Hamar Woreda Government Communication Service

Hamar Woreda Government Communication Service Information is a vital for all society

✍️ የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሳሙኤል ጋርሾ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) አማካኝነት በካራ ዱ...
03/09/2026

✍️ የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሳሙኤል ጋርሾ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) አማካኝነት በካራ ዱስ ቀበሌ እየተገነባ የሚገኘው መስኖ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ አደረጉ።

✅✅ ነሐሴ፦ 28/2018 ዓ.ም
#ካራዱስ

✍️ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) አማካኝነት በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ከ115 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት እየተገነባ የሚገኘው የካራዱስ መስኖ ፕሮጀክት አፈጻጸም ከ93 በመቶ በላይ መድረሱ ተገለጸ።

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በጽናት ለመቋቋም የተዘረጋ ሳይንሳዊና አረንጓዴ ጋሻ የሆነው የካራዱስ የፀሐይ ሃይል መስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ከ93 በመቶ በላይ ደረሰ፤ በቅርቡ ተጠናቆ ለአገልግሎ...
03/09/2026

የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በጽናት ለመቋቋም የተዘረጋ ሳይንሳዊና አረንጓዴ ጋሻ የሆነው የካራዱስ የፀሐይ ሃይል መስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ከ93 በመቶ በላይ ደረሰ፤ በቅርቡ ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃል

ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ተመላክቷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) አማካኝነት በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ከ115 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት እየተገነባ የሚገኘው የካራዱስ መስኖ ፕሮጀክት አፈጻጸም ከ93 በመቶ በላይ መድረሱ ተገለጸ።

የካራዱስ መስኖ የአርብቶና ከፊል አርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማስፈን ከፍተኛ ሚና ያለው በፀሐይ ሃይል (ሶላር) የሚሰራ በመሆኑ ለአረንጓዴ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎች የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ሲሆን፣ ግንባታው በቅርቡ ተጠናቆ በመስከረም ወር ለአገልግሎት እንደሚበቃ ይጠበቃል።

የፕሮጀክቱ መሃንዲስ ኢንጂነር ዮሐንስ ገዘኸኝ እና የቁጥጥር ድርጅቱ ተቆጣጣሪ መሃንዲስ ኢንጂነር አሰግድ አዲሱ እንደገለጹት፣ ከ80 ቀናት በላይ የዘለቀው ከባድ ዝናብና የነዳጅ እጥረት የግንባታ መዘግየት ፈጥረው የነበረ ቢሆንም በየደረጃው ባለው የተቀናጀ ክትትልና በሶስትዮሽ ውይይቶች ችግሮቹ ተቀርፈዋል።

የፕሮጀክቱ ሲቪል ሥራ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ባንታየሁ ዘመነ በሰጡት አስተያየት፣ በተሰጣቸው የሥራ ትዕዛዝ መሠረት ፕሮጀክቱን በተቀመጠው የጥራት ደረጃና የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በቁርጠኝነት እየሠሩ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ከ100 ሄክታር በላይ መሬት የማልማት አቅም ያለው ይህ ፕሮጀክት ለአካባቢው ወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ያለውየቀበሌው ነዋሪ ወጣት አጉሞ ሲልቦ ፕሮጀክቱ በአካባቢው በመገንባቱ በእጅጉ መደሰቱን ገልጾ፣ የነዋሪዎችን የኢኮኖሚ አቅም በማሳደግ ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጥ ተናግሯል። ፕሮጀክቱ ለውጤት እንዲበቃ ከአካባቢው ማህበረሰብ አንስቶ እስከ ዞን ድረስ ያሉ ባለድርሻ አካላት ያደረጉት ከፍተኛ ትብብርም ተመላክቷል።

ምንጭ፣የደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ

✍️ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ እቅድ ላይ የምክክር መድረክ መ...
03/09/2026

✍️ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ እቅድ ላይ የምክክር መድረክ መካሄድ ጀመረ።

