በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት /East Azernet Berbere PP

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት /East Azernet Berbere PP

በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት /East Azernet Berbere PP ፈጣን፣ወቅታዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ ለሁለንተናዊ ብልጽግና

የስልጤ ዞን ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ በወረዳችን ሲያከናውን የቆየውን የ2018 በጀት አመት የማህበራት ቆጠራና ኢንስፔክሽን ስራ አጠናቀቀ!ነሃሴ29/2018፤ !ከዞኑ ስራ...
04/09/2026

የስልጤ ዞን ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ በወረዳችን ሲያከናውን የቆየውን የ2018 በጀት አመት የማህበራት ቆጠራና ኢንስፔክሽን ስራ አጠናቀቀ!

ነሃሴ29/2018፤ !

ከዞኑ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ የተውጣጣው የእንስፔክሽን ቡድን በወረዳችን በመገኘት ለዘጠኝ ተከታታይ ቀናት ሲያከናውን የቆየውን የ2018 በጀት አመት የማህበራት ቆጠራና የምዘና ኢንስፔክሽን ስራ በማጠናቀቅ ለወረዳው አስተባባሪ አካላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ግብረመልስ ሰጥቷል።

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሙዲን ሙዘሚል፣ የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ከድር፣ የወረዳው ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ አቶ ቢረዳ አማን እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ቡድኑ ለዘጠኝ ቀናት ባካሄደው አጠቃላይ የ2018 በጀት አመት የአፈፃፀም ምዘናና የማህበራት የመስክ ቆጠራ ስራዎችን በጉድለትና በጥንካሬ ግብረመልስ ሰጥቷል።

የእንስፔክሽን ቡድኑ እንደገለፀው በተዘጋጀው ቼክ-ሊስት መሰረት ምዘና መደረጉንና በ2018 በጀት አመት የተደራጁ ማህበራትን በሁሉም ቀበሌያት ቤት ለቤት በመንቀሳቀስ በመስክ ቆጠራ ሲደረግ መቆየቱን በመግለጽ በተገኙ ጥንካሬዎችና ጉድለቶችን ለባለድርሻ አካላት ግብረ መልስ መስጠት እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል።

የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የጠራ መረጃቸው ተይዞ አስፈላጊዉን ሁሉ ድጋፍ በመስጠት በተሰማሩበት የስራ መስክ ላይ ውጤታማ መሆናቸውን ማረጋገጥና በገበያ ውስጥ ብቁ፣ ተወዳዳሪና አሸናፊ ሆነው በመውጣት ከራሳቸው አልፈው በሀገራችን ኢኮኖሚ ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ ማስቻል የኢንስፔክሽኑ ዋና ዓላማ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሙዲን ሙዘሚል በወቅቱ እንደገለፁት፦ ግብረመልሱ እጅግ ወሳኝና የተለዩ ክፍተቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማስተካከል እንዲሁም የተሻለ የድጋፍና ክትትል ስርዓት ዘርግቶ ለመፈጸም ቁርጠኝነት የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሙዲን አክለውም በወረዳችን በበጀት አመቱ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸው ከዚህ በተያያዘም የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስፋፋት እና የታዩ ክፍተቶችን በማረም ለቀጣይ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ከድር በበኩላቸው ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድግና የሥራ ዕድል ፈጠራው ዘላቂነት እንዲኖረው ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ክትትልና ድጋፍ ሲያደርጉ መምጣታቸውን ጠቁመው ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ ነው - ክቡር አቶ ሙዲን ሙዘሚል!ነሀሴ/29/2018/__________________________________...
04/09/2026

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ ነው - ክቡር አቶ ሙዲን ሙዘሚል!

