጽግና ፓርቲ ሰው-ተኮር መሆኑን የሚያሳይ በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ አጠናክሮ የዘወትር ባህሉ ሊያደርገው እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመቀጠልም የክልሉ አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብላቱ በበኩላቸው፤ በጎነት ከበጎ አዕምሮ የሚመነጭ ተግባር እንደሆነ በመግለጽ ይህ በክልሉ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አገነባቡ ከተያዙ ከ52 ቤቶች ውስጥ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል ።

የመኖሪያ ቤት ድጋፍ የተደረገላቸው ቤተሰቦች ከዚህ ቀደም በክረምት ወቅት በጎርፍ ይቸገሩ እንደነበር አስታውሰው፤ የተደረገላቸው ድጋፍ የነበረባቸውን ችግር የቀረፈና የመኖር ተስፋቸውን ያላመለመ መሆኑን በማንሳት ላበረከቱላቸው አመራሮችና ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዚሁ የቁልፍ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የክልሉ የሁለቱ ተቋማት አመራሮች፣ የጉራጌ ዞንና የእምድብር ከተማ የመንግሥትና የፓርቲ አመራሮች፣ ሠራተኞች እንዲሁም የአገር ሽማግሌዎች መገኘታቸው ተጠቅሷል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፈጣንና ጥራት ያለው የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ሆሳዕናበአፍሪካ ለ9ኛ፣ በኢትዮ...
28/08/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፈጣንና ጥራት ያለው የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
ሆሳዕና

በአፍሪካ ለ9ኛ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለተመሳሳይ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም አቀፍ የወሳኝ ኩነቶች ቀን ምክንያት በማድረግ፣ ፈጣንና ጥራት ያለው የሲቪል ምዝገባ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራ ተገልጿል ።

በመድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የኤጀንሲው ምክትል ዳይሬክተር አቶ በድሩ ሀሰን፤ ኤጀንሲው የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና አሰራሩን ለማቀላጠፍ ዘርፈ-ብዙ ተግባራትን በቁርጠኝነት በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ተነግሯል ።

የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠልም የተቀናጀ አሰራርን ማጠናከርና የተጀመሩ ስራዎችን ከግብ ማድረስ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተው አንስተዋል ።

በበዓሉ አከባበር ወቅት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ጽንሰ-ሐሳብና ጠቀሜታን የተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ የቀረበ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ከአለም አቀፍ ልምዶች በመነሳት በ2030 የሲቪል እና የቤተሰብ ኩነቶች ምዝገባ ሽፋንን 100 በመቶ ለማድረስ ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ተመልክቷል።

አገልግሎቱን ዘመናዊና የተቀላጠፈ በማድረግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ ተመልክቷል። ለዚህም እንደ አጋዥ መሳሪያ ይሆን ዘንድ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌያትና ሆስፒታሎች የታብሌት ስርጭት ተደራሽ መደረጉ ተጠቅሷል።

በቀጣይም ህብረተሰቡ የልደት፣ የጋብቻ፣ የፍቺና የሞት ኩነቶችን ህጉ በሚያዘው ጊዜ ገደብ ውስጥ የማስመዝገብ ባህሉን እንዲያሳድግና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ቅንጅት ተጠናክሮ የዲጂታላይዜሽን ስራው ስኬታማ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ ተመላክቷል።

28/08/2026
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የ2019 በጀት ዓመት የግብ ስምምነት ተፈረመነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ሆሳዕና  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወ...
20/08/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የ2019 በጀት ዓመት የግብ ስምምነት ተፈረመ
ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም ሆሳዕና
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባን በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የ2019 በጀት ዓመት የግብ ስምምነት ተፈራርሟል ።

የክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ የግብ ስምምነቱን የተፈራረመው ከዞኖችና ልዩ ወረዳዎች የሰላም እና ፀጥታ መዋቅሮች ጋር በሀላባ ዞን ቁልቶ ከተማ ባካሄደው ጉባኤ መሆኑ ተገልጿል ።

ምዝገባው የዜጎችን መብት ለማስከበር፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመረጃ ላይ ተመስርቶ ለመቅረጽ፣ እንዲሁም የሴቶችንና ሕፃናትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል ።