✅✅ ነሐሴ፦ 28/2018 ዓ.ም
#ዲመካ

✍️ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ እቅድ ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

✍️ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ወንዱ ቤራ እንደገለጹት፤ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽ ለማድረግና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ይጠይቃል።

✍️ አክለውም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና ድክመቶችን በማረም በ2019 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አቶ ወንዱ አሳስበዋል።

✍️ ​የሐመር ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ በርጆሌ ጊኖ በበኩላቸው፤ የጤና ዘርፉን ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ለጤናው ዘርፍ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ በተለይም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶችን ውጤታማ ለማድረግና የህብረተሰቡን ጤና ለማረጋገጥ ሁሉም ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

✍️ የሐመር ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ የሆኑት አቶ ወሌ ወንጌላ እንደገለፁት የጤና አገልግሎትን በማሻሻል በወረዳው የሚስተዋሉ የህብረተሰብ የጤና ችግሮች ለመፍታት የ2018 በጀት ዓመት የጤና ትራንስፎርሜሽን አጃንዳዎች መሰረት ያደረገ መረጃ ማጥራትና ማደራጀት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን በዕዉቀት ለመተግበር ያለዉ ሚናው የጎላ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

✍️ ዕቅዱ በዋናነት በበሽታ መከላከልና መቆጣጠር፣ በእናቶችና ህፃናት ጤና፣ በድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ፣ በጤና መረጃ ስርዓትና የሰው ሀብት ልማት እንደሚያተኩር ኃላፊው አብራርተዋል።

✍️ በውይይት መድረኩ ላይም የዞን አመራሮች፣ የወረዳ አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ የወረዳ አመራሮች፣ የወረዳው ግብረሰናይ ድርጅቶች አስፈፃሚ አካላት፣ የጤና ጽ/ቤት ማናጅመንት አካላት፣ የጤና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ የጤና ኤክስቴንሽኖች ተገኝተዋል።

✍️ "ከኤልኒኖ ተፅዕኖ በፊት ክትባትን በማጠናከር የእንስሳት ጤናን እንጠብቅ" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የእንስሳት ክትባት ዘመቻ በቃይሳ ቀበሌ በይፋ ተጀመረ ።✅✅ ነሐሴ፦ 28/2018 ዓ.ም ...
03/09/2026

✍️ "ከኤልኒኖ ተፅዕኖ በፊት ክትባትን በማጠናከር የእንስሳት ጤናን እንጠብቅ" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የእንስሳት ክትባት ዘመቻ በቃይሳ ቀበሌ በይፋ ተጀመረ ።

✅✅ ነሐሴ፦ 28/2018 ዓ.ም
#ዲመካ

✍️ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ከVSF Germany ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር "ከኢልኒኖ ተጽዕኖ በፊት ክትባትን በማጠናከር የእንስሳትን ጤና እንጠብቅ" በሚል መሪ ቃል የእንስሳት ክትባት ዘመቻ በይፋ ተጀምሯል።

✍️ የሐመር ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ዛንጋ ኛይታ እንዳሉት እየተካሄደ የሚገኘው የክትባት ዘመቻ በእንስሳቱ ላይ ሊከሰት የሚችለውን በሽታ ቀድሞ ለመከላከል አቅም ያለው መሆኑን በመጠቆም አርብቶአደሩ ያለማስቀረት እንስሳቶቻቸውን ማስከተብ እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

✍️ የክትባቱ ፋይዳ አባሰንጋን ቀድሞ መከላከል የሚያስችል መሆኑን የተናገሩት ዶ/ር ዛንጋ በሽታው ከመከሰቱ በፊት አስቀድሞ ማስከተብ እንዳለበት በማሳሰብ ሊከስት የሚችለውን ኤልኒኖ ለማቋቋም ወሳኝ ነው ብለዋል ።