ነሀሴ/29/2018/
__________________________________

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ተግባራዊ መገለጫ ነው ሲሉ የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሙዲን ሙዘሚል ገለፁ።

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሙዲን ሙዘሚል እና የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ከድር በዛሬው ዕለት በላይ-ዑምናን ቀበሌ ላይ በመገኘት ወጣቶች፣ በጎ ፈቃደኞችና የቀበሌው ማህበረሰብ በክረምት ወራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን አበረታትተዋል።

አቶ ሙዲን ሙዘሚል እና አቶ ቶፊቅ ከድር በቀበሌው ለአቶ ሳዲቅ አህመድ እየተሰራ ያለውን መኖሪያ ቤት ጭቃ የማስለጠፍ መርሃግብርን አስጀምረዋል።

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሙዲን ሙዘሚል እንደገለፁት እንደ ወረዳ በበጎ ፈቃድ ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው ብለዋል።

አቶ ሙዲን አክለውም በመደመር እሳቤ የሚከናወነው ሰው ተኮር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን ጠቁመው የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና ተጠቃሚነትን ለሚያረጋግጡ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በዚህም የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና መልሶ ግንባታ፣ የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ፣ ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠትና የትምህርት ቁሳ ቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ ስራዎች መጠናከራቸውን ቀጥለዋል ብለዋል።

የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤ ማሳያ ነው ያሉት አቶ ሙዲን የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት በሁሉም መስኮች ተጠናክረው ይቀጥላሉም ብለዋል።

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ከድር በበኩላቸው፦ የፓርቲያችንን ዕሴት በመጠበቅ ሰው ተኮር ተግባራትን በማስቀጠል የወረዳችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና በማረጋገጥ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያበስሩ ተግባራት ይቀጥላሉ ብለዋል።

አቶ ቶፊቅ ከድር አክለውም፦ ሰው ተኮር ተግባራት የዜጎቻችንን ጊዜያዊ ችግሮች ከማቃለልና ከመፍታት ባሻገር የአብሮነትና የመተሳሰብ ህብረብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክር መሆኑን ተቁመዋል።

የፓርቲያችን ሰው ተኮር ማህበራዊ መስተጋብር ቀጣዩን ትውልድ በነባሩ የመተሳሰብና የአብሮነት ዕሴት ላይ ለመገንባት ጉልህ ሚናም አለው ሲሉም ገልጸዋል።

የስልጤ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ከክልሉ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ተሸለመ።ሀበይ ተስ ባለሙ፣ ሀበይ ተስ ባለነ - እንኳን ደስ አላችሁ!!!የስልጤ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ...
03/09/2026

የስልጤ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስ መምሪያ ከክልሉ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ተሸለመ።

ሀበይ ተስ ባለሙ፣ ሀበይ ተስ ባለነ - እንኳን ደስ አላችሁ!!!

የስልጤ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ በ2018 አጠቃላይ ስራዎች አፈጻጸም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 2ኛ ደረጃን ይዞ ተሸልሟል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ዛሬ ሐሙስ ነሓሴ 28/2018 በቁሊቶ ከተማ ባካሄደው የ2018 ተግባራት አፈጻጸምና የ2019 የትኩረት መስኮች ግምገማ ሴክቶሪያል ጉባኤ ላይ የስልጤ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት መምሪያ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዞኖች 2ኛ ደረጃን ይዞ ተሸላሚ ሆኗል።

መምሪያው ይህን ውጤት በማስመዝገብ ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያላቸውን የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ አስተዳደር፣ የቀበሌና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ከልብ እያመሰገነ በአዲሱ በጀት አመት በተቋሙ የሚከናወኑ ሁሉን አቀፍ የሰው ሀብት፣ የሪፎርምና አገልግሎትን የማዘመን ተግባራት ይበልጥ እንዲጎለብቱና የላቀ ውጤት እንዲመዘገብ ቅንጅታዊ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪውን ያቀርባል።

በድጋሚ ሀበይ አፍሬ ባሙ ሀበይ አፍሬ ባልነ - እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!!

