Humbo Woreda Government Communication Affairs

Humbo  Woreda Government Communication Affairs This is the official page of humbbo woreda gov. communication affairs page please like page and stay

የሁምቦ ወረዳ  የምክር  ቤት የኦዲት ግኝት ዕዳ አስመላሽ  ግብረ -ኃይል የ2018 ዓ/ም የአፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ዉይይት አደረጉ። ሁምቦ ፦ነሐሴ 17- ...
02/09/2026

የሁምቦ ወረዳ የምክር ቤት የኦዲት ግኝት ዕዳ አስመላሽ ግብረ -ኃይል የ2018 ዓ/ም የአፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ዉይይት አደረጉ።

ሁምቦ ፦ነሐሴ 17- 2018 ዓ/ም የምክር ቤት የኦዲት ግኝት ዕዳ አስመላሽ ግብረ -ኃይል የ2018 ዓ/ም የእስካሁኑ
አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ዉይይት አደረጉ።

በመድረኩ የምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ተስፋዬ ጋንአሞ በቀጣይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትኩረት በመስጠት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶችና የኦዲት ግኝቶችን ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ አካላት መረባረብ አለበት በማለት አቅጣጫ አስቀምጧል።

በመቀጠልም እስካሁን የተመለሱ ኦዲት ገንዘብ ላይ ውይይት በማድረግ በሂደቱ ላይ ባጋጠሙ ችግሮች ላይ የጋራ መግባባትን በመፈጠር በቀጣይ የተሻለ አፈጻጸም እንድኖር ሁሉም መረባረብ አለበት ተብሏል።

‎በግምገማ መድረኩ የወረዳ ዋና አፈጉባኤ ፣ም/አፈጉባኤ ፣የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፈ፣የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፈ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲን የለውጥ ሥራ አደነቀ።በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ነብዩ ስሑል የተመራ...
01/09/2026

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲን የለውጥ ሥራ አደነቀ።

በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ነብዩ ስሑል የተመራ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ልዑክ በቻይና ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።

ልዑኩ በቤጂንግ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የአፍሪካ ጉዳዮች ኮሚቴ ጋር የፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነትን በተመለከተ ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ ላይ አቶ ነብዩ ስሑል፣ ብልፅግና ፓርቲ የሚመራበት የመደመር እሳቤና የፓርቲው ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ለሚታዩት ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ለውጦች ዋነኛ መሠረት መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤታማነት፣ የከተማና የገጠር ልማትን በተቀናጀ መልኩ ማከናወን፣ ሕዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች እና የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የፓርቲውን የእሳቤ ጥራትና የማስፈጸም አቅም የሚያሳዩ ዋነኛ ተግባራት መሆናቸውንም አቶ ነብዩ ጠቁመዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከሀገር ውስጥ የልማት ሥራ ባሻገር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ አቅም እያጠናከረ ያለ ተግባር መሆኑንም ገልጸዋል።

በፖለቲካው መስክ እየተመዘገቡ ያሉ አበረታች ለውጦችን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ በ2026 የአፍሪካ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጉባኤን በአዲስ አበባ ለማስተናገድ መመረጧንና ለጉባኤው ዝግጅት እያደረገች መሆኗን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል፣ ልዑኩን የተቀበሉት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል ወ/ሮ ሪኦ ዩሃ ብልፅግና ፓርቲ “ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግሥት፤ ጠንካራ መንግሥት ለጠንካራ ሀገር” በሚል እሳቤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እያስመዘገበ ያለውን ለውጥ ፓርቲያቸውና መንግሥታቸው በከፍተኛ አድናቆት እንደሚከታተሉ ገልጸዋል።

