Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau, Government Organization, Hossana.

በክልሉ የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ ይገባል ተባለ፡፡  (ሆሳዕና፣ ጳጉሜ 2/2018) በማዕከላዊ ኢትዮ...
07/09/2026

በክልሉ የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ውጤታማነትን ለማረጋገጥ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ ይገባል ተባለ፡፡

(ሆሳዕና፣ ጳጉሜ 2/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም የስትሪንግ ኮሚቴ የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ የፕሮግራሙ የ2018 ዓ/ም አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ዝግጅት ተገምግሞ ፀድቋል፡፡

በሪፖርቱ እንደተገለጸው ፕሮግራሙ በአምስት ዓመት ውስጥ በመንገድ ግንባታ፣ ጥገና፣ በተንጠልጣይ ድልድይ ሥራ በፕሮግራሙ በታቀፉ ስምንት ወረዳዎች የሚኖሩ ከ680 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ለማድረግ ከ33 ሺህ በላይ ዜጎችም የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ወደሥራ ተገብቷል፡፡

በውይይት መድረኩ የስትሪንግ ኮሚቴው አባላት፣ በፕሮግራሙ የተቀረጹ ፕሮጀክቶች የእስካሁን አፈጻጸም የተሻለ መሆኑን ገልጸው ውጤታማነቱን ለማጎልበት እንዲሁም ቀጣይነትና ተከታታይነትን ለማረጋገጥ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡

በፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ሂደት የክልሉን ፀጋዎች በተገቢው መጠቀም በመቻሉ ወጪ በመቀነስ ጥራት ማሳደግ መቻሉም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በውይይቱ ማጠቃለያ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሀመድ ኑሪዬ እንደተናገሩት ፕሮግራሙ በገጠር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኑሮ መሻሻል ጉልህ አስታጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል፡፡

ከግምገማ መድረኩ የተገኙ ግብዓቶችን የቀጣይ ዕቅድና ትግበራ አካል በማድረግ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት ይሠራል ሲሉም በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩርን በበኩላቸው እንደገለጹት ፕሮግራሙ በገጠር የግብርና፣ የትምህርት፣ የጤና ሥርዓትን በማሻሻልና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የተቀናጀ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡

በፕሮግራሙ ዓላማ፣ ዕቅድና ማስፈጸሚያ ስልቶች ላይ ግንዛቤ መፍጠርና የህብረተሰብ ባለቤትነትን መረጋገጥ እንዲሁም ውጤት ተኮር የሀብት አጠቃቀም ሥርዓት በቀጣይ በትኩረት ሊሠራ ይገባል ብለዋል፡፡

በአሳምነው ተከተል

የቢሮውን ተጨማሪ መረጃዎች ለማግኘት ‼️
📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/
📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB
📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL
📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678
📌 በቲክቶክ tiktok.com/
📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/...
📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==
አማራጮችን ይጠቀሙ!
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን! See less

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) አዲሱን የ2019  ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ487 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረጉሆሳዕና ፣ ጳጉሜ 2፣ 2018  ፡-የማዕከላዊ ኢትዮ...
07/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) አዲሱን የ2019 ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ487 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረጉ

ሆሳዕና ፣ ጳጉሜ 2፣ 2018 ፡-የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር) አዲሱን የ2019 ዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ487 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጋቸዉ ተገልጿል ።

በመደበኛ ፍርድ ቤት በወንጀል ጉዳይ እስራት ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት በመታረም ላይ ከነበሩት ታራሚዎች መካከል የይቅርታ አዋጁና ደንቡ የሚጠይቀውን መመዘኛ አሟልተው ለተገኙ በመደበኛ ይቅርታ ደንብ ወንድ 476፣ ሴት 9 በድምሩ ለ485፣ እንዲሁም በልዩ ሁኔታ ወንድ 2 በአጠቃላይ ለ487 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ የተደረገላቸው መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል 484ቱ ታራሚዎች በሙሉ ይቅርታ ከእስር እንዲፈቱ እንዲሁም 3 ታራሚዎች ደግሞ ከዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ወደ 25 ዓመት እስራት ዝቅ የተደረገላቸው መሆኑ ተገልጿል።