የመንግሥት ኢንቨስትመንቶች አቅጣጫን የማሳየት፣ የማስቀየርና ሽግግርን የመፍጠር ተልዕኮ አላቸዉ፡፡ የመደመር መንግሥት ገጽ 140
03/09/2026

የመንግሥት ኢንቨስትመንቶች አቅጣጫን የማሳየት፣ የማስቀየርና ሽግግርን የመፍጠር ተልዕኮ አላቸዉ፡፡

የመደመር መንግሥት ገጽ 140

 ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
03/09/2026



ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”

ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

የብልፅግና ዕሳቤ  ሁለንተናዊና ከፍ ያለ ራዕይ ያለው የልማት አቅጣጫ ነዉ! የብልፅግና ዕሳቤ የአንድ ዘርፍ ወይም የአንድ ዘመን የልማት አቅጣጫ ብቻ አይደለም። ሁለንተናዊ የሆነ የኢኮኖሚ፣ የ...
03/09/2026

የብልፅግና ዕሳቤ ሁለንተናዊና ከፍ ያለ ራዕይ ያለው የልማት አቅጣጫ ነዉ!

የብልፅግና ዕሳቤ የአንድ ዘርፍ ወይም የአንድ ዘመን የልማት አቅጣጫ ብቻ አይደለም። ሁለንተናዊ የሆነ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ ልማት፣ የሰላምና ደህንነት እንዲሁም የውጭ ግንኙነት ራዕይን ያካተተ ጥልቅ ዕሳቤ ነዉ፡፡ ሁለንተናዊ ብልፅግና የቁሳዊና የሰብዓዊ ፍላጎቶችን በማጣመር፣ የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል እና የሀገርን አቅም በማጎልበት የሚገነባ ልማት ነው።

የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በማጠናከር፣ ግብርናንና ኢንዱስትሪን በማስተሳሰር፣ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የሀገርን ኢኮኖሚ ወደ አምራችነት ማሸጋገር ዋና ትኩረት ነው። የገቢ ምርቶችን በአገር ውስጥ በጥራትና በብዛት መተካት፣ የኤክስፖርት ምርትን ማሳደግ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ማስፋት እና ለዜጎች ዘላቂና አስተማማኝ የሥራ ዕድል መፍጠር የኢኮኖሚያዊ ብልፅግና ዋና መሠረቶች ናቸው። በዚህ መርህ ላይ በመመርኮዝም ዘላቂ፣ ፈጣንና አካታች የኢኮኖሚ ዕድገት በማስመዝገብ የዜጎችን መሠረታዊ ፍላጎት ማሟላት፣ ድህነትን መቅረፍ እና የኑሮ ደረጃን ማሻሻል የብልፅግና ጉዞ ዋና ግቦች ናቸው።

ሰላምና ሀገራዊ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሁለንተናዊ ብልጽግና ዕሳቤ አንዱ አካል ነዉ፡፡ ልማት ያለ ሰላም ዘላቂ አይሆንም። ስለዚህ ሰላምን ማረጋገጥ፣ የሀገርን ሉዓላዊነትና ደህንነት ማስጠበቅ እና የሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር የብልፅግና ጉዞ ወሳኝ መሠረቶች ናቸው።

የዲሞክራሲ ሥርዓትን ማስፋት፣ የዜጎችን ጥያቄዎች በተገቢው መመለስ፣ የማኅበራዊ ትሥሥርን ማጠናከር እና የጋራ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ የሁለንተናዊ ብልፅግና አካል ነው። የኢትዮጵያን ክብር፣ ጥቅምና ሉዓላዊነት በሚያስጠብቅ መንገድ የውጭ ግንኙነትን ማጠናከር፣ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲን ማስፋት እና የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት ማሳደግ የብልፅግና ራዕይ አካል ነው።

የብልፅግና ጉዞ በቀስታ የሚሄድ የልማት ጉዞ ሳይሆን፣ መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል በሚሉ የልማት አቅጣጫዎች የተመራ ጥረት ነው። ዓላማውም የኢትዮጵያን የሰው፣ የተፈጥሮና የኢኮኖሚ ሀብቶች በብቃት በማንቀሳቀስ፣ ምርታማነትን በማሳደግና የዜጎችን ተሳትፎ በማጠናከር በአንድ ትውልድ ዕድሜ ውስጥ የበለፀገች፣ ሰላማዊና ተወዳዳሪ ኢትዮጵያን መገንባት ነው።

