ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት

ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት 📍የግብር ስወራና ማጭበርበር በጋራ እንከላከል
📍ግብርን መክፈል የዜግነት ግዴታ ነው
📍ግብር ከፋይነቴ ያኮራኛል
📍ታማኝ ግብር ከፋይ የሃገር አለኝታ
📍ግብር ለሀገር ክብር revenue authority

አቢዮ ኤርሳሞ ስታዲየምን ከታቀደለት ጊዜ ቀድሞ ለውድድር ለማድረስ እየተሠራ ነው – አቶ ታምሬ ኤርሚያስነሀሴ 20/2018  (ሆሳዕና)​የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ባለሙያዎች ቡ...
27/08/2026

አቢዮ ኤርሳሞ ስታዲየምን ከታቀደለት ጊዜ ቀድሞ ለውድድር ለማድረስ እየተሠራ ነው – አቶ ታምሬ ኤርሚያስ
ነሀሴ 20/2018 (ሆሳዕና)
​የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ባለሙያዎች ቡድን በሆሳዕና አቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም ያከናወነውን ሦስተኛ ዙር ምልከታ አጠናቀቀ።

በጉብኝቱ የተገኙት የሀዲያ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ እና የሀዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታምሬ ኤርሚያስ፣ የፌደራሉ ቴክኒክ ቡድን የጠቆማቸውን ቀሪ ሥራዎች ከተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ቀድመው በመጨረስ ሜዳውን ለውድድር ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ አስታወቁ።

​በ2019 የውድድር ዘመን አዳዲስ ክለቦች ወደ ሊጉ ስለሚቀላቀሉ ተጨማሪ መጫወቻ ሜዳዎች እንደሚያስፈልጉ የጠቆሙት የአክሲዮን ማህበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ፤ የሆሳዕና፣ የሀላባ እና የአርባምንጭ ስታዲየሞች መስፈርቱን አሟልተው እንዲዘጋጁ መመረጣቸውን ገልጸዋል። የፌደራሉ ቡድንም ከዚህ ቀደም የነበሩ ጉድለቶች የተሸፈኑበት ፍጥነት የሚያስመሰግን መሆኑን ጠቅሶ፣ ቀሪ ሥራዎች ጥራታቸውን ጠብቀው በፍጥነት እንዲጠናቀቁ አሳስቧል።

​በምልከታው መርሃ ግብር የኢትዮጵያ እግር ኳስ የውድድርና ሥነሥርዓት ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ወገኔ ዋልተንጉስን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ የሥራኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የተሻሻለው አዋጅ ስለታክስ ማጭበርበር ምን ይላል? ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና) በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መሰረት “የታክስ ማጭበርበር” ማለት ...
26/08/2026

የተሻሻለው አዋጅ ስለታክስ ማጭበርበር ምን ይላል?

ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና)

በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መሰረት “የታክስ ማጭበርበር” ማለት ታክስን ለመሰወር ወይም ህጋዊ ያልሆነ የታክስ ጥቅም ለማግኘት ሲባል የሚከተሉትን ድርጊቶች መፈጸም ነው፤

👉 ሐሰተኛ የሂሳብ መዝገቦችን፣ ሰነዶችን፣ ደረሰኞችን ወይም ሌሎች ሰነዶችን ማቅረብ፣
👉 ገቢን፣ ግብይትን ወይም ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ መደበቅ፣
👉 ሐሰተኛ ደረሰኞችን ማዘጋጀት ወይም መጠቀም፣
👉 ሐሰተኛ የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ
👉 ሰነዶችን ማጥፋት፣ መቀየር፣ መደበቅ፣
👉 ከአንድ በላይ ወይም ትይዩ የሂሳብ መዛግብትን ወይም ሰነዶችን ማዘጋጀትና መያዝ፣ እንዲሁም ለታክስ ባለስልጣኑና ለሌሎች አካላት ማቅረብ፤
👉ሐሰተኛ የተቀናሽ ወጪዎችን፣ የግብር ወይም የታክስ ነፃ መብት፣ የተመላሽን ወይም የማካካሻ ጥያቄን ማቅረብ፤
👉 ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የታክስ ግዴታን ለመቀነስ ማናቸውንም ሌሎች ድርጊቶች መፈጸም ወይም ሕግ እንዲፈፅሙ የሚያስገድዳቸውን አለመፈጸም፡፡

