የጠበላ ከተማ አስተዳደር / Tebela Town Administration

የጠበላ ከተማ አስተዳደር  / Tebela Town Administration Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የጠበላ ከተማ አስተዳደር / Tebela Town Administration, Government Organization, Humbo Tebela.

በጠበላ ከተማ አስተዳደር አላታ ቀበሌ መንደር 04 በልዩ መጠሪያ ዉሃ ገንዳ ሠፈር  በሕብረተሰብ ተሳትፎ 150 ሜተር የመንገድ ከፈታ ተደረገ።ጠበላ፤ ሚያዝያ 03/2018 ዓ.ም በጠበላ ከተማ ...
11/04/2026

በጠበላ ከተማ አስተዳደር አላታ ቀበሌ መንደር 04 በልዩ መጠሪያ ዉሃ ገንዳ ሠፈር በሕብረተሰብ ተሳትፎ 150 ሜተር የመንገድ ከፈታ ተደረገ።

ጠበላ፤ ሚያዝያ 03/2018 ዓ.ም በጠበላ ከተማ አስተዳደር በአላታ ቀበሌ መንደር 04 በልዩ መጠሪያ ዉሃ ገንዳ ሠፈር በሕብረተሰብ ተሳትፎ 150 ሜተር የመንገድ ከፈታ ተደርጓል።

መንገዱ በአከባቢው ህብረተሰብ ዘንድ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየ ስሆን ዛሬ ምላሽ ማግኘቱ እንዳስደሰታቸው የአካባቢ ነዋሪዎች ይናገራሉ።

የአንድ አከባቢ ልማት የማከናውነው በመንግሥት ብቻ ሳይሆን የህብረተሰብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ እንደሆነም ተገልጿል።

ዛሬ በቀበሌው የተጀመረው ልማት ሥራ በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ የሚቀጥል ነው ተብሏል።

በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ለ2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም የቤትና የመሠረተ ልማት ግንባታ እየተጠናቀቀ ነውጠበላ፤ ሚያዚያ 03/2018 የወላይታ ዞን አስተባባሪ አካ...
11/04/2026

በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ለ2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም የቤትና የመሠረተ ልማት ግንባታ እየተጠናቀቀ ነው

ጠበላ፤ ሚያዚያ 03/2018 የወላይታ ዞን አስተባባሪ አካላት በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ለ2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም እየተሰሩ ያሉ ስራዎች መስክ ምልከታ አደርገዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማየትና አስፈላጊ ድጋፍ ለማድረግ ዓላማ ጉብኝት ማድረጉን ገልፀዋል።

የሚገነቡ ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች ለተፈናቃዮች ምቹና ዝግጁ እንዲሆኑ ምልከታ ማድረጉንም ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ለ2ኛ ዙር ተፈናቃዮች መልሶ ለማስፈር አስፈላጊ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፥ በተለይም ጤና፣ ትምህርት እና ሌሎች አስፈላጊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ለማሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተፈናቃዮች መልሶ ለማስፈር ቀሪ ስራዎች እየተጠናቀቀ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

ለ2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም 70 የሚጠጉ ቤቶች በሰፈራ ቦታ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፥ ይህንን መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በመሳተፍ እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

ለተፈናቃዮች የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የንፁህ መጠጥ ወሃ፣ የሕክምና ተቋማት እና ሌሎች አስፈላጊ መሠረተ ልማትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ግንባታ እየተጠናቀቀ ይገኛል።

በዞኑ ካዎ ኮይሻ ወረዳ በተከሰተው በመሬት መንሸራተት እና ናዳ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉት ወገኖች በአበላ አባያ ወረዳ አባያ ጮካሬ ጥጣ መንደር ላይ "ሰፈራ ጣቢያ" በተዘጋጀው ቦታ የመጀመሪያ ዙር ተፈናቃዮች ማስፈሩን ይታወሳል።

በመስክ ምልከታው የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ፣ የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ፣ የዞኑ የመንግስት ረዳት ተጠሪዎች አቶ መስፍን ቶማስና ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤልን ጨምሮ ሌሎች የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በወላይታ ዞን የነዳጅ እጥረት ምከንያት በማድረግ ከታሪፍ እና ከወንበር በላይ የሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነውጠበላ፤ሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን የነዳጅ እጥረት ም...
11/04/2026