በቀጣይ በአምስቱም የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ የታቀዱ ግቦችን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የአመራሩ፣ የባለሙያው እና የባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎና ኃላፊነት መወጣት ወሳኝ መሆኑ በስምምነቱ ወቅት ተመላክቷል።

የ2018 በጀት ዓመት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አፈጻጸም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮችና ሆስፒታሎች የዕውቅና ሽልማት ተበረከተነሐሴ 14/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
20/08/2026

የ2018 በጀት ዓመት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አፈጻጸም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮችና ሆስፒታሎች የዕውቅና ሽልማት ተበረከተ

ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና)

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ በ2018 በጀት ዓመት በወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ከፍተኛና አርአያነት ያለው አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዞን፣ የልዩ ወረዳ የሠላምና ፀጥታ መምሪያ/ጽ/ቤቶችና ሆስፒታሎች የዕውቅና ሽልማት አበረከተ።

የኤጀንሲው ዓመታዊ የአፈጻጸም ግምገማ እንደሚያመላክተው፣ በዞኖችና በልዩ ወረዳዎች ደረጃ በተከናወነው የጋብቻ ምዝገባ የተሻለ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን፣ በተለይም በወቅታዊና በዘገየ የጋብቻ ምዝገባ ከ50 በመቶ በላይ አፈጻጸም በማስመዝገብ ግንባር ቀደም መሆናቸውን ገልጸዋል ።

በሌላ በኩል የነባር ጋብቻ ምዝገባን በማጠናከርና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የፍቺ ምዝገባ አፈጻጸምን ከ100 በመቶ በላይ ማድረስ የተቻለበት አሰራር በክልል ደረጃ በጥሩ ተሞክሮነት ተጠቅሷል።

በተጨማሪም በወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ፣ በተለይም በልደትና በሞት ኩነቶች ምዝገባ ላይ አበረታች ውጤት ያስመዘገቡ ሆስፒታሎች የሽልማቱ አካል መሆናቸው በበጎ ተሞክሮነት ተወስዷል።

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ከሚሰጠው ሀገራዊ ፈይዳና ጠቀሜታ አኳያ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መጠናከር እንደሚገባው ተገለጸ(ሆሳዕና፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ...
20/08/2026

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ከሚሰጠው ሀገራዊ ፈይዳና ጠቀሜታ አኳያ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መጠናከር እንደሚገባው ተገለጸ

(ሆሳዕና፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ከተጠሪ ተቋማት፣ ከባለድርሻ አካላትና ከስር መዋቅሮች ጋር በ2018 አፈጻጸም እና በ2019 ዕቅድ ላይ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አበበ ከበደ እንደተናገሩት፤ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ከሚሰጠው ሀገራዊ ፈይዳና ጠቀሜታ አኳያ የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን በማጠናከር እየተሠራ ነው ብለዋል።

ኤጀንሲው የዜጎችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ለማረጋገጥ፣ ለአገራዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ዕቅዶች ትክክለኛ መረጃን በማቅረብ፣ እንዲሁም «እያንዳንዱ ሰው የሚታወቅባት ኢትዮጵያን» ለመገንባት እየሠራ ይገኛል ብለዋል።

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ሽፋኑን ለማሳደግ በክልሉ በሚገኙ 7 ዞኖች እና 3 ልዩ ወረዳዎች ከሚገኙ 1,278 የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች መካከል በ1,259 ቀበሌዎች ምዝገባው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ በሁሉም ኩነቶች 155,562 ምዝገባ የተከናወነ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ ልደት 140,280፣ ሞት 5,708፣ ጋብቻ 8,932፣ ፍቺ 628 እና ጉድፈቻ 14 ተመዝግቧል። ከነዚህም ውስጥ 10,572 ኩነቶች በታብሌት የተመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የምዝገባ አፈጻጸምና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ አበረታች ውጤቶች የተመዘገቡበት መሆኑን የተናገሩት አቶ አበበ፤ የክረምት የተማሪዎች ልደት ምዝገባ በስኬት መከናወኑን ጠቅሰዋል።

በክልሉ ውስጥ በሚገኙ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስርጭቶች፣ እንዲሁም በሕትመት ውጤቶች ወቅታዊ መልዕክቶችን በማስተላለፍ የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

በዲጂታላይዜሽንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ በተሠሩ ሥራዎች በሁሉም ዞኖች፣ ልዩ ወረዳዎችና ሆስፒታሎች የታብሌት ምዝገባ ሂደት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረው፤ በቀበሌዎች አገልግሎት ፈላጊዎችን የፋይዳ መታወቂያ የመጠየቅ ባህል መዳበሩ ትልቅ እምርታ ማምጣቱን አመላክተዋል።

የክብር መዝገብ ሹሞች ሥራውን እንደ ተደራቢ ተግባር ማየት እና አገልግሎቱን በሳምንት የተወሰኑ ቀናት ብቻ መስጠታቸው ደግሞ አሁንም እንቅፋት መሆኑን አቶ አበበ ተናግረዋል።

ከአሰራር ውጪ ከአገልግሎት ፈላጊ ዜጎች ተጨማሪ ክፍያ በሚጠይቁና ከደላላ ጋር በመመሳጠር ገንዘብ በመጠየቅ የተሳተፉ 31 የክብር መዝገብ ሹሞችና ተጠራጣሪዎችን በሕግ የማስጠየቅ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ በሁሉም ኩነቶች ወቅታዊና የዘገየ የምዝገባ ሽፋንን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚሠራ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ በልዩ ልዩ ምክንያት ምዝገባ ያቋረጡ ቀበሌዎች ወደ ምዝገባ ሥራ እንዲመለሱ ማድረግ፣ የታብሌት ምዝገባን በሁሉም መዋቅሮች ማጠናከር እና የመዝጋቢዎችን የክህሎት ክፍተት መሙላት ተጠናክሮ እንደሚሠራ ተናግረዋል።

መድረኩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል፣ ያጋጠሙ ማነቆዎችን እና በቀጣይ ትኩረት የሚሰጥባቸው ተግባራት ዙሪያ በመምከር መግባባት የሚደረስበት ነው ብለዋል።

የክልሉ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የሕግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ተወካይ አቶ ግርማ ጊቻሞ በበኩላቸው፤ ሁሉም ሰው የሚታወቅባትን ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ ራዕይ ተሰንቆ እየተሠራ ያለ በመሆኑ፣ ይህንን በሚመጥን ልክ መፈጸም ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል።

ተቋሙ በርካታ ጠንካራ ጎኖች ያሉት ቢሆንም አሁንም የሚስተዋሉ ውስንነቶችን መቅረፍ እንደሚገባውና ምዝገባው በማይከናወንባቸው አካባቢዎች ምዝገባውን በማስጀመር ለዜጎች አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ኤጀንሲው በ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተሠራ ያለውን ሥራ የሚመጥን የቴክኖሎጂ አሰራር ስርዓት በመዘርጋት ኪራይ ሰብሳቢነትን በተገቢው መከላከል እንደሚገባውም ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልል ቢሮ ኃላፊዎች፣ የዞንና ልዩ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የዕድሮች ጥምረት፣ የሆስፒታል ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወራት የሥራ አፈጻጸምና ድጋፋዊ ክትትል ሪፖርት ግምገማ መድረክ ማካሄድ  ጀመረ።ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም...
20/08/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወራት የሥራ አፈጻጸምና ድጋፋዊ ክትትል ሪፖርት ግምገማ መድረክ ማካሄድ ጀመረ።
ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም
ሆሳዕና

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አበበ ከበደ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ በክልሉ ባሉ 7 ዞኖች እና 3 ልዩ ወረዳዎች በተካሄደው ድጋፋዊ ክትትል በሁሉም የኩነት ዓይነቶች፣ በዲጂታላይዜሽን እና በግንዛቤ ፈጠራ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል ።

ከዚሁ ጎን ለጎን በሞትና ጋብቻ ምዝገባ አፈጻጸም፣ በታብሌትና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ቅንጅት ጋር ተያይዞ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት በ2019 በጀት ዓመት የዜጎችን የምዝገባ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል ።