✍️ የሚሰጠው ክትባት በወረዳው ሁሉም ቀበሌያት (31) እንዲሁም በዲመካ ከተማ አስተዳደር ስር ባሉት አራት(4) ቀበሊያትን ጨምሮ እንደሚካሄድ ዶ/ር ዛንጋ አብራርተዋል።

✍️ በአሁን ሰአት እየተሰጡ ያሉት ክትባት አይነት እና ዶዝ(Dose) አንትራክስ (Anthrax).......... 60,000 Dose፣ Bovine Pastuerellosis (B.P).........50,000 Dose፣ Lumpy Skin Disease(LSD)..........62,000 Dose፣ New Castle Disease Vaccine (ፈንግል)...........5000 Dose አጠቃላይ ድምር(Total Doses):177,000 ዶዝ(Doses ) መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

✍️ የህክምና ባለሙያዎች እያንዳንዱን ተከታትሎ ክትባት አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸውም ኃላፊው አሳስበዋል።

✍️ የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ጋርሾ እንዳሉት የኤልኒኖ ክስተትን ተከትሎ የእንስሳት በሽታዎች የመከሰት ዕድል ሊገጥም እንደሚችል ያነሱ ሲሆን የዘርፉ ባለሙያዎች ክትባቱን በመስጠት አርብቶ አደሮች ደግሞ እንስሳትን በማስከተብ የድርሻውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

✍️ በማስጀመሪያው መርሃግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሐመር ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ እና ረዳት የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ በሱፍቃድ ጎይቲ እንዳሉት የእንስሳት ጤናን መጠበቅ የዘርፉን ምርታማነት በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

✍️ ክትባቱን በይፋ ያስጀመሩት የደቡብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ዋና ኃላፊ የሆኑት አቶ ምላርገው አዲሱ እንዳሉት አንድም ከብት እንዳይሞት ዕቅድ በመያዝ በሁሉም የዞናችን መዋቅሮች ክትባት ማስጀመራቸውን በመግለፅ ክትባቱ አባሰንጋ የሚባለውን በከብቶች ላይ የሚከሰተውን ገዳይ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል ነው ብለዋል ።

✍️ አንድም ከብት ህክምና አገልግሎት ሳያገኝ መቅረት እንደሌለበት አፅንኦት የሰጡት አቶ ምላርገው የአየር ንብረት ለውጥና የኢልኒኖ ተጽዕኖ መቋቋም የሚችል አቅም መገንባት አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል ።

✍️ የመምሪያ ኃላፊው አክለውም እደተናገሩት የዕንስሳቱን ጤና በተጠናከረ ሁኔታ ለመጠበቅ ወረዳው በበጀት አስደግፎ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር በመያዙ የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑትን አቶ ሳሙኤል ጋርሾን ከልብ በማመስገን ሌሎች ወረዳዎች ከዚህ ሊማሩ ይገባል በማለት የሚሰጡ የመድሃኒት ዶዞች በበጀት በማስደገፍ ትኩረት በተሰጠባቸው መዋቅሮች ላይ እንደሚደረግ አቶ ምላርጋቸው ተናግረዋል።

✍️ ዘመቻው ከዛሬው ዕለት ተጀምሮ በሁሉም ቀበሌያት ክትባት መጀመሩንና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊው አፅንኦት ሰጥተዋል።

✍️ በስተመጨረሻም ይህ የክትባት ዘመቻ እንዲሳካ በሎጂስቲክ ድጋፍ እያደረገ የሚገኘውን VSF Germany ግብረሰናይ ድርጅትን ዋና አስተዳዳሪው ከልብ አመስግነዋል።

✍️ በክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ መረሃ ግብሩ ላይም የደቡብ ኦሞ ዞን ፊት አመራሮች፣ የሐመር ወረዳ እና የዲመካ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ የሐመር ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የ ኃላፊዎች፣ የዞን እና የወረዳ ግብርና ጽ/ቤት እንስሳት ጤና ዘርፍ ባለሙያዎች ተገኝተዋል ።