በወላይታ ዞን የነዳጅ እጥረት ምከንያት በማድረግ ከታሪፍ እና ከወንበር በላይ የሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው

ጠበላ፤ሚያዝያ 3/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን የነዳጅ እጥረት ምከንያት በማድረግ ከታሪፍ እና ከወንበር በላይ የሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ተገልጿል።

የወላይታ ዞን ፖሊስ መመሪያ የትራፊክ ፍሰት ቁጥጥር አደጋ መከላከል ማስተባባሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ወልደ ቢልሶ በከተማ አስተዳደር ተገኝተው ድንገተኛ ቁጥጥር ያደረጉ ሲሆን ከታርፍ በላይ የሆነ እያስከፈሉ የነበሩ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የከተማው ፖሊስ ጽ/ቤት መረጃ ይጠቁማል።

የጽ/ቤቱ ዋና አዛዥ ረ/ኢ ገብሬ ለጃሞ እንዳስታወቁት የነዳጅ እጥረት ምክንያት በማድረግ ከታርፍ በላይ የሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች ላይ የሚወሰድ እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

አያይዘውም ተገልጋዩን ህብረተሰብ የነዳጅ እጥረት እንደ ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ለማንገላታትና ከተቀመጠው ታርፍ ውጭ ለማስከፈል የሚጥሩ አሽከርካሪዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።

በዚህ የነዳጅ እጥረት ባጋጠመበት ወቅት አሽከርካሪዎች ለግላቸው ብቻ ከማሰብ የነዳጅ ችግር እስከሚፈታ ህብረተሰቡን በታማኝነት ማገልገል እንደሚገባ አሳስበዋል።

ከአሰራር ውጭ የሚሰሩ ማንኛውም ተሸከርካሪዎች ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ዋና አዛዡ የተናገሩት ዋና አዛዡ ወቅቱ የበዓል በመሆኑ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲመርጡ አሳስበዋል።

የቁጥጥርና ክትትል ስራ ከወትሮው ከፍ ባለ ሁኔታ በትኩረት የሚሰራ መሆኑን የጠቆሙት የአረካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የትራፊክ ፍሰት ቁጥጥር አደጋ መከላከል ማስተባባሪያ ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር ዮናስ ታንቶ ናቸዉ።

ከታርፍ በላይ የሚያስከፍሉ እና ትርፍ የሚጭኑ አካላትን ህብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ም/ኢንስፔክተሩ አሳስበዋል።

ወቅቱ የትራፊክ ፍሰት የሚበዛበት በመሆኑ አሽከርካሪዎች ከልክ ያለፈ ፍጥነት እንዳይጠቀሙና እግረኞች በግራ ጠርዝ እንዲሄዱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የወላይታ ዞን አስተዳደር ከዞኑ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ጋር በመሆን ከካዎ ኮይሻ ወረዳ ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ ለሰፈሩት ወገኖች ማዕድ አጋራጠበላ፤ሚያዚያ 03/2018 የወላይታ ዞን አስ...
11/04/2026

የወላይታ ዞን አስተዳደር ከዞኑ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ጋር በመሆን ከካዎ ኮይሻ ወረዳ ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ ለሰፈሩት ወገኖች ማዕድ አጋራ

ጠበላ፤ሚያዚያ 03/2018 የወላይታ ዞን አስተዳደር ከዞኑ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ጋር በመሆን ከካዎ ኮይሻ ወረዳ ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ ለሰፈሩት ወገኖች የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓል መዋያ ስጦታ አበርክቷል።

በማዕድ ማጋራቱ የተገኙት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ እንኳን የትንሣኤ በዓል በሠላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከዚህ በፊት የገና በዓልን ከካዎ ኮይሻ ወረዳ ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ ለሰፈሩት ወገኖች ጋር አብሮ ማክበሩን አስታውሰዋል።

ዛሬ የትንሳኤ በዓልን በዞኑ ከካዎ ኮይሻ ወረዳ ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ የሚገኙ ወገኖች ራሳቸውን እስከሚችሉ ድረስ በዓሉን በጋራ ማክበር ትልቅ ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል።

እርስበርስ ተጋግዘንና ተደጋግፈን እንዲሁም አንድነታችን አጠናክረን በጋራ መሰራት ከቻልን አካባቢያቸውን መቀየር እንችላለን ብለዋል።