ይቅርታ የተገረገላቸው የህግ-ታራሚዎች በማረሚያ ቆይታቸው መልካም ስነ-ምግባር ያሳዩ፣ ለፈፀሙት የወንጀል ድርጊት የተፀፀቱ እና አንዳንዶቹም ከተጎጂዎች ጋር እርቅ የፈፀሙ፣ ካሳ እና መቀጫዎችን የከፈሉ ስለመሆናቸው በየደረጃው ተረጋግጦ በቀረበዉ መሠረት ይቅርተዉ የተፈቀደ መሆኑን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ፣ ታራማዎች ወደ አካባቢያቸዉ ሲመለሱ ተገቢውን ድጋፍ እንድያደርግላቸው ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል ፡፡

የይቅርታዉ ተጠቃሚ ዜጎችም ወደሚኖሩበት ማህበረሰብ ሲቀላቀሉ በመልካም ስነ-ምግባራቸው አርዓያ በመሆን ህብረተሰቡን እንዲክሱ ክቡር ርዕሰ መስተዳደሩ አሳስበዋል፡፡

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ጳጉሜ 2 " ዘላቂ ልማት ሀገራዊ ማንሰራራት ቀን"  በከተማ አስተዳደሩ በላቀ ትጋትና በህዝብ ተሳትፎ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የተደረገው የመስክ ምልከታ፣
07/09/2026

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ጳጉሜ 2 " ዘላቂ ልማት ሀገራዊ ማንሰራራት ቀን" በከተማ አስተዳደሩ በላቀ ትጋትና በህዝብ ተሳትፎ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የተደረገው የመስክ ምልከታ፣

የማንሰራራት ቀን" በስልጤ ዞን ከተሞች!ጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን" በስልጤ ዞን ከተማ አስተዳደሮች ባለፉት ጊዜያት በከተሞቹ የተመዘገቡ የማንሰራራትና ወደ ከፍታው የመሻገር ማሳያዎችን በመጎ...
07/09/2026

የማንሰራራት ቀን" በስልጤ ዞን ከተሞች!

ጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን" በስልጤ ዞን ከተማ አስተዳደሮች ባለፉት ጊዜያት በከተሞቹ የተመዘገቡ የማንሰራራትና ወደ ከፍታው የመሻገር ማሳያዎችን በመጎብኘት እንዲሁም ጅምሮችን አጠናክሮ ጉድለቶችን መፍታትና ውጤቶችን ማስቀጠል ውይይት በማድረግ እየተከበረ ውሏል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት በዞኑ ከተሞች በዋናነትም በአምስቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ በከተማ ውበትና ጽዳት፣ በኮሪደርና የወንዝ ዳር ልማት እንዲሁም የከተሞቹን ተወዳዳሪነት የሚያሳድጉ ዘርፈ-ብዙ የልማት አቅርቦትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መከናወናቸው የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ማንሰራራት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን!
07/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን!

ዘላቂ ልማት ለሀገር ማንሰራራት በሚል መሪ ሃሳብ ጰጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ መሶብ የአንድ ማዕከል ሆሳዕና እና አዲሱ የሆሳዕና ከተማ ኮሪደር ልማት  ሥራዎች ምልከታ ተደረ...
07/09/2026

ዘላቂ ልማት ለሀገር ማንሰራራት በሚል መሪ ሃሳብ
ጰጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ
መሶብ የአንድ ማዕከል ሆሳዕና እና አዲሱ የሆሳዕና ከተማ ኮሪደር ልማት ሥራዎች ምልከታ ተደረገ።

"ዘላቂ ልማት ለሀገር ማንሰራራት" በሚል ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን በሆሣዕና ከተማ የተሠሩ መሠረተ ልማት ሥራዎች ምልከታ የተደረገ ስሆን ፣መሶብ የሆሳዕና አንድ ማዕከል አገልግሎት እና እየተሰራ ያለው የሆሳዕና ከተማ አዲሱ የኮሪደር ልማት ሥራ የምልከታው አካል ናቸው ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ሙዱላ ከተማ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት ያስገነባውን ቤት አስመርቆ አስረከበ።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት...
07/09/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ሙዱላ ከተማ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት ያስገነባውን ቤት አስመርቆ አስረከበ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ሙዱላ ከተማ በአንዲት አቅመ ደካማ ያስገነባውን ቤት የክልል፣ የልዩ ወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮችና የአከባቢዉ ህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት አስመርቆ አስረክቧል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ላልሾ እንደተናገሩት በጎነት በቀና አስተሳሰብ በዉዴታ የሚናደርግ ተግባር እንደሆነ ጠቅሰዋል ።

