Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau, Government Organization, Hossana.

የአሮጌው ዘመን አዙሪት ለትውልዱ አይመጥንም!! ​የሰው ልጅ የሥልጣኔ ጫፍ ላይ ለመድረስ የሚያደርገው አድካሚ ጉዞ፣ በሐሳብ ልዕልና፣ በምክንያታዊነት፣ በሰላማዊ መስተጋብር፣ እንዲሁም በምርምር...
06/06/2026

የአሮጌው ዘመን አዙሪት ለትውልዱ አይመጥንም!! ​

የሰው ልጅ የሥልጣኔ ጫፍ ላይ ለመድረስ የሚያደርገው አድካሚ ጉዞ፣ በሐሳብ ልዕልና፣ በምክንያታዊነት፣ በሰላማዊ መስተጋብር፣ እንዲሁም በምርምርና ቴክኖሎጂ ላይ የተገነባ ነው። ፖለቲካዊ ፍላጎትን በጉልበት ለማስፈጸም መሞከር፣ ከሰለጠነ ውይይት ይልቅ የጠመንጃን ቋንቋ መምረጥ፣ ንጹሐንን በመግደልና ተቋማትን በማኮላሸት ስጋትን ማንገስ የትላንቱ የጨለማ ዘመን እንጂ፣ የዛሬውና የነገው የፖለቲካ ስልት ሊሆን ከቶ አይችልም።

​የሕዝብን የጠራ ፍላጎት በጠመንጃ አፈሙዝና በፍርሃት ቆፈን ሥር አድርጎ ለማሸነፍ የሚኬድበት አቋራጭ ጎዳና፣ ለዚህ ዘመን የነቃ እሳቤ የማያብር ያረጀና ያፈጀ ስልት ነው። የዛሬው ትውልድ ይህንን የጥፋት አዙሪት በጽኑ አመክንዮ እና በነቃ ተሳትፎው እያመከነው ይገኛል።

የታሪክ ጠባሳ እና የተማርነው እውነት

​ያለፉት ዘመናት የታሪክ ማኅደሮቻችንን አቧራ ስናራግፍ፣ ኢትዮጵያ በጠመንጃ ፖለቲካ እና በኃይል እርምጃ ያተረፈችው መቆሚያ የሌለው የደም አበሳ እና የንብረት ውድመት እንጂ፣ ለኩራት የሚበቃ የሥልጣኔ ትሩፋት አልነበረም።

ፖለቲካዊ ልዩነቶችን በሰለጠነ የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ከመፍታት ይልቅ፣ በየቋጥኙ ሥር መሽጎና ጦር መዝዞ የራስን እውነት በሌሎች ላይ ለመጫን የተደረጉ አፍራሽ ድርጊቶች ሀገሪቱን ለዘመናት ወደ ኋላ ጎትተዋታል። በዚህ ስሑት መንገድ ብዙ ተዳምተናል፣ እጅግ ውድ የሆነ የሰው ሕይወት ገብረናል፤ ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም ክፉኛ ጎድቶታል።

የዓለም ተሞክሮ፡ ከጥፋት ወደ ሐሳብ ልዕልና

​ዓለም የደረሰችበትን የፖለቲካ ሥልጣኔ ስንቃኝ፣ ያደጉትና የበለጸጉት ሀገራት የደረሱበት የከፍታ ማማ ምስጢር የጠመንጃን አፈሙዝ ዘግተው ሐሳብን በማንገሳቸው መሆኑን እንረዳለን። እንደ ሶማሊያ፣ ሊቢያ እና የመን ያሉ ሀገራት፣ የፖለቲካ ፍላጎትን በኃይል ለማስገደድ በሞከሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ሳቢያ ሀገረ መንግሥታቸው ፈርሶ (Failed State) ሕዝባቸው ለከፋ ስደትና መከራ ተዳርጓል።

​ከእነዚህ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ተሞክሮዎች የምንማረው አንድ ታላቅ እውነት ቢኖር፤ እውነተኛ የፖለቲካ አሸናፊነት የሚረጋገጠው የሕዝብን ልብ በበሳል ፖለቲካዊ ፕሮግራም እና በአሳማኝ ፖሊሲ በመማረክ እንጂ፣ አፈናን በመጠቀም አለመሆኑን ነው። የዘመኑ የኢትዮጵያ ትውልድ ይህንን የሰለጠነ ፖለቲካዊ ሒደት ጠንቅቆ ይገነዘባል፤ ሀገሩም ከተያያዘችው የሥልጣኔ እና የብልጽግና ጎዳና እንድትሰናከል አይፈቅድም።