በስፍራው ለሚገኙ ህብረተሰብ ክፍሎች የዞኑ አስተዳደር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለማሟላት እየሰራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

አያይዘውም የዞኑ አስተዳደር አከባቢውን በልዩ ሁኔታ እየደገፈ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፥ ሌሎች መሠረታዊ የሆኑ መሠረተ ልማቶች ለማሟላት ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

በስፍራው የሚገኙ ተሳፋሪዎች ራሳቸው እስከሚችሉ ድረስ ጠንክረው መሰራት እንዳለባቸውም መክረዋል።

እንዲሁም አከባቢውን ለመቀየር የተለያዩ ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን መትከልና ማልማት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ብልፅግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት ከመጣ ወዲህ በጎ ተግባር ባህል ሆኖ መምጣቱን የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው፥ ፓርቲው ሰው ተኮር እንደሆነም ገልፀዋል።

በሁሉም አካባቢ ለተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚደረግ በጎ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።

በማዕድ ማጋራት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ፣ የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ፣ የዞኑ የመንግስት ረዳት ተጠሪዎች አቶ መስፍን ቶማስና ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤልን ጨምሮ የዞኑ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የጠበላ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸብር ዘካሪያስ ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና ትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ የመ...
10/04/2026

የጠበላ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸብር ዘካሪያስ ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና ትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል...

​ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤
​እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

​የስቅለት በዓል የፍቅር፣ የመስዋዕትነት፣ የትዕግስትና የይቅርታ ከፍተኛ ተምሳሌት ነው። ይህን ታላቅ በዓል ስናከብር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ድኅነት ሲል የከፈለውን ፍጹም ፍቅርና መስዋዕትነት በጥልቅ በማሰብና በመዘከር ሊሆን ይገባል።

​ይህ ታላቅ የመስዋዕትነት እና የፍቅር እሴት በዕለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ በማድረግ፣ እርስ በርስ በመዋደድ፣ በመተሳሰብ እንዲሁም ይቅር በመባባል አብሮነታችንን ይበልጥ ልናጠናክር ይገባል። በመሆኑም በዓሉን ስናከብር አቅም የሌላቸውንና የተቸገሩትን በማገዝ፣ የታመሙትን በመጠየቅና ያዘኑትን በማፅናናት ፍቅራችንን በተግባር እንድናሳይ አደራ እላለሁ።

​የከተማችንን ብሎም የሀገራችንን ሰላም፣ ልማትና ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ ሁላችንም በያለንበት የስራ መስክ በቅንነትና በታታሪነት መትጋት ይጠበቅብናል። የጀመርነውን የዕድገት ጉዞ ከዳር ለማድረስ የህዝባችን ጠንካራ አንድነት፣ መቻቻልና ትብብር ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ ነው። የበዓሉ መንፈስ ለበለጠ ስራ፣ መግባባትና ስኬት መነሳሳትን እንዲፈጥርልን እመኛለሁ።

​በድጋሚ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የተትረፈረፈ በረከት በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ።

​አቶ አሸብር ዘካሪያስ
የጠበላ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ
ሚያዝያ 02/2018 ዓ.ም
ጠበላ፣

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ!- ዶ/ር አማረ አቦታየትንሣኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ በመስቀል ላ...
10/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ!- ዶ/ር አማረ አቦታ

የትንሣኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ሁሉ በመስቀል ላይ እስከሞት ድረስ ራሱን አሳልፎ በመሰጠት ወደር የለሽ ፅኑ ፍቅር ያሳየበት እና ለበደሉት ሳይቀር ይቅርታ እና ምሕረትን የሰጠበት የድህነት በዓል ነው፡፡

የክርስቶስ መነሣት ተዘግቶ የሚቀር ነገር እንደሌለ አስተምሮናል። አይሁድ በመቃብሩ ላይ ድንጋይ ገጥመው ማኅተም ሲያትሙ ነገር ሁሉ አለቀ፤ ተጠናቀቀ ብለው ነበር። ያ ድምዳሜ ግን ሦስት ቀን ብቻ ነው የቆየው። ሞቱ በሕይወት፣ መቃብሩ በትንሣኤ ተሻረ።