በተጨማሪም አሠራርን ከብልሹ አሠራር ለማፅዳት በተደረገ እንቅስቃሴ አጠራጣሪ ሰነዶች ተይዘው ማጣራት እየተደረገባቸው እንደሚገኝና ጥፋት በፈጸሙ አካላት ላይም ሕጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃዎች መወሰዳቸውን ገልጸዋል።
በመድረኩም የክልል ተጠሪ ተቋማት ፣ የዞንና የልዩ ወረዳ የሠላም እና ፀጥታ አመራሮች እና የወሳኝ ኩነት አስተባባሪዎች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የባለድርሻ አካላት የኤጀንሲው ማኔጅመንት አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ።

ባለፉት ሦስት ዓመታት ሰላምና ጸጥታ የክልሉ ቀዳሚ አጀንዳ ተደርጎ በመሠራቱ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሶስት አመት በፊት በአዲስ መልክ ተደራጅቶ ወደ ተግባር ሲገባ...
17/08/2026

ባለፉት ሦስት ዓመታት ሰላምና ጸጥታ የክልሉ ቀዳሚ አጀንዳ ተደርጎ በመሠራቱ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሶስት አመት በፊት በአዲስ መልክ ተደራጅቶ ወደ ተግባር ሲገባ ልዩ ትኩረት ይፈልግ የነበረው ጉዳይ የሰላምና ጸጥታ መረጋገጥ እንደነበር የክልሉ መንግሥት በግልጽ አስቀምጧል ።

በተለይም የክልሉ መንግሥት ተረጋግቶ እንዳይሰራ፣ በሕዝቦች መካከል መተማመን እንዳይፈጠርና ወደ ልማት ከመግባት ይልቅ ትርምስ እንዲፈጠር ከውስጥም ከውጭም በተደራጀ መንገድ ይደረጉ የነበሩ አሉታዊ ጫናዎች በርካታ ነበሩ።

ክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ላይ እንደሚያነሱትም በተለይ የማህበራዊ ሚዲያ ውዥንብር፣ የተዛቡ መረጃዎችና ገጽታን ለማጠልሸት የታቀዱ ተደጋጋሚ እንቅስቃሴዎች ትልቅ የሰላምና ጸጥታ ስጋት ሆነው ነበር።

ለክልሉ አለመረጋጋት ሆን ብለውና ተደራጅተው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ከ250 በላይ አደገኛ ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶች ይነዙት የነበረው ጥላቻ፣ ውዥንብር፣ የግጭት ድባብና ክልላዊ አንድነትን የመሸርሸር ፈተና ደቅኖ ነበር።

ከዚህ በተጨማሪም በውይይት የሚፈቱ ጉዳዮችን የግጭት መነሻ የማድረግ ሙከራዎች፣ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች የቆዩ አለመግባባቶችንና የሕዝብ ጥያቄዎችን በመጠምዘዝ ማህበረሰብን ወደ አላስፈላጊ ሽኩቻ የማስገባት ፍላጎቶች እና የአጎራባች ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች የጸጥታ ስጋትም እንዲሁ የክልሉ ፈተና እንደነበር ይታወሳል።

ከእነዚህ ተጨባጭ ስጋቶች መነሻ ክልሉ ሰላምና ጸጥታ የማረጋገጥ ጉዳይን ቀዳሚ አጀንዳው በማድረግ ግልጽ አቅጣጫዎችን አስቀምጦ በቁርጠኝነት ተንቀሳቅሷል ።

አስተማማኝ ሰላምና ጸጥታ ለሁሉም ልማቶችና ብልጽግና እንዲሁም ለክልሉ ሕዝቦች ሰላማዊ መስተጋብር ዋስትና መሆኑን ጠንቅቆ በመረዳት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በተቀናጀ መንገድ ወደ ተግባር ገብቷል።

በዚህ መነሻ የሰላምና ጸጥታ ማረጋገጥ ተግባራትን በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲሁም በጠንካራ የክትትልና ግምገማ ሥርዓት በመምራት በዘርፉ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ ማድረግ ተችሏል።

የሕዝቦችን አብሮነትና ወንድማማችነት የማጎልበት፣ የሰላም ጠንቅ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ፣ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ቅድሚያ የመስጠት፣ ባህላዊ የግጭት አፈታት እሴቶችን በጥናት ለይቶ ለዘላቂ ሰላም እሴት ግንባታ የድርሻቸውን እንዲወጡ ማስቻል፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎችን የሰላም ግንባታ ሚና የማገልበት ሥራዎች በክልሉ መንግሥት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው ስኬታማ ተግባራት ነበሩ።