ነባራዊው እውነታ እና የመንግሥት ጽኑ ጥረቶች

​በአሁኑ የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ፣ መንግሥት የሕዝብን የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ፣ ጠንካራና ገለልተኛ ተቋማትን ለመገንባት እና የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማጽናት በርካታ ወሳኝ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል። ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን በማቋቋም ዘመናትን የተሻገሩ ሀገራዊ የፖለቲካ ስብራቶችን ለመጠገን፣ እንዲሁም በቅርቡ የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በስኬት በማጠናቀቅ የሥልጣን ሽግግር ውሳኔ በድምጽ መስጫ ካርድ እንጂ በጥይት እንዳይሆን ሰፊ ጥረት አድርጓል።

​ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አሁንም የአሮጌው ዘመን እንደራሴ ነን ባዮች የራሳቸውን ፖለቲካዊ ፍላጎት በኃይል ለመጫን ይሞክራሉ። የሕዝብን ሰላማዊ ኑሮ ለማወክ ንጹሐንን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶችን በመፈጸም፣ እንዲሁም የዲጂታል ሚዲያዎችን በመጠቀም የሐሰት ትርክትን (Disinformation) በማሰራጨት ሕዝብን ከሕዝብና ከመንግሥት ለማጋጨት ይጥራሉ። ነገር ግን፣ "ውሸት ያሯሩጣል እንጂ አያደርስም" እንደሚባለው ጥልቅ አባባል፣ የእነዚህ ኃይሎች የሐሰት ፕሮፓጋንዳ እና የተንኮል ሴራ በጊዜ ሒደት ገመናው እየተገለጠ፣ በነቃው ሕዝብ ፊት እርቃኑን እየቀረ ይገኛል። መንግሥት እነዚህን የጥፋት ኃይሎች በሕግ አግባብ ከመመከት ባለፈ፣ ትዕግስትንና ሆደ ሰፊነትን መርሆው በማድረግ ለሰላም የዘረጋው እጅ፣ ለሀገር ግንባታ ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ታላቅ ማሳያ ነው።

​ትውልዱ ይህንን ሀገራዊ እውነት ጠንቅቆ ተረድቷል። አሁን ያለንበት የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የትንሣኤ ዘመን፣ የቴክኖሎጂ ፈጠራና የመስፈንጠሪያ ዘመን እንጂ፣ ወደ ኋላ ተመልሰን በሽፍትነት የአሮጌውን ዘመን የጥፋት አዙሪት የምንለማመድበት ጊዜ አይደለም። ሀገረ መንግሥቱ ከሕዝቡ ጋር በመቀናጀት የሚያደርገውን የሕግ የበላይነት የማስከበር፣ ሰላምን የማረጋገጥ እና ልማትን የማፋጠን ጉዞ፣ አዲሱ ትውልድ በሙሉ አቅሙ ይደግፈዋል።

​የፖለቲካ ፍላጎትን በጠመንጃ እና በሐሰት ትርክት ለማስፈጸም የሚደረገው ጥረት በመቃብር ያለ፣ ያለፈ ዘመን ትርክት ነው። ዛሬ ላይ የሐሳብ ልዕልና፣ የምክንያታዊነት እና የዴሞክራሲያዊ ውይይት ድምጽ ከፍ ብሎ እየተሰማ ነው። ትውልዱ የጥፋት ኃይሎችን አጀንዳ በማመከን፣ መንግሥት ለጀመረው ሀገረ መንግሥት ግንባታ፣ ለተቋማት ጥንካሬ እና ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ሒደት ጽኑ ዘብ በመቆም፣ የበለጸገች እና የተከበረች ኢትዮጵያን ወደፊት እያሻገረ ይገኛል። የአሮጌው ዘመን አዙሪት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተሰብሯል!