ትንሣኤ ከጽናት በኋላ የሚገኝ ድል ነው። ከፊቱ የጅምላ ፍርድ፣ ውግዘት፣ ግርፋት፣ መራቆት፣ መከዳት፣ የፀሐይ መጨለም፣ የጨረቃ ደም መልበስ፣ የከዋክብትም መርገፍ አለው። በዚህ ሁሉ ግን በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ ክርስቶስ በጽናት ቆመ። ስለ ዓላማ ሲባል መከራን ታገሠ። ስለ ሰው ልጅ ሲባል ሁሉን እየቻለ በጽናት ተጓዘ።

ትንሣኤ የማሸነፍ በዓል ነው። ራሳችን እስካልተሸነፍን ድረስ ማንም ሊያሸንፈን እንደማይችል እንማርበታለን። ሮማውያንና አይሁድ በክርስቶስ ላይ የሚችሉትን ሁሉ አድርገው ነበር። ፈርደውበታል፤ ገርፈውታል፤ ጎትተውታል፤ ሰቅለውታል፤ ገድለውታል። በመጨረሻም በመቃብር ቀብረው መቃብሩን አትመውታል።

እነዚህ ሁሉ ነገሮች ኢየሱስ ክርስቶስን በመቃብር አሥረው ከትንሣኤ አላስቀሩትም። በትንሣኤ ሌሊት፣ ሞት ታሪክ መቃብርም ተረት ሆነ። ያ ሁሉ ግርግርና ጩኸት ከንቱ ሆነ። ከሞት አጠገብ ሕይወት፣ ከመቃብር አጠገብ ትንሣኤ ተገለጠ።

እንደሀገር ብሎም እንደ አከባቢያችን የማይቻሉ የሚመስሉትን ታላላቅ ፕሮጀክቶቻችንን በየደረጃው እያሳካን የመጣንበት ትልቁ ምስጢር ጠንካራ አንድነታችን ነው።

ስለሆነም ከመቼውም ጊዜ በላይ አንድነታችንን የሚሸረሽሩ ጉዳዮችን በፅናት በመታገል፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች ለሚሰራጩ የሀሰተኛ መረጃዎች ጆሮ ሳንሰጥ የጀመርናቸውን ሥራዎች አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል።

በዞኑ የተወዛዘፉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ርብርብ እየተደረገ ሲሆን ለዚህም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን ለማስተላለፍ እፈልጋለሁ።

ከፊታችን ግንቦት ላይ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የዴሞክራሲን ድል የምንቀዳጅበት፣ ወደ ቀጣይ ብሩህ ዘመን የምንሸጋገርበት በር ነው። በመሆኑም ሠላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ነጻና ተዓማኒ ምርጫ ለማካሄድ እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉም ሰው የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ በላቀ እንዲያበረክት ጥሪዬን አቀርባለሁ።

እንደሀገርና እንደዞናችን የተጀመሩ የልማት ስራዎች ለማስቀጠል፣ ሠላምን ለማጽናት፣ ዕድገትንና ለውጥ ለማምጣት፣ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚቻለው የብልፅግና ፓርቲ ምርጫ ምልክት የሆነው ስንዴ ነዶ መምረጥ እንደሆነ በዚህ አጋጣሚ አሳስባለሁ።

ሰላምና ልማት የሁለንተናዊ ብልፅግናችን መዳረሻዎች ናቸው። የሕዝባችን መሠረታዊ ፍላጎትም የሚረጋገጠው በልማት ነው። ልማት ደግሞ የሰላም ውጤት ነው። የሁሉም ስኬቶቻችን መሰረት የሆነውን ሰላማችን ለማረጋገጥ በጋራ መቆም፤ በቅንጅትና በትብብር መስራት ይኖርብናል።

ለተቸገሩ ማካፈል፤ ጧሪ ለሌላቸው መርዳትና ማዕድ ማጋራት ትናንትም ሆነ ዛሬ ሁነኛ የአብሮነታችን መገለጫ ነው።

ስለሆነም በዓሉን ስናከበር ባሕላችን እና ኃይማኖታዊ እሴታችን በሚፈቅደው መሠረት የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማሰብ በአብሮነት እና በመተባበር እንድናሳልፍ፤ በዓሉም የሰላም፣ የጤና፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆንልን እመኛለሁ።