በበጎነት የሚሰሩ ተግባራት ወንድማማችነትና እህትማማችነት እንዲሁም ፍቅርን ከማጠናከር ባለፈ የብዙ አቅመ ደካሞችንና ወላጅ አጥ የሆኑ ህፃናትን እምባ እያበሰ እንደሚገኝ የቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል ።

የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ሀብታሙ በላይነህ በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ ሰዉ ተኮር ፓርቲ በመሆኑ ዜጎች የተሻለ ኑሮ እንዲኖራቸው ኢንሼትቮችን ቀርጾ እየሰራ እንዳለ ጠቁመዋል ።

በተያዘዉ ክራምት በጎ ሥራዎች በቤት ግንባታ ፣ በደም ልገሠ ፣ በመንገድ ጥገና፣ በአራንጓዴ አሻራና በሌሎችም የትኩረት መስኮች በርካታ ተግባራት እየተሰሩ እንዳሉ ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ሀብታሙ ተናግረዋል ።

የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በልዩ ወረዳዉ ለአቅመ ደካማ እናት ቤት ገንብቶ ከነሙሉ የቤት ዕቃ በማስረከቡ ያመሰገኑት ኢንጂነር ሀብታሙ ይህ ልዩ ወረዳ ልዩወ ወረዳ በመሆን የተገኘ ዕድል መሆኑን መጥቀሳቸውን ከልዩ ወረዳው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመልክታል ።

‎ትብብርንና መተጋገዝን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መትከልና ባህል እንዲሆኑ የሚያደርጉ ስራዎች ተሰርተዋል፦ አቶ ይሁን አሰፋ‎(‎ሆሳዕና፦ጳጉሜ 2/2018)‎፣ በለውጡ መንግስት የተጀመረው የበጎ ...
07/09/2026

‎ትብብርንና መተጋገዝን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መትከልና ባህል እንዲሆኑ የሚያደርጉ ስራዎች ተሰርተዋል፦ አቶ ይሁን አሰፋ

(‎ሆሳዕና፦ጳጉሜ 2/2018)‎፣ በለውጡ መንግስት የተጀመረው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የብዙዎችን ህይወት የታደገ፣እምባቸውን ያበሰና ትብብር እየተጠናከረ እንዲመጣ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉንም አስታውቀዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የክረምት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማጠቃለያ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

‎በክረምት ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ማጠቃለያ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ይሁን አሰፋ፣የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ ከፍተኛ ግምት የሚሰጣቸውና ብዙዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ስራዎች መስራት መቻሉን አብራርተዋል።

‎ትብብርንና መተጋገዝን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መትከልና ባህል እንዲሆኑ የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውንም ገልጸው፣አላማው ሰው ሆኖ ሰውን መርዳት እንደሆነም አስረድተዋል።

‎የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የብልጽግና ፓርቲ እሳቤ መሆኑንም አቶ ይሁን ገልጸው፣በዚህ ፕሮግራም ትውልድን መቅረጽና ለነገ ሀገር ተረካቢነት የሚበቁ ዜጎች እየተገነቡ ስለመሆኑም አሳውቀዋል።

‎የክልሉ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት እያደረጉ ለሚገኘው የነቃ ተሳትፎ ምስጋና ያቀረቡት ሃላፊው፣‎ወጣቶቹ የህዝቦች አብሮነት እየተጠናከረ እንዲመጣና የክልሉን ገጽታ መገንባት የሚያስችሉ ጠንካራ ስራ መስራታቸውንም አመልክተዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወጣት አብዱ ድንቁ በበኩሉ የክልሉን ወጣቶች በማነቃነቅ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጿል።

‎የክልሉ ወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የክልሉን ህዝቦች አብሮነት እያሳደገ፣የብዙ ቤተሰቦችን የዓመታት ጥያቄ እየመለሰና ትብብርና አንድነትን እያጎለበተ መምጣቱንም አስረድቷል።

‎በየዓመቱ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚሳተፉ ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን፣ስራው ባህል እየሆነና በስርዓት እየተመራ መምጣቱንም የገለጸው ወጣት አብዱ፣ለስራው መሳካት የላቀ እገዛ እያደረጉ ለሚገኙ የክልሉ አመራሮችና ወጣቶች ምስጋና አቅርቧል።