#ኢቢሲ

የመደመር እሳቤ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይታጠር ለዓለም ማኅበረሰብ የተበረከተ ስጦታ ሆኗልባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በኢትዮጵያ የተመዘገቡ ታላላቅ የልማትና የዲፕሎማሲ ስኬቶችን የሚዘክር ልዩ መ...
06/06/2026

የመደመር እሳቤ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይታጠር ለዓለም ማኅበረሰብ የተበረከተ ስጦታ ሆኗል

ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በኢትዮጵያ የተመዘገቡ ታላላቅ የልማትና የዲፕሎማሲ ስኬቶችን የሚዘክር ልዩ መድረክ በዩናይትድ አረብ ኢሚሬትስ ዱባይ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

‘‘መደመር ከድንበር ባሻገር’’ በሚል መሪ ቃል በዱባይ እና ሰሜን ኢሚሬቶች የኢፌዴሪ ቆንስላ ጀነራል ፅሕፈት ቤት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማኅበር በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፥ የመደመር እሳቤ ከሀገር ውስጥ ልማት ባለፈ በውጭ ግንኙነትና በዲፕሎማሲው ረገድ ያስገኛቸው ውጤቶች ድንበር ተሻግረው በውጭ ሀገራት ለሚኖሩ ዜጎች ትልቅ ትርጉም የሰጡ መሆናቸው ተነስቷል።

በዱባይ እና የሰሜን ኢሚሬቶች የኢፌዴሪ ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘሪሁን መገርሳ በመድረኩ ላይ እንዳሉት፥ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ታሪክ የሰማኒያ ዓመታትን ያህል ግዙፍ የልማትና የፖለቲካ ታሪክ መስራት ተችሏል።

በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትሩ አዘጋጅነት የታተሙት አራቱ የመደመር መጻሕፍት እና ያመጧቸው የለውጥ ስኬቶች እየተዘከሩ ባሉበት በዚህ መድረክ ላይ፥ የመደመር መጽሐፍ በዓረብኛ ቋንቋ ተተርጉሞ በቅርቡ በዩናይትድ አረብ ኢሚሬቶች በይፋ መመረቁ ትልቅ ዓለም አቀፋዊ ስኬት መሆኑ ተጠቁሟል።

ከ350 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባት በዚሁ የባህረ ሰላጤው ሀገር ባለፉት ዓመታት የተከተለው የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣ መሆኑም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማኅበር የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ወይዘሮ ህሊና ታደሰ በበኩላቸው፥ ያለፉት የለውጥ ዓመታት የዲያስፖራው ማኅበረሰብ በተባበረ ክንድ የሀገሩን ዕድገት እውን ለማድረግ የሚያስችለው ትልቅ አቅም የፈጠረበት መሆኑን አብራርተዋል።

በዱባይ እና አካባቢው የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እየተሳተፉበት ባለው በዚህ መድረክ ላይ የለውጥ ዓመታቱ ታላላቅ ስኬቶች በዘጋቢ ፊልም ተደግፈው ለታዳሚው ቀርበዋል።

የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች!!✍7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ የዲሞክራሲ ሥርዓት ባለቤትነትን እና ለሰላም ያ...
06/06/2026

የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች!!

✍7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ የዲሞክራሲ ሥርዓት ባለቤትነትን እና ለሰላም ያለውን ጽኑ ፍላጎት በተግባር ያረጋገጠበት ታሪካዊ ክስተት ነው። የምርጫው የሀገርና የሕዝብ የህልውና መሠረት መሆኑን መንግሥት በጽኑ የሚያምን በመሆኑ ፍትሐዊ፣ ተአማኒና ወቅቱን የጠበቀ እንዲሆን ከመንግሥትና ከሕዝብ ጋር በቅንጅት ሲሠራ ቆይቷል።

✍የሀገሪቱን የለውጥ ጉዞ ለማደናቀፍ በውስጥ እና በውጭ ኃይሎች የተቀናጁ የጥፋት ሙከራዎች ተደርገዋል። መሠረተ ልማቶችን በማውደም እና የዜጎችን ዕለታዊ እንቅስቃሴ በመግታት በሕዝብ ደህንነት ላይ ቀጥተኛ ስጋት ለመፍጠር ተሞክሯል።

✍ሥልጣንን በምርጫ ሳይሆን በኃይል ለመቆጣጠር የሚሹ፣ የሕዝብን ድምፅ የመቀበል ታሪክ የሌላቸውና የጥፋት አጀንዳ አስፈጻሚዎች ምርጫውን እንደ ህልውና ስጋት ተመልክተውታል። እነዚህ ኃይሎች የዲሞክራሲ ሂደቱን ለማስቆም ከምርጫው በፊት፣ በምርጫ ወቅት እና ከምርጫው በኋላ ከፍተኛ የትርምስ እንቅስቃሴዎችን አድርገዋል።

✍መረጃዎችን በማጋነን እና የሐሰት ወሬዎችን በመፈብረክ በኅብረተሰቡ ላይ ስነ-ልቦናዊ ጫና ለመፍጠር ዘመናዊ ቴክኖሎጂና የሚዲያ አውታሮች በስፋት ጥቅም ላይ ውለዋል።