✍️ የሐመር ወረዳ አቢይ ኮሚቴ በ2018 የጳጉሜን ቀናት አከባበር ዙሪያ ዉይይት አደረጉ ‎✅✅ ነሐሴ፦ 28/2018 ዓ.ም                   #ዲመካ‎✍️ ‎በሐመር ወረዳ አምስቱ የጳ...
03/09/2026

✍️ የሐመር ወረዳ አቢይ ኮሚቴ በ2018 የጳጉሜን ቀናት አከባበር ዙሪያ ዉይይት አደረጉ

✅✅ ነሐሴ፦ 28/2018 ዓ.ም
#ዲመካ

✍️ ‎በሐመር ወረዳ አምስቱ የጳጉሜ ቀናት አከባበርን በማስመልከት በተዘጋጀው የማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ የወረዳው አቢይ ኮሚቴ ከአባላቱ ጋር ዉይይት አድርጓል።

✍️ የውይይት መነሻ ሰነዱን ያቀረቡት ‎የሐመር ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ን/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ ባርጆሌ ጊኖ በዘንድሮው ዓመት የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል ያሉ ሲሆን ብልጽግና ፓርቲ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን ሁኔታ በአግባቡ አውቆ የወደፊቱን መዳረሻን እና መንገዳችንን በውል ለይቶ አስቀምጧል ብለዋል።

✍️ ባሳለፍናቸው ሰባትት የለውጥ ዓመታት በየዘርፉ አኩሪና እምርታዊ ድሎችን ማስመዝገብ ተችሏል ያሉ ሲሆን በርካታ ውስብስብ ችግሮችንም ማለፍ ተችሏል። መጪው አዲስ ዓመት ድሎቻችንን ይበልጥ የምናሰፋበት እና ተግዳራቶቻችንን የምንቀንስበት ዓመት ሊሆን ይገባል።

✍️ በሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ የሚታወቁትን #የጳጉሜ #ቀናት በልዩ ልዩ ኩነቶች በማክበር ተቋማትንም ሆነ ህዝቡን ለተልዕኮ ማዘጋጀት አስፈላጊ በመሆኑ ይህ የጳጉሜ ቀናት አከባበር ማስፈፃሚ እቅድ ተዘጋጅቶ ውይይት ተደርጓል።

✍️ ጥረቶቻችንን፣ ስኬቶቻችንን፣ ፈተናዎቻችንንና የመሻገሪያ አቅጣጫዎቻችንን በተሟላ የሪፎርም እይታ ህዝባችን እንዲገነዘበው ለማድረግ፣ ስኬቶችን ለማስቀጠልና ተግዳራቶችን ለመሻገር የሚያስችል ብቁ ዝግጅት ለማድረግ፣ የነገውን ሀገር ተረካቢ ወጣት ለሀገር ግንባታ ሚናውን እንዲወጣ ለማነሳሳት እና መጪውን አዲስ አመት በአዲስ ተስፋ ለመቀበል መሆኑ ተብራርቷል።

✍️ #በዚህም #መሠረት ፦ ‎የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት ፤

‎ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣
‎ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣
‎ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣
‎ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም
‎ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት እንደሚከበር ለማወቅ ተችሏል።

✍️ በአምስቱ የጳጉሜ ቀናት የሚከናወኑ መርሃ- ግብሮች የተሳኩ እንዲሆን አመራርና። መላው አባሎቻችንና ሕዝባችን ሚናውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

"የሴቶችን ሁል አቀፍ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ "፦የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም የክልሉ ሴቶች ማህበር የ201...
02/09/2026

"የሴቶችን ሁል አቀፍ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ "፦የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የክልሉ ሴቶች ማህበር የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና በ2019 ዕቅድ ላይ ያተኮረ መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

ሴቶችን በልማት ህብረት ማደራጀት ለሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ጉልህ ድርሻ እንዳለውም ተጠቁሟል።

የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ካሰች ኤሊያስ እንደገለፁት፣ቢሮው ሴቶችን በማደራጀትና በተለያዩ የልማት ስራዎች በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል ።

ሴቶችም የተሰጣቸውን ዕድል በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸውም ኃላፊዋ አስገንዝበዋል ።

በመተጋገዝና በመቀናጀት ለሚፈለገው ውጤት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው ፣በሚያቀራርቡን ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል ።

የህብረቱ አባላት ቁጥርን ማሳደግ መዋጮን በማጠናከር ሀብት የማሰባሰብ ተግባር ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚያስፈልግ የገለፁት ወ/ሮ ካሰች ለህብረቱ ውጤታማነት ይበልጥ መትጋት ይገባል ብለዋል። ።

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ወ/ሮ ካሰች አጽንኦት ሰጥተዋል።

የክልሉ ሴቶች ማህበር ሰብሳቢ ወ/ሮ መነን ዘውዱ በበኩላቸው፣ሴቶችን በልማት ህብረት ማደራጀት ለሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል ።

በወቅቱ አስተያየታቸውን የሰጡት የመድረኩ ተሳታፊዎች ሴቶች በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆን የተቀናጀ ጥረት ያስፈልጋል ብለዋል።

የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በልማት ህብረት ማደራጀትና የተደራጁትን ማብቃት እንዲሁም አባላቱን የማሳደግ ተግባር የሁሉም ኃላፊነት እንደሆነም አስተያየት ሰጪዎች አበክረዋል ።

የብድር አቅርቦት ማመቻቸት እንዲሁም ብድሩን ወስደው በአግባቡ በመጠቀም ውጤታማ እንዲሆኑ የተጠናከረ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል ።

በቀጣይ አደረጃጀቱን የተሻለ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር መድረኩ ተጠናቋል ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 5ቱ የጳጕሜን ቀናት በተለያዩ የመንግሥትና የሕዝብ መርሐ ግብሮች በድምቀት ይከበራሉ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የቀናቱን አከባበርን አስመልክቶ የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬ...
02/09/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 5ቱ የጳጕሜን ቀናት በተለያዩ የመንግሥትና የሕዝብ መርሐ ግብሮች በድምቀት ይከበራሉ

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

የቀናቱን አከባበርን አስመልክቶ የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ ኃይለማሪያም ተስፋዬ መግለጫ ሰጥተዋል።

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶችን በፅናት በመሻገር በአሁኑ ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ።

ክልላችን ደቡብ ኢትዮጵያም ከተደራጀበት ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ ሁለንተናዊ ለውጦችን በማስመዝገብ በዚህ የማንሠራራት ምዕራፍ ውስጥ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡

የጳጕሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር ውስጥ ወደ አዲስ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ እንደመሆኑ መጠን፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ አንኳር ስኬቶችን በመዘከር የምንደምርበት፣ ክፍተቶችን ደግሞ በማረም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋን የምንሰንቅበት መለያችን ነው፡፡

የ2018 ዓ.ም የጳጕሜን ቀናት አከባበር ሀገራችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ይሁንታ ያገኘው ፓርቲ መንግሥት የሚመሠርትበት፣ የተመረጠው መንግሥት የተጣለበትን አደራ ለመወጣት በሚዘጋጅበት፣ እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ውጤቶችን ወደ ትግበራ ለማስገባት ጠንካራ ዝግጅት በሚደረግበት ታሪካዊ ወቅት የሚከበር በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

ይህንን ታላቅ ሀገራዊና ክልላዊ ንቅናቄ በብቃት ለመምራት በክልል ደረጃ ዐቢይና ንዑሳን ኮሚቴዎች ተደራጅተው ወደ ሙሉ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተገብቷል።