በተለይ በክልሉ ሕዝቦች መካከል ለዘመናት ጸንተው የቆዩ ባህላዊ፣ ማህበራዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ-ምድራዊ ትስስሮችንና የአብሮነት ማሳያዎችን በማጎልበት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያላሰለሱ ጥረቶች ተደርገዋል ።

የእነዚህን ዘርፈ ብዙ የጋራ እሴቶች የሰላም ዋጋና ድርሻ ግንዛቤ ውስጥ ያስገቡ ወሳኝ እርምጃዎች ተወስደዋል ።

በተናጠልም በጋራም ታላላቅ ህዝባዊ ኮንፈረንሶችና ተከታታይ የማህበረሰብ ውይይቶች ተደርገዋል ።

በሌላ በኩልም በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ለረጅም ዓመታት ሲንከባለሉ የቆዩ አለመግባባቶችን ዘላቂና አስተማማኝ በሆነ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን፣ የሕዝቦች የጋራ እሴቶችንና ሁለንተናዊ ግንኙነቶችን በሚያስጠብቅ መልኩ ለመፍታት ጥናቶች ተካሂደዋል ።

በጥቅሉም በክልሉ ባለፉት ሦስት ዓመታት በጠንካራና ስኬታማ የአመራር ብቃት፣ የአስተማማኝና ዘላቂ የሰላም ግንባታ፣ የህግ የበላይነትን በቁርጠኝነት የማስከበር፣ ለዜጎች መስተጋብር ዘላቂና ሁለንተናዊ ግንኙነት ቅድሚያ የመስጠት፣ ለፍትሃዊ የልማት ተደራሽነት፣ የቅሬታ ምንጭ ለሆኑ የህዝብ ጥያቄዎች፣ ለሰላም ስጋቶችና ለጸጥታ መደፍረስ መንስኤዎች ቅድመ መከላከል ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራበት፣ አመርቂ ስኬትም የተመዘገበበት ነበር ለማለት ይቻላል።

ክልሉ ባሳለፍነው 2018 በጀት አመት ያለ ምንም የጸጥታ ችግር በብቃት ያስተናገዳቸው ሀገራዊ ሁነቶች እንደ 20ኛው የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን፣ ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ እና ሰባተኛው ጠቅላለ ምርጫ ያሉ ታላላቅ ሀገራዊ ሁነቶች ክልሉ የሰላም ተምሳሌት ለመሆኑ ተጨበጭ ማሳያ ናቸው።

በመሆኑም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ሕዝብ ያለምንም ስጋት 24 ሰዓት ምርትና ሰው የሚንቀሳቀስበት፣ የልማት ብቻ ሳይሆን የአስተማማኝ ሰላምና አብሮነት ተምሳሌት የማድረግ ቅንጅታዊ እንቅስቃሴዎች ውጤት በጉልህ እየተንጸባረቀ ይገኛል።
(የክልሉ ኮሙኒኬሽን )

መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዜጎችና በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል - ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ‎መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዜጎችና በሀገር ...
14/08/2026

መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዜጎችና በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል - ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ‎መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዜጎችና በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል አሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያና ማላዊ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በጋራ መከላከል የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

‎ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፍልሰት እድሎችም ተግዳሮቶችም ያሉት ውስብስብ ሂደት ነው፡፡

‎ፍልሰትን በአግባቡ ማስተዳደር ከተቻለ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ለማፋጠንና እና ቀጣናዊ ውህደትን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

በአንጻሩ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት በዜጎችና በሀገር ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል ብለዋል።

‎የማላዊ ሪፐብሊክ የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ፒተር ሙኩሂቶ በበኩላቸው፤ ዜጎችን ለመታደግና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀልን ለማስቆም ማላዊ በቁርጠኛነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።
FBC

Address

አድራሻ:~የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር ፅ/ቤት ህንፃ 1ኛ ፎቅ
Hossana
HOSSANA,

Opening Hours

Monday 08:30 - 05:30
Tuesday 08:30 - 05:30
Wednesday 08:30 - 05:30
Thursday 08:30 - 05:30
Friday 08:30 - 05:30

Telephone

+468210183

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ:

Shortcuts

Share