✍የኢትዮጵያ ሕዝብ የጥፋት ኃይሎቹ ያቀረቧቸውን ሦስት ተከታታይ ማደናቀፊያ ጥሪዎችና ማስፈራሪያዎች ወደ ጎን በመተው ውድቅ አድርጓቸዋል፦ የመጀመሪያው፦ "የምርጫ ካርድ አትውሰዱ" የሚለውን ጥሪ ባለመቀበል ካርድ ወስዷል። ሁለተኛው፦ "በፓርቲዎች የድጋፍ ሰልፍ ላይ አትገኙ" የሚለውን ጫና ጥሶ አደባባይ ወጥቷል። ሦስተኛው፦ "ድምፅ አትስጡ" የሚለውን ማስፈራሪያ ውድቅ በማድረግ፣ ታይቶ በማይታወቅ ከፍተኛ ቁጥር ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመጉረፍ የዜግነት መብቱን አስከብሯል።

✍ይህ የሕዝብ የነቃ ተሳትፎና ውሳኔ ኢትዮጵያውያን የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ባለቤት መሆናቸውን እና ማንኛውንም የኃይል እና የትርምስ አጀንዳ የሚያከሽፉ መሆናቸውን በተግባር ያረጋገጠ ታላቅ ክስተት ሆኖ የሚመዘገብ ነዉ።

✍ሕዝቡ በምርጫው ላይ በነቂስ ወጥቶ የተሳተፈው ያለ መስዋዕትነት አይደለም፤ ትልቁን ዋጋ የከፈለው ራሱ ሕዝቡ ነው። ሕዝቡ "ፅንፈኝነትና ሥርዓት አልበኝነት አያስፈልገኝም፤ የሕዝብን ፍላጎት የሚያስቀጥል፣ በሕግ ልጠይቀው የምችል ጽኑ መንግሥት ያስፈልገኛል" የሚል መልዕክት አስተላልፏል፡፡

✍ ሰፊ የሽብር እንቅስቃሴዎች በጸጥታ ተቋማት የተቀናጀና ወቅቱን የጠበቀ አጸፋዊ እርምጃ እንዲክሽፉ ተደርገዋል።

✍በደህንነት ምክንያት ምርጫ ያልተጀመረባቸውን ጥቂት ጣቢያዎ 143 ጣቢያዎችን ሰበብ በማድረግ "ምርጫ ተቋረጠ" የሚል የማደናገሪያ ወሬ ተለቆ ነበር። ከ50 ሺህ በላይ በሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ሂደቱ በሰላም የተከናወነ ሲሆን፣ የዓለም ማህበረሰብና የታዛቢ ቡድኖች በተመለከቱት ሁኔታ የጥፋት ኃይሎች ተሸናፊነትና የእውነት አሸናፊነት ተረጋግጧል።

✍ምርጫውን ማደናቀፍ ያቃታቸው ፅንፈኛ ቡድኖች፣ አሁን ደግሞ ሕዝብን ከአውድ ለማውጣት ሌላ የጥፋት ካርድ ለመሳብ እየሞከሩ ይገኛሉ።

✍በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ ተማሪዎች በአንድነት የቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ እያዩ በነበረበት ወቅት በተፈጸመ የፈንጂ ጥቃት *የአንድ ተማሪ ሕይወት ሲያልፍ፣ 26 ተማሪዎች ቆስለዋል።

✍ኢትዮጵያ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት የተለያየ ሃይማኖትና ብሔር ያላቸው ሕዝቦች በአብሮነትና በመደጋገፍ የኖሩባት፣ በሰላም ምሳሌ የምትሆን ሀገር ናት። ይህንን ብዝሃነት እንደ ጥንካሬ በመቁጠር ተደምረን ሀገር የመገንባት ታሪካችን የትናንትም፣ የዛሬም፣ የነገም ሆኖ ይቀጥላል።

✍የ“ሻኔ” የሽብር ቡድን በአርሲ ዞን፣ አሰኮ ወረዳ፣ ደለታ ጨፌ ቀበሌ ላይ ጥቃት ፈጽሟል። በጥቃቱም መጀመሪያ ከፀጥታ አካላት ጋር ግጭት ተፈጥሮ 5 ሚሊሻዎች እና 3 የፖሊስ አባላት ተሰውተዋል።
የጸጥታ አካላቱ ሕዝቡ እንዲሸሽ ጥረት ቢያደርጉም፣ 4 ሲቪሎች ተገድለዋል። በተጨማሪም አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፣ አንድ የመንግሥት ጤና ጣቢያ እና 65 የግለሰብ ቤቶች ተቃጥለዋል።