የጳጕሜን ቀናትን በክልላችን በታቀደው መሠረት በንቅናቄ ለማክበር የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ እስከ ታችኛው የመንግሥት መዋቅር የወረደ ሲሆን አምስቱም ቀናት በተሰጣቸው ልዩ ስያሜዎችና መሪ መልእክቶች መሠረት እንደሚከተለው የሚከበሩ ይሆናል።

ጳጕሜን 1 “የእምርታ ቀን”፦ በክልላችንና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች የተመዘገቡ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬቶች፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ የተመዘገቡ ድሎች እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ውጤቶች ይጎላሉ፡፡ ሀገራችንና ክልላችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያደረጉት ያለውን መዋቅራዊ ሽግግር የሚያመላክቱ ሥራዎች በግንባር ቀደምትነት ይከወናሉ፡፡

ጳጕሜን 2 “የማንሠራራት ቀን”፦ በየደረጃው የተመዘገቡ የልማትና የመሠረተ ልማት ውጤቶች በዜጎች ዕለታዊ ሕይወት ላይ ያመጡትን አዎንታዊ ለውጦች ማሳየትና የኢትዮጵያንና የደቡብ ኢትዮጵያን የማንሠራራት ዘመን የሚያበስሩ የይዘት ሥራዎች ትኩረት ይሰጣቸዋል፡፡

ጳጕሜን 3 “የጽናት ቀን”፦ የፀጥታ መዋቅራችንን ዘመናዊ ቁመና፣ በሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ ያደገበትን አቅም ማሳየትና ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ለሕዝብ ሰላም የተከፈለውን የጀግኖች መስዋዕትነት በመዘከር ይከበራል።

ጳጕሜን 4 “የኅብር ቀን”፦ በለውጡ ዓመታት በተደረጉ ሪፎርሞች የተገኙ የብዙኃን አካታችነት ስኬቶች፣ ሀገር በቀል እሴቶች፣ የወል ትርክት ግንባታ ሂደቶች እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችን ህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ አብሮነትና በጎ አድራጎት የሚያጎሉ ሁነቶችና የሚዲያ ይዘቶች ይቀርባሉ፡፡

ጳጕሜን 5 “የነገው ቀን”፦ የሀገራችንን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ፣ የሳይበር ሉዓላዊነትን፣ የ“መሶብ” ለአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የ“5 ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ” ስኬቶችን በማሳየት፤ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የነገዋን ከፍታ የሚወሰን ዋና አቅም መሆኑን የሚያመላክቱ ሥራዎች ይከናወናሉ፡፡

መላው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች፣ ወጣቶች፣ የፀጥታ አካላትና የመንግሥት ሠራተኞች የጳጕሜን ቀናት አከባበርን የተቀደሱ እሴቶቻችንን በማጎልበት፣ አብሮነታችንን በማጠናከርና ለነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ በጋራ በመቆም በደማቅ ሁኔታ እንድታከብሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረትና ትጋት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!
መልካም የጳጕሜን ቀናትና የአዲሱ ዓመት የመሸጋገር በዓል ይሁንልን!

አቶ ኃይለማሪያም ተስፋዬ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ

ወላይታ ሶዶ፤

በበጀት ዓመቱ የላቀ የሥራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች የዕውቅና ሰርተፍኬትና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቷል ።‎*********‎‎ዲመካ ፣ ነሔሴ 26/2018 ዓ.ም‎‎በተካሄደው የደቡብ ኦሞ ዞን...
02/09/2026

በበጀት ዓመቱ የላቀ የሥራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች የዕውቅና ሰርተፍኬትና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቷል ።
‎*********

‎ዲመካ ፣ ነሔሴ 26/2018 ዓ.ም

‎በተካሄደው የደቡብ ኦሞ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ማጠቃለያ መድረክ በበጀት ዓመቱ የላቀና የተሻለ የሥራ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች የዕውቅና ሰርተፍኬትና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በዚህ መሰረት ከአንድ እስከ ሶስት የወጡ መዋቅሮች በደሰጃ ተቀምጠዋል።