ሁለንተናዊ ብልፅግና ከኢኮኖሚ ዕድገት ባሻገር፣ የዜጎች የተሻለ ኑሮ፣ የሀገር አቅምና የጋራ ተጠቃሚነት ግብ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅርጠኝነት መስራት ይኖርበታል፡፡

03/09/2026
የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በህብረተሰቡ በተሰበሰበ ብር ከ200 በላይ ሳቶ ግዢ ፈጽሞ ማቅረቡን ገለጸ!ቂልጦ፣ ነሃሴ/28/2018 ዓ ም________________________...
03/09/2026

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በህብረተሰቡ በተሰበሰበ ብር ከ200 በላይ ሳቶ ግዢ ፈጽሞ ማቅረቡን ገለጸ!

ቂልጦ፣ ነሃሴ/28/2018 ዓ ም
_______________________________

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከቀበሌዎች በህብረተሰቡ በተሰበሰበ ብር ከ200 በላይ ሳቶ ግዢ ፈጽሞ ማቅረቡን ገልጿል።

የወረዳው ጤና ጽ/ቤት እንደ ወረዳ ጽዱና ሞዴል ቀበሌዎችን ለመፍጠር በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን አሁን ላይም ተግባሩን ይበልጥ ለማሻሻል በቀበሌ ደረጃ ከህብረተሰቡ በተሰበሰበው ብር ከ200 በላይ ሳቶ ግዢ ፈጽሞ ለቀበሌዎች ሊያሰራጭ መሆኑን ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣...
02/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!

የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናትና በፈጠራ በመሻገር፣ በአሁን ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ዘይቤ ውስጥ ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ወረቶች የሚደመሩበት እንዲሁም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር በመሆሃ በሳቢ ኹነቶችና የንቅናቄ መንገዶች የሚመራ ይሆናል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ እንደሚሆንም የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አመላክቷል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት፤ ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል።

በትምህርት ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሚሆን ተማሪ እንዳይኖር መተባበር ከሁላችንም ይጠበቃል! አቶ ሳሊም ዋበላ!ነሀሴ/27/2018/_________________________...
02/09/2026

በትምህርት ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሚሆን ተማሪ እንዳይኖር መተባበር ከሁላችንም ይጠበቃል! አቶ ሳሊም ዋበላ!

ነሀሴ/27/2018/
___________________________________

የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በቋሚነት ለሚያስተምሩዋቸው ለሶስት ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

በዚህም ወቅት የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ የሆኑት አቶ ሳሊም ዋበላ እንዳሉት በትምህርት ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሚሆን ተማሪ እንዳይኖር መተባበር ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል።

ሀላፊው አቶ ሳሊም አክለውም እንዳነሱት ይህ ድጋፍ በአቅም ውስንነት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሚሆኑ ተማሪወችን ችግር የሚቀርፍ ከመሆኑ ባሻገር በራስ አቅም የመደጋገፍ ባህልን የሚያስድግ በመሆኑ ተግባሩ ቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።

በዘንድሮ አመት እንደ ወረዳ በርካታ ዘርፎችን ያካተተ የክረምት የበጎ ፈቃድ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ያነሱት አቶ ሳሊም ከነዚህም ውስጥ የትምህርት ቁሳቁስ የመግዛት አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች ድጋፍ ማድረግ የዚሁ አካል መሆኑንም ገልጸዋል።

በመጨረሻም እንደተነሰው ግዜው ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው የሚመለሱበት ወቅት ከመሆኑ መነሻ የመማሪያ ቁሳቁስን መግዛት የማይችሉ ተማሪዎችን በቅርበት በመደገፍና በማገዝ ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ በልዩነት መስራት ያስፈልጋል ሲሉ ሀላፊው አቶ ሳሊም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Address

Worabe
Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በስልጤ ዞን የምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት /East Azernet Berbere PP posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share