✍በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ለቤተክርስቲያን ግንባታ ንዋያትን ለማንቀሳቀስ የተቀረጹ የቆዩ ቪዲዮዎችን በመጠቀም፣ “ቤተክርስቲያን በስደት ላይ ነች” በሚል ሕብረተሰቡን በአሉታዊ መልኩ ለማቀስቀስ የተደረገው የሐሰት መረጃ ስርጭት በሃይማኖትም ሆነ በሞራል ስህተት ነው።

✍መንግሥት እና ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የበላይ አመራሮች ጋር በቅርበት በጥልቀት በመወያየት በጥቃቱ መጠን፣ መንስኤና በአጥፊዎቹ ፍላጎት ላይ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል። በቀጣይም የሃይማኖት አባቶች ቦታው ድረስ ሄደው ሁኔታውን እንዲመለከቱና መሰል ችግሮች እንዳይደገሙ አብሮ ይሰራል።

✍ሁኔታው ሃይማኖታዊ መልክ ይዞ ወደ አጠቃላይ ግጭት እንዳያመራ ራሳቸውን የጠበቁ የመንፈሳዊ ወጣቶች ማህበራትና የሃይማኖት አባቶች ላሳዩት ማስተዋል እናመሰግናለን።

✍ነገሮችን በስሜት ሳይሆን እውነታውን መነሻ አድርጎ በልኩ የማየት ባህል ሊኖረንይገባል። ችግሮች ሲከሰቱ ወዲያውኑ ወደ ሚዲያ ከመሮጥ ይልቅ ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ጋር በመወያየት፣ ለተጎዱት ድጋፍ ማድረግና በቀጣይ መፍትሄ ላይ መምከር ያስፈልጋል።

✍የውስጥና የውጭ ኃይሎች ማኅበራዊ እሴቶችን በመንካት ሕዝቡን ወደ ግጭት ለመክተት የሚያደርጉትን የሚዲያና የስነ-ልቦና ጦርነት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በማስተዋልና አብሮነቱን በማጠናከር ሊያከሽፈው ይገባል።

ለነገዋ ኢትዮጵያ የተጣለ አረንጓዴ መሠረት - ኢትዮጵያን ያለበሰው የ8 ዓመታት አኩሪ ጉዞ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት እና አስ...
06/06/2026

ለነገዋ ኢትዮጵያ የተጣለ አረንጓዴ መሠረት - ኢትዮጵያን ያለበሰው የ8 ዓመታት አኩሪ ጉዞ

የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት እና አስተባባሪነት ኢትዮጵያን ከበረሃማነት በመታደግ አረንጓዴ ገጽታዋን የመመለስ ትልቅ ራዕይ ሰንቆ የተጀመረ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።

በአረንጓዴ አሻራ ከ2011 እስከ 2018 ዓ.ም ባለፉት 8 ዓመታት ኢትዮያውያንን ከዳር እስከዳር በማስተባበር አስደናቂ የስኬት ታሪክ ተጽፏል።

የመርሀ ግብሩ ጅማሮ በ2011 ዓ.ም ሲከፈት ከ4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በመትከል የነገዋን አረንጓዴ ኢትዮጵያ መሰረት ጥሏል። በ2012 ዓ.ም "በመትከል ማንሰራራት" በሚል አገራዊ ስሜት ከ5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።

በአረንጓዴ አሻራ ላይ የህዝቡ ተነሳሽነት ይበልጥ እያደገ መጥቶ በ2013 ዓ.ም “ኑ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብስ” በሚል መሪ ቃል ከ6.8 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መሬት የነኩ ሲሆን፣ በ2014 ዓ.ም ደግሞ “አሻራችንን ለልጆቻችን” በሚል ራዕይ ከ7.2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ባህል በሕዝቡ ዘንድ ጠንካራ መሠረት እየያዘ መጥቶ በ2015 ዓ.ም “አሻራችን ለትውልዳችን፤ ለትውልድ እንስራ፤ ለኢትዮጵያ እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ ከ7.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።

በ2016 ዓ.ም ደግሞ ''የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ'' በሚል መሪ ቃል በተመሳሳይ ከ7.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የኢትዮያን ምድር አልብሰዋል።