በአዋጁ የተሻሻሉ የታክስ ስሌቶች እና የይርጋ ጊዜ ገደብን በተመለከተ ሲገልጽ የታክስ ባለስልጣኑ የማጭበርበር ድርጊት የተፈጸመ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ያገኘ እንደሆነ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 10 (አስር) ዓመት ውስጥ ሊያሻሽል ይችላል ይላል፡፡

ይሁን እንጂ በአዋጁ ንዑስ አንቀጽ 5 ላይ የታክስ ማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙ በማስረጃ የተረጋገጠ በሚሆንበት ጊዜ የታክሱ ባለስልጣን የ10 (አስር) ዓመቱን የይርጋ ጊዜ ገደብ ሳያልፍ በማናቸውም ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማሻሻያን ሊያደርግ እንደሚችል ይገልጻል፡፡

የማዕከላዊ ክልል ገቢዎች ቢሮ የድጋፍ ቡድን በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በመገኘት የገቢ አሰባሰብን ውጤታማነት ለማሳደግ እና ተቋማዊ አፈጻጸሞችን ለማጠናከር በሚያግዙ ጉዳዮች ላ...
26/08/2026

የማዕከላዊ ክልል ገቢዎች ቢሮ የድጋፍ ቡድን በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በመገኘት የገቢ አሰባሰብን ውጤታማነት ለማሳደግ እና ተቋማዊ አፈጻጸሞችን ለማጠናከር በሚያግዙ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረገ።

ሆሳዕና፣ ነሐሴ 20/2018 — በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ውድነህ የሚመሩት የድጋፍ ቡድን በሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በመገኘት የገቢ አፈጻጸምን ለማሻሻል፣ የግብር አሰባሰብ ሥርዓቱን ለማጠናከርና ተቋማዊ አፈጻጸምን ለማሳደግ ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ ገምግሟል።

የድጋፍ ቡድኑ ከጽ/ቤቱ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በመወያየት በሥራ ሂደቶች ላይ የሚታዩ ጠንካራ ጎኖችን፣ ክፍተቶችንና በቀጣይ መሻሻል የሚገባቸውን ጉዳዮች ለይቷል።

በመድረኩ እስካሁን ያለው የገቢ አፈጻጸም በዝርዝር ተገምግሞ፣ ከዕቅድ አንጻር የተመዘገበው ውጤት፣ የተገኙ አፈጻጸሞችና ያልተሳኩ የሥራ ዘርፎች በጥልቀት ተነስተዋል።
በተለይም የገቢ ምንጮችን በአግባቡ መለየት፣ የግብር ከፋዮችን መረጃ ማደራጀት፣ የግብር አሰባሰብና ክትትል ሥራዎችን ማጠናከር እንዲሁም የተቋሙን የዕለት ተዕለት አሠራር በውጤት ላይ እንዲመሠረት ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

ለ2019 በጀት ዓመት የተያዘውን የገቢ ዕቅድ በተግባር ለማሳካት የሚያስችሉ ስልቶች ላይም ጥልቅ ምክክር ተካሂዷል።

በተለይም የደረሰኝ አጠቃቀምና ቁጥጥርን ማጠናከር፣ የደረሰኝ አሰጣጥ ምጣኔን ማሳደግና ያለደረሰኝ የሚከናወኑ የንግድ ግብይቶችን በደረሰኝ መሆኑን የመቆጣጠር ስራ መሰራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
የደረሰኝ አሰጣጥ ሥርዓት በትክክል መተግበሩ የገቢ መሠረቱን ከማስፋት ባለፈ የግብር ፍትሐዊነትንና ግልጽነትን ለማረጋገጥ ያለው ሚና ተገልጿል።

በዚህም የንግድ ተቋማት የደረሰኝ አጠቃቀም በተደጋጋሚ እንዲከታተል፣ ጥሰት በሚፈጽሙ አካላት ላይ በሕግ መሠረት እርምጃ እንዲወሰድና ታዳጊ ችግሮች በቅድሚያ እንዲፈቱ ተመላክቷል።