1ኛ ሐመር ወረዳ
2ኛ ዲመካ ከተማ አስተዳደር
3ኛ ዳሰነች ወረዳ

‎በመድረኩም የ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት የሥራ ዘመን ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫዎችንና ግቦችን መነሻ ያደረገ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የዘርፍ አመራሮች የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል ።

✍️ በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በሁሉም አከባቢዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተጠቆመ።✅✅ ነሐሴ፦ 26/2018 ዓ.ም                   #ዲመካ✍️ በሐ...
01/09/2026

✍️ በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በሁሉም አከባቢዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተጠቆመ።

✅✅ ነሐሴ፦ 26/2018 ዓ.ም
#ዲመካ

✍️ በሐመር ወረዳ አቺ ሙሳ ቀበሌ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄን ለመመለስ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ስራ እየተሰራ መሆኑን የሐመር ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ል/ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሪት ዶቦ አይማ ተናገሩ።

✍️ የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሳሙኤል ጋርሾ በቦታው ተገኝተው እንዳሉት የህብረተሰብ ተሳትፎ ለማነኛውም መሰረት ልማት ወሳኝ በመሆኑ በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚሰሩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በሁሉም አከባቢዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

✍️ የመንገድ መሰረት ልማት ትልቁ ልማት በመሆኑ መንገድ መስረተ ልማት ወላድ እናቶችን፤ ህመም ወይም ድንገተኛ ጤና ችግር ሲኖር ቶሎ ወደ ጤና ተቋም ለማድረስ አምቡላንስም ይሁን ሌሎች ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት አስተዳዳሪው ገልፀዋል።

✍️ በአካባቢው የሚታየውን የመንገድ ችግር ለማቃለል ህዝቡ ያሳየው ተነሳሽነት የሚበረታታ እንደሆነ በመግለፅ ሌሎች አከባቢዎች ከዚህ ተሞክሮ መውሰድ እንዳለባቸውም አቶ ሳሙኤል አሳስበዋል።

✍️ የደቡብ ኦሞ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ መስተዋት በዛብህ መንገድ ማጣት በብዙ መልኩ የህዝቡን ህይወት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንደሚጎዳ በመግለፅ፣ በብዙ የገጠር አካባቢዎች ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ ባለመኖሩ መንግስት ልማቱ ፍትሀዊ ተደራሽነት ላይ ሚዛናዊ እይታ በማድረግ ማህበረሰቡን በማስተባበር የሚሰራ መሆኑን አንስተዋል።

✍️ ወረዳው የማህበረሰብን የመንገድ መሰረት ልማት ተደራሽነት ጥያቄ ለመፍታት በሚሰራው ስራ በጉልበትና በገንዘብ በማገዝ የአቺሙሳ ቀበሌ ማህበረሰብ የድርሻቸውን እየተወጡ መሆኑን የሐመር ወረዳ ትራንስፖርት እና መንገድ ል/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ዶቦ አይማ ገልፀዋል።

✍️ አሁን ላይ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የመንገድ ከፈታ ስራዎች ዘላቂነት ያለውን አገልግሎት እንዲሰጡና በሌሎች ቀበሊያቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቀጣይም በትኩረት ይሰራል ሲሉ ኃላፊዋ ተናግረዋል።

✍️ አከባቢው ለግብርና ስራ ብሎም እንስሳና የእንስሳ ተዋፅዖ ምርቶችን ወደ ገበያ ለማውጣት የመንገድ ከፈታ ስራው ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተገልጿል።

✍️ የሐመር ወረዳ ትራንስፖርት እና መንገድ ል/ጽ/ቤት የገጠር መንገድ ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ሙልጌታ ገብሬ እንደገለፁት በአቺ ሙሳ ቀበሌ የተጀመረው የመንገድ ከፈታ በህብረተሰቡ ተሳትፎ 5ት ኪሎ ሜትር መሆኑን የገለፁ ሲሆን ይህ የህብረተሰብ ተሳትፎ ተሞክሮም በሌሎች በ6ት ቀበሊያት ተጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል።