ኢትዮያውያን አምና በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የአገራችንን አልፎ ዓለም አቀፍ ክብረወሰን ጭምር ሰብሮ ከ8 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በመትከል ማሳካት ተችሏል።

የዘንድሮው የ2018 ዓ.ም መርሀ ግብርም ይህንኑ የዕድገት ጉዞ በማስቀጠል ከ8 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ይተከላሉ ተብሎ ታቅዷል።

ይህ የ8 ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ ጉዞ ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ትግል ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ አኩሪ አገራዊ ድል ነው።

ኢቢሲ

የወጣቶች ንቁ የምርጫ ተሳትፎ እና የጎላ ድምፅ፤ ለነገዋ ኢትዮጵያ ግንባታና ለዲሞክራሲው ምዕራፍ አዲስ ተስፋበኢትዮጵያ የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶችን ሚና ወደ ላቀ ደረጃ ያሻገ...
06/06/2026

የወጣቶች ንቁ የምርጫ ተሳትፎ እና የጎላ ድምፅ፤ ለነገዋ ኢትዮጵያ ግንባታና ለዲሞክራሲው ምዕራፍ አዲስ ተስፋ

በኢትዮጵያ የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የወጣቶችን ሚና ወደ ላቀ ደረጃ ያሻገረና ኢትዮጵያን በጽኑ የዲሞክራሲ መሰረት ላይ ለመገንባት የሚያስችል ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን አስታወቀ።

ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን የሰጡበት ይህ ታሪካዊ ምርጫ የሕዝብን ውሳኔ ማረጋገጡ ብቻ ሳይሆን፥ መላው የሀገራችን ወጣቶች በሂደቱ ላይ ያሳዩት ንቁ ተሳትፎ ለነገዋ የበለጸገች ሀገር ግንባታ አዲስ ተስፋ የሰነቀ መሆኑ ተገልጿል።

የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ተወካይ አቶ አሌክስአንደር ንጉሴ ከኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ባለፈ የምርጫው በሰላም መጠናቀቅ የተረጋጋ ፖለቲካና የዳበረ የዲሞክራሲ ሥርዓት በሀገራችን መሬት እንዲይዝ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

ፌዴሬሽኑ በምርጫው ሂደት በሀገር አቀፍ ደረጃ ወጣቶችን በታዛቢነት ከመመደብ ጀምሮ የመራጮች ትምህርት በመስጠት ረገድ ሰፊ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በዚህም በድምሩ 32 ሺህ 500 ወጣቶችን በታዛቢነት እንዲሁም 2 ሺህ 500 ወጣቶችን በአስተባባሪነት በማሰማራት ታሪካዊ ኃላፊነቱን በብቃት መወጣቱን ገልጸዋል።

በየምርጫ ጣቢያዎቹ የተሰማሩት የፌዴሬሽኑ ታዛቢዎች ከተለያዩ የፖለቲካ ፖርቲዎች ተወካዮች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና ከምርጫ አስፈፃሚዎች ጋር በቅንጅትና በገለልተኝነት መስራታቸው ለሂደቱ ስኬታማነት ከፍተኛ እገዛ ማድረጉንም አመላክተዋል።

ይህ አይነቱ የተደራጀ የወጣቶች ተሳትፎም ለመጪው ትውልድ የምትሆን አስተማማኝ ሀገርን ለማስረከብ በሚደረገው ጉዞ ውስጥ እንደ ትልቅ የሽግግር ምዕራፍ የሚቆጠር መሆኑ ተጠቅሷል።

በተለይም በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወጣቶች በፖለቲካው መድረክ ላይ በስፋት እንዲሳተፉና እጩ ሆነው እንዲቀርቡ ዕድል የሰጡበት ሁኔታ መታየቱ ዘርፉን ይበልጥ ተስፋ ሰጪ እንደሚያደርገው መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ይህ በፓርቲዎች የተወሰደው አወንታዊ እርምጃ ወጣቶች የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ በራሳቸው የፖለቲካ ተሳትፎና የብስለት ድምፅ እንዲወስኑ በር የከፈተ በመሆኑ፥ ምርጫው የኢትዮጵያውያን መምረጫ ብቻ ሳይሆን የሀገራዊ አንድነትና የዲሞክራሲ አሸናፊነት ማሳያ ሆኖ እንዲመዘገብ አስችሎታል ብለዋል።

በበርካታ የምርጫ ክልሎች የድምፅ ማዳመር እና ቆጠራ ሂደቱ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ ማዳመር እና ቆጠራ...
06/06/2026