ወ/ሮ ሪኦ ዩሃ አክለውም፣ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲና ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነት የሚያደርጉትን ትብብር እና የጋራ ጥቅሞችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ቅንጅት በቀጣይ ለማጠናከር ፓርቲያቸው ጠንካራ አቋም እንዳለው አረጋግጠዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ልዑክ በቤጂንግ በነበረው የመጀመሪያ ቀን ውሎ፣ ከሁለትዮሽ ውይይቱ በተጨማሪ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን ታሪክ፣ ልምድ፣ ድሎችና ተግዳሮቶች የሚያሳየውን የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ሙዚየም ጎብኝቷል።

ጉብኝቱ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ካለፈው ታሪኩ በመማር የአሁኑን ስኬቶች እንዴት እያጠናከረ እንደሚገኝና የወደፊት ራዕዩን ለማሳካት እያከናወነ የሚገኘውን እንቅስቃሴዎች ለመመልከት ጠቃሚ የመማማሪያ ልምድ ሆኗል።

በቀጣዮቹ ቀናት የሁለቱ ፓርቲዎች አመራሮች የጋራ ልምድ የሚጋሩበትና እርስ በእርስ የሚማማሩበት መርሃ ግብር ይከናወናል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ የ10ኛ ሳምንት ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀመጡ   ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብ...
01/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ የ10ኛ ሳምንት ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀመጡ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ለማብሰር በመንግስት እና ፓርቲ አመራር በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በመከናወን ላይ የሚገኙ የ10ኛ ሳምንት ተግባራት ያሉበት ደረጃን በበይነ መረብ በመገምገም ለታለመው ግብ ስኬት ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡

በስብሰባው የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ወገኔ ቡዙነህ፤ በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ሳምንታዊ አፈጻጸም የተመለከተ ዝርዝር ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በውይይቱ፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነት በመሸጋገር በክልሉ በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በመከናወን ላይ ባሉ ተግባራት የ10ኛ ሳምንት አፈጻጸም መሻሻሎች መኖራቸውን ገልፀው ፤ ዕቅዱን ለማሳካት ከተቀመጠው የጊዜ ሰለዳ እና በክልሉ ካለው አቅም አንጻር አሁንም በየመዋቅሩ ብዙ መስራት እንደሚገባ በአጽንኦት ገልፀዋል፡፡

አመራሩ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘው ሀገራዊና ክልላዊ ግብ፤ አንገብጋቢና የማይቀር የሉአላዊነት ጉዳይ መሆኑን በውል ተገንዝቦ የተጀመሩ ተግባራትን ብዝኃ ታታሪነትን ተላብሶ በሙሉ ትኩረት በቁርጠኝነት በመምራት ከግብ ማድረስ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በክልሉ በራስ አቅም የሰብዓዊ ድጋፍ መሸፈን የሚያስችል አቅም ለመገንባት በመደረግ ላይ ያለው ርብርብ የሚያግዝ የተሻሻለ የአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ ደንብ ማፅደቁን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ደንቡን በሁሉም ደረጃ በአግባቡ ገቢራዊ በማድረግ ለውጤት ማብቃት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

ለዚህም ደንቡን ወደ ተግባር ለመቀየር በክልል ደረጃ የተጀመሩ የህብረተሰብ ውይይቶችን በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች ተደራሽ በማድረግ፤ ለታለመው የአደጋ ጊዜ የመጠባበቂ ፈንድ የሚውል ገንዘብ በአፋጣኝ ከዚህ ወር ጀምሮ የማሰባሰብ ስራውን መጀመር እንደሚገባ አስምረዋል።

የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ አጀንዳው የመላው ህዝብ የጋራ አጀንዳ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሀብት በማሰባሰቡ ሂደት አመራሩ፣ የመንግስት ሠራተኛው፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የልማት ድርጅቶች፤ የሀይማኖት ተቋማት፣ የንግዱ ህብረተሰብ፤ አርሶና አርብቶ አደሩን ጨምሮ ሁሉም የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ማድረግ በሚያስችል አግባብ ማስፈጸም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የተያዘው ግብ በየደረጃው ያለው አመራር የመምራት፤ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙ የሚለካበት ጭምር መሆኑን ተረድቶ፤ ለስኬቱ በመፍጠንና መፍጠር መሪህ በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት መመራትና መፈፀም እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