የደረጃ ሽግግር ሥራዎችን ከተነሱ ዋና ጉዳዮች መካከል አንዱ ሲሆን የግብር ከፋዮችን በትክክለኛ የግብር ደረጃ መመደብ፣ የንግድ እንቅስቃሴያቸውንና የገቢ አቅማቸውን በመረጃ መደገፍ እንዲሁም ከደረጃ ሽግግር ጋር የተያያዙ የአሠራር መዘግየቶችን ማስወገድ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

ይህም እያንዳንዱ ግብር ከፋይ በትክክለኛ የገቢ አቅሙ ጋር ተመጣጣኝ ግብር እንዲከፍል በማድረግ የገቢ አፈጻጸሙን ለማሻሻል ያግዛል ተብሏል።
በተጨማሪም ያለውን ውዝፍ ዕዳ በቅንጅታዊ የሕግ ማስከበር ሥራ ወደ መንግስት ገቢ መቀየር እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

የውዝፍ ዕዳ ያለባቸውን ግብር ከፋዮች በዝርዝር መለየት፣ የዕዳውን መጠንና ምክንያት ማረጋገጥ፣ በማስታወቂያና በማስጠንቀቂያ የመክፈያ ዕድል መስጠት እንዲሁም በተሰጠው ጊዜ የማይፈጽሙ አካላት ላይ ተገቢውን የሕግ እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
የሕግ ማስከበር ሥራው በተቀናጀ መልኩ እንዲከናወን ከሌሎች የመንግስት ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባም ተጠቁሟል።

በተጨማሪም የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢዎች አፈጻጸም ተገምግሞ፣ ዘርፉ ተጨማሪ ትኩረትና ጠንካራ እርምጃ እንደሚፈልግ ተጠቁሟል።
የማዘጋጃ ቤት ገቢዎች ከከተማው የልማት ፍላጎትና ከሕዝብ አገልግሎት ጋር በቀጥታ የተያያዙ በመሆናቸው የገቢ ምንጮችን በሙሉ መለየት በትክክል መሰብሰብ እንደሚገባ ተመላክቷል።

በመጨረሻም በቀጣይ ጊዜ ሊከናወኑ በሚገቡ ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት ተፈጥሮ፣ ለፈጻሚ አካላት የሥራ ስምሪት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

የህገወጥ ንግድ ቁጥጥርና የታክስ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ተጀመረ14/12/2018 | ሆሳዕናየሀዲያ ዞን ገቢዎች መምሪያ እና ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የህገወጥ ንግድን ቁጥ...
20/08/2026

የህገወጥ ንግድ ቁጥጥርና የታክስ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ተጀመረ

14/12/2018 | ሆሳዕና
የሀዲያ ዞን ገቢዎች መምሪያ እና ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የህገወጥ ንግድን ቁጥጥር፣ ኑሮን ማረጋጋት እና የታክስ ህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ ያለመ የንቅናቄ መድረክ በሆሳዕና ከተማ ማካሄድ ጀመሩ።

በመድረኩ ከሁለቱም መምሪያዎች የቀረቡ የመነሻ ሰነዶችን መሰረት በማድረግ በገቢ አሰባሰብ፣ በግብርና ታክስ አስተዳደር ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች፣ የህገወጥ ንግድ ቁጥጥር እና የህግ ተገዥነትን ማሳደግ ላይ ምክክር እየተካሄደ ይገኛል።

የመድረኩ ዋና ዓላማ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ትብብርና ተግባቦት በመፍጠር፣ በገቢ አሰባሰብና በታክስ አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት እና ለቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው።

በመድረኩ የሀዲያ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ታምራት ግዛውን ጨምሮ የዞን፣ የከተማ፣ የወረዳ አመራሮችና ሌሎች የተጠሩ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት



#ሆሳዕና

18/08/2026
18/08/2026
ከተሞች መሠረተ ልማቶችን ለማሟላት ዘላቂ የገቢ አቅም ሊኖራቸው ይገባል፦ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል(ነሐሴ 12/2018) አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል ይህንን ያሉት በንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅና...
18/08/2026

ከተሞች መሠረተ ልማቶችን ለማሟላት ዘላቂ የገቢ አቅም ሊኖራቸው ይገባል፦ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል

(ነሐሴ 12/2018) አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል ይህንን ያሉት በንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅና በገቢ ፖቴንሻል ጥናት በቀረበው ረቂቅ ሰነድ ላይ ግብአት ለማሰባሰብ እየተካሄደ በሚገኘው ክልላዊ የውይይት መድረክ ላይ ነው ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል፣ መድረኩ በንብረት ታክስ አዋጁና በገቢ ፖቴንሻል ጥናቱ ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠርና የቀጣይ አተገባበር አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ንብረት ታክስ የከተሞችን የገቢ አቅም ለማሳደግ፣ የከተማ አገልግሎቶችንና የልማት ፍላጎቶችን ለመደገፍ ከሚያስችሉ ዋና የገቢ ምንጮች አንዱ መሆኑን አቶ ስንታየሁ ጠቁመዋል።

ከተሞች በፍጥነት ሲያድጉ የመሠረተ ልማት ፍላጎታቸውም በዚያው መጠን ስለሚጨምር፣ ዘላቂና ተገማች የራሳቸው የገቢ ምንጭ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የንብረት ታክስ ሥርዓቱ የንብረት ምዝገባና ግመታን፣ የግብር መወሰኛን፣ የክፍያ ሥርዓትንና የግብር ከፋዮችን መብትና ግዴታ በግልጽ የሚያስቀምጥ ሁለንተናዊ ሥርዓት መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። በአተገባበሩም ፍትሐዊነት ቀዳሚ መርህ ሆኖ በከተሞችና በግብር ከፋዮች መካከል የሚኖረውን መተማመን ማጠናከር እንደሚገባ አቶ ስንታየሁ አስገንዝበዋል።

እንዲሁም የገቢ ፖቴንሻል ጥናቱ ያሉትንና እስካሁን በበቂ ሁኔታ ያልተነኩ የገቢ ምንጮችን ለመለየት፣ የገቢ አሰባሰብ ክፍተቶችን ለማሳየትና ለዘላቂ የልማት ፋይናንስ ጠንካራ መሠረት ለመጣል ጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል። ጥናቱ ተግባራዊ ምክረ ሐሳቦችን ማቅረብ እንዳለበትና በመድረኩ የተሳተፉ አካላትም ለጥናቱ ስኬት የሚጠበቅባቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው አቶ ስንታየሁ አመልክተዋል።

በመድረኩ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቀመሪያ ረሻድ ፣ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘይቱና ኢብራሂም ጨምሮ ከክልል፣ ከዞንና ከከተማ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣ የገቢዎችና የፋይናንስ ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

በመድረኩ የረቂቅ ሰነድ ቀርቦ የጋራ ምክክር እየተካሄደበት ይገኛል

በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ህገወጥ የመሬት ወረራውን ለመከላከል የተዘጋጀ የህዝብ የንቅናቄ የውይይት መድረክ ተጀመረ ።ነሀሴ 11/2018 (ሆሳዕና) የውይይት በመድረኩ ዋና ዓላማ በከተሞች የሚ...
17/08/2026

በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ህገወጥ የመሬት ወረራውን ለመከላከል የተዘጋጀ የህዝብ የንቅናቄ የውይይት መድረክ ተጀመረ ።
ነሀሴ 11/2018 (ሆሳዕና)
የውይይት በመድረኩ ዋና ዓላማ በከተሞች የሚስተዋለውን ህገወጥ የመሬት ወረራውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ መሆኑንም ተጠቁሟል ።

የሆሳዕና ከተማ ፓሊስ ብሔራዊ ሎተሪ ደርሶሃል በሚል ህብረተሰቡ በማታለል የዝርፊያ ወንጀል ሲፈጽሙ ደርሼባቸዋለሁ ያላቸውን ሁለት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ ። በሆሳዕና ከ...
16/08/2026

የሆሳዕና ከተማ ፓሊስ ብሔራዊ ሎተሪ ደርሶሃል በሚል ህብረተሰቡ በማታለል የዝርፊያ ወንጀል ሲፈጽሙ ደርሼባቸዋለሁ ያላቸውን ሁለት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ ።

በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ጊዜያት ህብረተሰቡን የሎተሪ ዕጣ ደርሶኝ ነው በማለት በማጭበርበር እና የተለያዩ አደንዛዥ ዕፆችን በመጠቀም ህብረተሰቡን ሲዘረፉ የነበሩትን ተጠሪጣሪ ግለሰቦች
1ኛ.መስፍን ባልቻ ባፋ 2ኛ.ቃለዓብ ኤፍሬም አልፋዬ
የተባሉ ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቀን 9/12/2018 ዓ.ም በጀሎ ናራሞ ቀበሌ በተለምዶ ጎንቦራ ሆቴል አከባቢ ከሰዓቱ ጠዋት 3:30 ላይ ከአንዲት ሴት ሎተሪ ደርሶኝ ነው ብሎ በማጭበርበር ልጁቱን ይዞ ሲንቀሳቀሱ በፖሊስ እጅ ከፈንጅ ተይዞ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራና የታክቲክ ማስተባበር ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ኮ/ር ኤርደዶ አወኖ ገልጸዋል።

አክለውም ፖሊስ የወንጀሉን ድርጊት በማጣራት ላይ መሆኑን በመግለጽ በተለያዩ ጊዜያት በተመሳሳይ ወንጅል የተጎዱ የህብረተሰባችን ክፍሎች በአካል በመቅረብ ለምርመራ ቡዱኑ ሪፖርት እንድያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል ።

ወንጀልን በጋራ እንከላከል !!!

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ:ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም – (ሆሳዕና)የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ2....
11/08/2026

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ:
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም – (ሆሳዕና)

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ከፍ ያለ የገቢ ዕድገት ማስመዝገቡን አስታወቀ።

ጽ/ቤቱ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር 1,065,070,465.11 ብር ብልጫ በመሰብሰብ 81.69 በመቶ የገቢ ዕድገት ማስመዝገቡ ተገልጿል።

የተመዘገበው ውጤት በአንድ የሥራ መስክ ብቻ የተገኘ ሳይሆን በተቋሙ ውስጥ በተጠናከረው የተቀናጀ አሠራር፣ በጠንካራ የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በውዝፍ ዕዳ አሰባሰብና በዕለት ተዕለት የአፈጻጸም ክትትል የተመዘገበ ነው።

በተለይም የደረሰኝ አጠቃቀምን በመቆጣጠር፣ የአከራይ ተከራይ ግብርን በወቅቱ ባልከፈሉ አካላት ላይ ተገቢውን የሕግ እርምጃ በመውሰድ፣ ለረጅም ጊዜ ያልተከፈሉ ውዝፍ ዕዳዎችን በጥብቅ ክትትል በመሰብሰብ እና በቁልፍ የገቢ ምንጮች ላይ ትኩረት በማድረግ ለውጤቱ መገኘት አስተዋጽኦ ማድረጉ ተጠቁሟል።

እንዲሁም መላው የጽ/ቤቱ የታክስ ሠራዊት በቁርጠኝነት መሥራቱና የሥራ አፈጻጸም በየዕለቱ በመገምገም የታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ ማስተካከል መቻሉ ለውጤቱ መሠረት መሆኑ ተገልጿል።

በበጀት ዓመቱ የገቢ አፈጻጸም የተቋሙን የሥራ አቅም ከማሳየቱም በላይ፣ የከተማዋን የራስ ገቢ አቅም ለማሳደግ የተጀመረው ጥረት ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን ያመላክታል።

ለተመዘገበው ውጤት አስተዋጽኦ ላደረጉ የክልል ገቢዎች ቢሮ፣ የሀዲያ ዞን አስተዳደር ፣ የሀድያ ዞን ገቢዎች መምሪያ፣ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና ስራ አስፈፃሚ ፣ የከተማው አመራር ፑል ፣ ማዘጋጃ ቤት፣ ንግድና ገበያ ልማት ፣ ፍትሕ፣ ፖሊስ፣ ፍርድ ቤት፣ መንገድ ትራንስፖርት ፣ ስድስቱ ቀበሌ አስተዳደር እንዲሁም መላው የጽ/ቤቱ አመራር፣ ማኔጅመንት፣ የቡድን መሪዎችና የታክስ ባለሙያዎች ጽ/ቤቱ ምስጋና አቅርበዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት

Address

Hossana

Telephone

+251465554581

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ፅ/ቤት:

Shortcuts

Share