በበርካታ የምርጫ ክልሎች የድምፅ ማዳመር እና ቆጠራ ሂደቱ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ ማዳመር እና ቆጠራ ሂደት አፈጻጸምን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ በርካታ የምርጫ ክልሎች የማዳመሩን ሥራ አጠናቀው ውጤት ይፋ እያደረጉ መሆኑን ገልጸው፣ በተወሰኑ አካባቢዎች ግን የተለያዩ ተግዳሮቶች በማጋጠማቸው ምክንያት ሂደቱ መዘግየቱን አስታውቀዋል።

በአዲስ አበባ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሚገኙ 29 የምርጫ ክልሎች ውጤታቸውን አጠናቀው ወደ ዋናው ማረጋገጫ ማዕከል መላካቸውን ቦርዱ ገልጿል።

በምርጫው ሂደት የተለያዩ ቅሬታዎች ለምርጫ ቦርዱ የቀረቡ ሲሆን ቦርዱ ለእነዚህ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት፣ በተለይም የፓርቲ ወኪሎች በድምፅ ቆጠራው ላይ በአካል እንዲገኙ ከማድረግ አንጻር ጠንካራ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ሰብሳቢዋ አብራርተዋል።

በቀጣዮቹ ሁለት እና ሦስት ቀናት ውስጥ ሁሉም የምርጫ ክልሎች የማዳመሩን ሥራ አጠናቀው በምርጫ ክልላቸው ውጤት ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ቦርዱ በመግለጫው አመላክቷል።

የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የአርሶ አደሩን የላቀ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተቀዳሚ አጀንዳ ማድረግ ያስፈልጋል-   አቶ ኡስማን ሱሩር(ሆሳዕና ፣ ግንቦት 29/ 2018) የግብርናውን ዘርፍ በማዘመ...
06/06/2026

የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የአርሶ አደሩን የላቀ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተቀዳሚ አጀንዳ ማድረግ ያስፈልጋል- አቶ ኡስማን ሱሩር

(ሆሳዕና ፣ ግንቦት 29/ 2018) የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን የአርሶ አደሩን የላቀ ተጠቃሚ ማረጋገጥ ቀዳሚ አጀንዳ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ገልጸዋል።

ለዚህ ስኬት ከነበረበት ኋላቀር አሠራርና ከዝናብ ጥገኝነት በመዉጣት ፣ ቴክኖሎጂ መር ግብርናን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ያስፈልጋል ብለዋል።

አቶ ኡስማን ከሀዲያ ዞን ከተለያየ መዋቅሮች ለተውጣጡ ከ1ሺ 800 በላይ የግብርና ልማት ጣቢያ ባለሙያዎች ስልጠና ማጠቃለያ ላይ እንደገለፁት ግብርናን በማዘመን ለገበያ፣ ለኤክስፖርት እና ለኢንዱስትሪ የሚሆን ምርት የሚያመርት አርሶ አደር መፍጠር የመወቅሩ ቀዳሚ ተግባ መሆን አለበት ብለዋል ።

ቴክኖሎጂን የማሸጋገር አዳዲስ አሠራሮችን በመተግበር ከድህነት ለመዉጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰዉ ለዚህም ስኬት በየደረጃው በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በአዲስ እሳቤ በላቀ ትጋት መጓዝ በአጠረ ጊዜ ክልሉን የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው አርሶ አደሩን ከድህነት ነፃ የሚያወጡ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች በመተግበር ላይ ናቸው ሲሉም አክለዋል።

ገበያ ተኮር ግብርናንና የተሟላ የእሴት ሰንሰለት ግብርናን በተናጠል ማየት እንደማይገባ የጠቆሙት አቶ ኡስማን፤ ከምርት ጀምሮ እስከ መጨረሻው የገበያ መዳረሻ ያለውን የእሴት ሰንሰለት ተከትሎ መጓዝ በዘርፉ ለሚመዘገብ ዉጤት የላቀ አስተዋፅኦ ያበረክታል።

እንደ ውሃ ተኮር ግብርና፣ አረንጓዴ አሻራ እና የሌማት ትሩፋት ያሉ ስኬታማ የክልሉ ኢኒሼቲቮች የገበያ ፍላጎት በማሟላት አኳያ የማያበረክቱት አስተዋጽኦ የላቀ ስለመሆኑም ገልጸዋል።

የግብርናው ዘርፍ ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል፣ ለሴቶች ደግሞ አስተማማኝ የገቢ ምንጭ በመፍጠር ረገድ እየተመዘገበ ያለዉን ስኬት ይበልጥ ማስፋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮን ተጨማሪ መረጃዎች ለማግኘት ‼️

📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/

📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB

📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL

📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678

📌 በቲክቶክ tiktok.com/

📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/?si=Ipdg3R3A3hpPQEUV

📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==

አማራጮችን ይጠቀሙ!!