የሰብዓዊ ድጋፍን ከማረጋገጥ ተግባራት ጎን ለጎን ከኢሊኖ ክሰተት ጋር ተያይዞ የአየር ንብረት ለውጥ በምርታማነት ላይ የደቀነውን ፈተና እና በሰውና በእንስሳት ጤና ላይ ልያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመከላከልና ለመቀነስ የሚያስችል የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን መስራት እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።

ከአየር መዛባት ችግር ጋር ተያይዞ በሁሉም አካባቢዎች በፍጥነት ለሚደርሱ ሰብሎች ትኩረት ሰጥቶ መስራት እና የመጠባበቂያ እህል ክምችት ስራዎችን በአግባቡ መምራት እንደሚገባም አክለዋል።

ተረጂዎችን ከማሻገር ጋር በተያያዘ በማህበረሰብና በቤተሰብ ደረጃ የጠራ የብዝነስ ዕቅድ ነድፎ ለአንድ ተጎጂ አንድ የስራ እድል የመፈጠር ግብን

በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤትና ጠበላ ከተማ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዩኒቲ ማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ጥምረት(CCC) እና ተጋላጭ ልየታ ዙሪያ ኦሬንቴ...
01/09/2026

በወላይታ ዞን ሁምቦ ወረዳ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤትና ጠበላ ከተማ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ዩኒቲ ማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ጥምረት(CCC) እና ተጋላጭ ልየታ ዙሪያ ኦሬንቴሽን መድረክ እያካሄደ ነው

‎ጠበላ፤ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም የወላይታ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ጥምረት(CCC) እና ተጋላጭ ልየታ ዙሪያ ኦሬንቴሽን መድረክ በሁምቦ ወረዳ እና ጠበላ ከተማ አስተዳደር እያካሄደ ነው።

‎መድረኩ ማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ምንነት እና ዓላማ ዙሪያ ለባለድርሻዎች በማስገነዘብ ቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ነው።

‎በመድረኩ የወላይታ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ ወ/ሮ ቅድስት ወልቃ፣የሁምቦ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ታደለች ታንቱ፣ የሁሉቱ መዋቅር ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የቀበሌ አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻዎች እየተሳተፉ ነው።

የሁምቦ ወረዳ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የክረምት ወራት በጎ ተግባራት አካል የሆነው ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት ግንባታ ሥራ አካሄደ።ሁምቦ፣ ነሐሴ 26/2018 ዓ/ም በሁምቦ ወረዳ የ...
01/09/2026

የሁምቦ ወረዳ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የክረምት ወራት በጎ ተግባራት አካል የሆነው ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት ግንባታ ሥራ አካሄደ።

ሁምቦ፣ ነሐሴ 26/2018 ዓ/ም በሁምቦ ወረዳ የክረምት ወራት በጎ ተግባራት አካል የሆነው ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ እንደ ቀጠለ ይገኛል።

በዛሬው ቀን የሁምቦ ወረዳ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በሾጮራ ኦጎዳማ ቀበሌ ለሚገኙ አቅመ ደካማ የሆነው አቶ ኡፋይሳ ኡታሎ የቤት ግንባታ የሚሆን የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርገዋል።

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረ ይህ የክረምት ወራት በጎ ተግባራት ለተለያየ ማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ አቅመ ደካማ ወገኖች የሚሆን ድጋፍ በሁሉም መስክ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በፓርቲው መሪነት በተጀመረው ሰው ተኮር የሆነ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መነሻ ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ዘርፈ ብዙ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች በተደረገ ድጋፍ ቤት የሌላቸው ወገኖችን የቤት ባለቤት ከማድረግ ጀምሮ በርካታ ዜጎችን ከችግር ማላቀቅ ተችሏል ።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን የሚያጠናክር በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ ያስፈልጋል ።