‎በክልሉ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለተሞክሮ የሚሆኑ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን፣በጎነት ጊዜና ገደብ የሌለውና ዓመቱን ሙሉ የሚሰራ መሆኑን፣ስራው የብዙዎችን እንባ በማበስ የመኖር ተስፋ እያለመለመ ስለመምጣቱም ወጣት አብዱ አብራርቷል።

‎የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ታምራት ግዛው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በዞኑ በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ እየተመራ ጥሩ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የብዙዎችን እንባ ማበስ መቻሉን፣ጥራትን በማረጋገጥ ስራውን ለማስፋፋት መታቀዱንም አቶ ታምራት አመልክተዋል።

‎በመድረኩ የሀላባ፣የከምባታና የጠምባሮ ወጣቶች ለወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያሰባሰቧቸውን ሀብቶች ወደ ሀዲያ ዞን ይዘው በመምጣት ለተያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች አከፋፍለዋል።

የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ምልከታ በማድረግ ተከብሯል ።ጳጉሜ 2 "ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የሚ...
07/09/2026

የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ምልከታ በማድረግ ተከብሯል ።

ጳጉሜ 2 "ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የማንሰራራት ቀን ምክንያት በማድረግ የተሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ምልከታ በማድረግ ተክብሯል።

ምልከታ ከተደረገባቸው መሠረተ ልማቶችን መካከል የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ፣ የሀላባ ዞን አስተዳደር ህጻን፣ በኢንዱስትሪ እና በጥቅል የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ይገኙበታል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ አንድ አገልግሎት፣ ከሰንበት እስከ ሰንበት ገበያ ማዕከል ግንባታ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ኮሪደርል ልማትም እንዲሁ ምልከታ ተደርጎባቸዋል።

የርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው መልዕክትየመስቃን እና ማረቆ ሕዝቦች የተጋመዱባቸዉ ዘርፈ ብዙ ትስስሮች እና  መስተጋብሮች ዘመናትንና ትዉልዶችን የተሻገሩ ፣ ዘመን የማይሽራቸዉ ሕያዉ ሆነዉ...
07/09/2026

የርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው መልዕክት

የመስቃን እና ማረቆ ሕዝቦች የተጋመዱባቸዉ ዘርፈ ብዙ ትስስሮች እና መስተጋብሮች ዘመናትንና ትዉልዶችን የተሻገሩ ፣ ዘመን የማይሽራቸዉ ሕያዉ ሆነዉ የሚቀጥሉ እዉነታዎች ናቸዉ።

እዉነታዉ ይህ ሆኖ ሳለ፤ በምስራቅ መስቃን እና ማረቆ የተወሰኑ አካባቢዎች አለመግባባቶች እና ግጭቶች ሲከሰቱ ቆይተዋል፤

ሲከሰቱ የቆዩ አለመግባባቶችን እና አልፎ አልፎ የሚያጋጥሙ ግጭቶችን በህዝቦቹ ባህላዊ የሽምግልና ስርዓት መሠረት በመዳኘት አካባቢዉን ወደ ተሟላ ሠላም ለማሸጋገር የተደረጉ ጥረቶች ዉጤታማ መሆናቸዉን ዛሬ ገምግመናል፤
ከመሰቃን እና ማረቆ ሕዝቦች የተዉጣጡ የባህል ሽማግሌዎች ባደረጉት ጥረት በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን በማስፈን አብሮነትን ለማጠናከር የሚያስችሉ መደላድሎች መፈጠራቸዉን ተገንዝበናል።
የመሰቃን እና የማረቆ ሕዝቦች የባህል ሽማግሌዎች ችግሩ እልባት እንዲያገኝ እያደረጉት ለሚገኘዉ ከፍተኛ ጥረት ምስጋናዬን እያቀረብኩ፣ የየአካባቢዎቹ ሕብረተሰብም አብሮነትን ለማጠናከር እና ዘላቂ ሠላምን ለማስፈን በሚደረገዉ ጥረት የበኩሉን በንቃት እንዲወጣ አደራ ለማለት እወዳለሁ።

Address

Hossana
72

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau:

Shortcuts

Share