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

በክልሉ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የሁሉ አቀፍ  የገጠር ተደራሽ  መንገድ ልማትን  የማስፋፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ( ሆሳዕ...
06/06/2026

በክልሉ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የሁሉ አቀፍ የገጠር ተደራሽ መንገድ ልማትን የማስፋፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ

( ሆሳዕና ፦ግንቦት 29/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ ከስራ ተቋራጮችና ከአማካሪዎች ጋር የስራ ግምገማ ለማድረግ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊና የሁሉ አቀፍ ገጠር ተደራሽ መንገድ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማቴዎስ ሎምበሶ እንደተናገሩት መንገድ ለየትኛውም ልማት ዋነኛ ሞተር በመሆኑ በገጠር መንገድ ተደራሽነት ልማትን ለማፋጠን በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል።

ፕሮግራሙ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል የፈጠረ እና ኢኮኖሚያዊ ብሎም ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ስለመኖሩም አብራርተዋል።

በክልሉ የተጀመረው ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ውጤታማ ሆኖ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ እና ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በጥራትና በጊዜ ተጠናቀው አገልግሎት ላይ እንዲውል መረባረብ ያስፈልጋል ብለዋል።

በክልሉ ከአለም ባንክ በተገኘው 1ቢሊዮን 398 ሚሊዮን ብር በላይ ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የ5 ዓመት ፕሮጀክት በአዲስ መንገድ ግንባታ ፣ በጥገና፣ በተንጠልጣይ ድልድይ እና በሌሎች ስራዎች ተግባራዊ እየሆኑ ናቸው ብለዋል።

ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት የተቋራጭ፣ የአማካሪ እና የአስፈጻሚ አካለት ቅንጅትን ማጠናከር ይገባል ያሉት አቶ ማቴዎስ ዝቅተኛ አፈጻጸም ያላቸው ተቋራጮች ለህብረተሰቡ ተጠቃሚ መትጋት ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

በቢሮዉ የገጠር ትስስር እና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ አቶ መሀመድ ባሙዲን በበኩላቸው በፕሮጀክቶቹ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት በአንድ ላይ መነጋገሩ ቀጣይ ስራዎችን ለማሳለጥ የሚያግዝ ነው።

ለየትኛውም ችግር መፍትሔ የሚያስፈልጉ በመሆናቸው ተቋራጮች የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በአጭር ጊዜ ተጠናቀው ለህዝቡ አገልግሎት እንዲሰጥ ሌተቀን መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት አንድን ፕሮጀክት ውጤታማ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር ይገባል ብለው በፕሮጀክቶቹ ስራ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም ለህዝቡ ተጠቃሚነት ይሰራል ነው ያሉት።

በስራ ላይ የነዳጅ እጥረት ትልቅ ማነቆ መሆኑን ገልፀው የሚመለከታቸው አካላት የመንገድ የሚሰጠውን አገልግሎት ታሳቢ እንዲያደርጉ አሳስበው ቢሮው የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ ቅንጅታዊ ስራዎችን ማጠናከር ይባል ብለዋል።

በመድረኩም ፕሮጀክቱ ከጀመረበት ከ2017 በጀት ዓመት ጀምሮ የነበረው አፈጻጸም ሪፖርት ቀርበው ውይይት ተደርገዋል።

በአድነው አሰፋ

ለተጨማሪ መረጃ ‼️

📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/

📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB

📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL

📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678

📌 በቲክቶክ tiktok.com/

📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/?si=Ipdg3R3A3hpPQEUV

📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

ብልፅግና ፓርቲ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀመረ የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊ የምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፓርቲው የ...
06/06/2026

ብልፅግና ፓርቲ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም መገምገም ጀመረ

የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊ የምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፓርቲው የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲ እቅድ አፈጻጸም በጅግጅጋ ከተማ መገምገም ጀምሯል።

ፓርቲው በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ እቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫና በምርጫው ወቅት የነበረውን አፈጻጸም ይገመግማል፣ ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞችን ይለያል፣ በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

06/06/2026

Address

Hossana
72

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau:

Share