በመርሃ ግብሩ ላይ የሁምቦ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግኑኝነት ዘርፊ ኃላፍ ሻ/ል ሶሎሞን ላቤና፣ የሁምቦ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ታደለች ታንቱ፣የሁምቦ ወረዳ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፍ ወ/ሮ መስተዋት ማደቦ ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

‎የሁምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ  አስተባባሪነት በሾጮራ ኦጎዳማ ቀበሌ ፅዳት ዘመቻ ተከናወነ‎‎ሁምቦ፤ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም  የሁምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስተባ...
31/08/2026

‎የሁምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት በሾጮራ ኦጎዳማ ቀበሌ ፅዳት ዘመቻ ተከናወነ

‎ሁምቦ፤ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም የሁምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት በሾጮራ ኦጎዳማ ቀበሌ ፅዳት ዘመቻ ተከናውኗል።

‎በፅዳት ዘማቻ ቦታ የተገኙት የሁምቦ ወረዳ ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፍ ወ/ሮ ታደለች ታንቱ እንደተናገሩት የፅዳት ዘመቻው የአከባቢውን ውቤት ለመጠበቅና ለጤናው ምቹና ሳቢ አከባቢ የመፍጠር ዓላማ የያዘ መሆኑ ተናግረዋል።

‎የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የአከባቢ ፅዳትና ውበት ሥራ በክንፉ አስተባባሪነት እየተሰራ የመጣና ለወደ ፍትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ አክለዋል።

‎የሁምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወጋየሁ ወጋሶ የፅዳት ዘመቻ አከባቢውን ውብ ከማድረግ በተጨማሪ ንፅህናን ባለመጠበቅ የሚመጡ በሽታዎችን ለመከላከል ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል።

‎በሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት ልዩ ልዩ የክረምት ወራት በጎ ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝም የጠቆሙ ስሆን በሁሉም ዘርፍ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ በትኩረት ይሰራል ብሏል።

የክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ የ 2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ 2019 ጠቋሚ ዕቅድ መድረክ እየተካሄደ ነው ነሐሴ 25/2018 ዓ.ምርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ...
31/08/2026

የክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ የ 2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ 2019 ጠቋሚ ዕቅድ መድረክ እየተካሄደ ነው

ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ቢሮ የ 2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ 2019 ጠቋሚ ዕቅድ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ቢሮው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ 2019 ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ ዉይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

በተጨማሪም የንቅናቄ ሰነድ፣ የዕዉቅና እና የሰርተፊኬት አሰጣጥ መርሃ-ግብር እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል።

በመድረኩ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገ/መስቀል ጫላን ጨምሮ የክልሉ መንግስት አስተባባሪ አካላት፣ የቢሮ ኃላፊዎች፣ የሁሉም ዞኖችና ሪጂዮ ፖሊሲ ከተሞች የመሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት ተወካዮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።

"በቀሪዉ ጊዜ በሁሉም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የስምሪት መስኮች ተመጣጣኝ አፈፃፀም እንዲመጣ በትኩረት ይሰራል"- አቶ ገ/መስቀል ጫላ‎‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘዉ የክረምት በጎ ...
30/08/2026

"በቀሪዉ ጊዜ በሁሉም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የስምሪት መስኮች ተመጣጣኝ አፈፃፀም እንዲመጣ በትኩረት ይሰራል"- አቶ ገ/መስቀል ጫላ

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘዉ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ 18 የትኩረት መስኮች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከብልፅግና እሳቤ የሚመነጭ ተግባር በመሆኑ በክልሉ ፓርቲና መንግስት የጋራ ቅንጅት ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል።

የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አበረታች ዉጤቶች የታዩበት መሆኑን የገለፁት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ጫላ በቀሪው ጊዜያት በሁሉም የስምሪት መስኮች ተመጣጣኝ አፈፃፀም ለማምጣት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚገነቡ ቤቶችን ፈጥኖ ከማጠናቀቅ ጎን ለጎን ቤት የሚገነባላቸዉ ዜጎችን የኑሮ ሁኔታ በዘላቂነት ለማሻሻል በትኩረት እንደሚሰራም አፅንኦት ሰጥተዋል።

በተለይም በክልሉ "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብርና ሉአላዊነት" በሚል መሪ ቃል ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጠናከሩ ስራዎች መጀመራቸው ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል።

ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎች ማሳተፍና የመረጃ አያያዝ ስርዓቱን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።

ተግባራት በዐቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ ጥብቅ ቁርኝት መመራታቸዉ፣ የተቀናጀ የሀብት አሰባሰብ ስርዓት መኖሩ፣ ሁሉም ተግባራት ወደ ስታንዳርድ መምጣታቸዉ እንዲሁም አንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት እስከታችኛው መዋቅር መዉረዱ በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጥንካሬ የተለዩ ነጥቦች ናቸዉ።

በሲድኒ ማራቶን አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈሀምቦ፣ ነሐሴ 24፣ 2018  በሲድኒ ማራቶን ኢትዮዽያዊው አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፏል።ትናን...
30/08/2026

በሲድኒ ማራቶን አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ

ሀምቦ፣ ነሐሴ 24፣ 2018 በሲድኒ ማራቶን ኢትዮዽያዊው አትሌት አዲሱ ጎበና ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፏል።

ትናንት ምሽት ለ24ኛ ጊዜ በተካሄደው የማራቶን ውድድር አትሌት አዲሱ ጎበና 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል።

አትሌቱ የገባበት ሰዓትም የቦታው ክብረ ወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።

በውድድሩ ጭምዴሳ ደበሌ 2ኛ፣ ጀማል መኮንን 5ኛ እንዲሁም የባለፈው ዓመት የርቀቱ አሸናፊ ኃይለማርያም ኪሮስ 6ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል።

በሴቶች ደግሞ ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጅፕችርችር በቀዳሚነት ውድድሩን አጠናቅቃለች።

በርቀቱ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሹሬ ደምሴ፣ ሄቨን ሀይሉ እና መሰረት አበባየሁ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን ማጠናቀቃቸውን ከፌዴሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

‎በወላይታ ዞን ወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው‎‎ሁምቦ፤ነሐሴ 23/2018 በወላይታ ዞን ወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈጻጸም ያለ...
29/08/2026

‎በወላይታ ዞን ወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው

‎ሁምቦ፤ነሐሴ 23/2018 በወላይታ ዞን ወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈጻጸም ያለበት ደረጃ የግምገማ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

‎መድረኩ በዋናነት ከተረጅነት ወደ ምርታማነት፣ የመኸር አዝመራ፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ የክረምት ትምህርት ስራዎች እና ጨምሮ ሌሎች ወቅታዊ ንቅናቄ አጀንዳዎች ላይ ያተኮረ መሆኑን ተገልጿል።

‎የእስካሁኑ የፓርቲና የመንግስት ወቅታዊ ንቅናቄ ተግባራት ያለበት ደረጃ ተገምግሞ ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣል ተብሎም ይጠበቃል።

‎በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በጥንካሬ እና በጉድለት ተለይቶ ከቅዳሜ እስከ ቅዳሜ እየተገመገመ መሆኑን ይታወሳል።

‎በመድረኩ የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ፣ የዞኑ ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መስፍን ቶማስን ጨምሮ የዞን አጠቃላይ አመራር እና የወረዳና ከተማ አስተዳዳሪዎች እና ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች እየተሳተፉ ናቸው።

Address

Wolaita Zone Humbo Woreda
Humbo Tebela
DREAMBOAT

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Humbo Woreda Government Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Humbo Woreda Government Communication Affairs:

Shortcuts

Share