✍️ በአቺ ሙሳ ቀበሌ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተጠናከረው የመንገድ ከፈታ ስራ መንግስት ሊያወጣ የሚችለውን ከ4ት ሚሊዮን ብር በላይ መቀነስ መቻሉን ባለሙያው ገልፀው ይህ የህብረተሰብ ተሳትፎ ፍላጎት በበርካታ ቀበሊያት መታየቱን ተናግረዋል።

✍️ በሐመር ወረዳ የአቺ ሙሳ ቀበሌ ነዋሪዎች እንደገለፁት በቀበሌው የመንገድ ችግር በስፋት የሚታይ በመሆኑ መንግስትን ብቻ ከመጠበቅ ማህበረሰቡን በማስተባበር መንገድ ከፈታ የተጀመረ መሆኑን በመግለፅ ቀጣይ የመንግስት ድጋፍ እንዳይለያቸው ጠይቀዋል።

✍️ በመጨረሻም የሐመር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሳሙኤል ጋርሾ የግሬደር ማሽን ድጋፍ ያደረጉትን የደቡብ መንገዶች ባለስልጣንን ከልብ አመስግነዋል።

✍️ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሃ ግብር በዲመካ ከተማ ተካሂዷል።✅✅ ነሐሴ፦ 25/2018 ዓ.ም                   #ዲመካ✍️...
31/08/2026

✍️ በደቡብ ኦሞ ዞን የሐመር ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሃ ግብር በዲመካ ከተማ ተካሂዷል።

✅✅ ነሐሴ፦ 25/2018 ዓ.ም
#ዲመካ

✍️ የክረምት በጎ ፈቃድ አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሃ ግብር ላይ 36 ሰው ደም ለመለገስ ፍላጎት አሳይቶ 25ቱ በተለያየ ኬዝ ውድቅ የተደረገ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 11 ዩኒት ደም መሰብሰቡ ተችሏል።

✍️ መንግስት ሠራተኛው በበጎ ፈቃድ ደም እንዲለግስና የገጠመንን ችግር በጋራ እንድንፈታ እንዲሁም በደም ተጠቃሚ ህሙማን ለመፍጠር መረባረብ እንደሚገባ የሐመር ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ የሆኑት አቶ አብርሃም አየለ ገልጸዋል።

✍️ የሐመር ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ዋና ኃላፊ የሆኑት አቶ ወሌ ወንጌላ በክረምት ወራት ደም መለገስ እና ሌሎች የበጎ ፍቃድ ተግባራት ላይ መሰማራት ከስጦታዎች ሁሉ ውዱን ስጦታ በመስጠት በድንገተኛ አደጋ እና በወሊድ ምክንያት ለሚፈስ ደም መተኪያ እንዲሆን እያደረጉ በመሆኑ ትልቅ ስራ እየተሰራ በመሆኑን ይህ ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገልፆል።

✍️ ከበጎ ፈቃድ ደም ለጋሾች የሚገኘው ደም በጤናው ዘርፍ የዕለት ተዕለት ስራ ላይ የበርካታ ሰዎችን ህይወት በመታደግ ላይ ስለሚገኝ ሁሉም ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበትም ተመላክቷል።

✍️ በደም እጥረት ምክንያት የሚሞቱ እናቶች ቁጥር በርካታ መሆናቸውን በመገንዘብ ሁሉም ዜጋ በተለይ ደግሞ ወጣቱ ትውልድ ደም እየለገሰ የወገኑን ህይወት ለመታደግ በንቃት መሣተፍ እንደሚገባ የሐመር ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ም/ኃላፊ የሆኑት አቶ አብዮት ደስታ ተናግረዋል።

Address

South Omo
Humbo Tebela

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hamar Woreda Government Communication Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Hamar Woreda Government Communication Service:

Shortcuts

Share