በድጋሚ ለክርስትና እምነት ተከታዮች፥ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡

ዶ/ር አማረ አቦታ
የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

የጠበላ ከተማ አስ/ር ከንቲባ ዶ/ር ታረቀኝ ገቸሬ ለ2018 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት እና የትንሳኤ በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል            ...
10/04/2026

የጠበላ ከተማ አስ/ር ከንቲባ ዶ/ር ታረቀኝ ገቸሬ ለ2018 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት እና የትንሳኤ በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት እና ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ።

በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለይም በክርስትና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ መንፈሳዊ ክዋኔ እና ድምቀት ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና ትንሳኤ በዓል መሆኑ ይታወቃል።

"ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሳቱ ለህያዉ ተስፋና ለማይጠፋ ፥ እድፈትም ለሌለበት ፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምህረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ሃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኃል" (1ጴጥ 1፥3 - 5) እንደተባለዉ ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎ መሞቱና ከሙታን ተለይቶ መነሳቱ በየዓመቱ ይከበራል።

በዚሁ መሠረትም መላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች የጌታን ሕማማት በፆምና በፀሎት ሲያስቡ ሰንብተዉ የትንሣኤ በዓልን ያከብራሉ።

ለመላው የከተማችን ነዋሪዎች በሙሉ

የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰዉ ልጆች ፍቅር ሲል የከፈለውን መስዋዕትነት የምናስታውስበት ዕለት ስለሆነ እኛም የክርስቶስን መንገድ በመከተል በዓሉን ስናከብር በመተሳሰብ፣ በመረዳዳት፣ በወንድማማችነት፣ ያለው ለሌለዉ በማካፈል፣ በፍቅር እና በአንድነት መሆን አለበት እያልኩ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።

በከተማችን እየተሰሩ ያሉ የልማት ሥራዎች በተጀመረው ልክ ተጠናክሮ ቀጣይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ ሕዝባችን ከተማ መንግስት ጎን በመቆም የተለመደውን ድጋፉን አጠናክሮ እንድቀጥል በዚህ አጋጣሚ ላሳስባችሁ እፈልጋለሁ።

የከተማችን ማህበረሰብ በሙሉ የ7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሁሉም ዜጋ ህገመንግስታዊ መብቱን በመጠቀም በቀሪ ቀናት መራጭነት ካርድ በመውሰድ የሚበጀውን መንግስት መምረጥ እንዳለባችሁ ለመግለጽ እወዳለሁ።

በመጨረሻም ህብረተሰቡ በዓሉን ሲያከብሩ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ ነገሮችን በማስወገድ የበዓሉን ሰላማዊ ድባብ የሚያጠለሹ ነገሮችን ሲመለከቱ ለፀጥታ ተቋማት ጥቆማን በማቅረብ መተባበር ይገባል።

በዓሉ የሠላም፣የፍቅር እንዲሆን እየተመኘሁ በድጋሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

ዶ/ር ታረቀኝ ገቸሬ
የጠበላ ከተማ አስ/ር ከንቲባ
ሚያዝያ 02/2018 ዓ.ም
ጠበላ፣

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረ/ፕሮፌሰር  ሳሙኤል ተሰማ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።እንኳ...
10/04/2026

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ይህ በዓል የመስዋዕትነት፣ የፍቅር፣ የተስፋና የአዲስ መነሻ ምልክት ሲሆን፣ ለሰው ልጆች ሁሉ የአንድነትና የመተሳሰብ መልዕክት ይዞ ይመጣል።
በዚህ ታላቅ በዓል ወቅት የክርስቶስን ትምህርትን ፣ የጌታችን መስዋዕትነት ለሰው ልጆች ሁሉ ያሳየውን ከፍተኛ ፍቅርና ትህትና በማሳየት እሱ ያለምንም ጥፋትና ለሰው ልጆች ካለው ፍቅር የተነሳ በመስቀል ተሰቅሎ የሰውን ልጅ የኃጢአት ዕዳ ፅህፈትን የደመስበትን ይህን በማስታወስ፣ እኛም በራሳችን መካከል ይበልጥ መተሳሰብ፣ በመረዳዳትና ሰላምን በማጠናከር በዓሉን ማክበር አለብን።
መጽሐፍ እነደሚለው ፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። ፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
እሱም ለሰው ልጆች በመስቀል ተሰቅሎ ሞቶ አልቀረም። የገዥዎች፣ የፀሐፊዎች ክስ እንዲሁም የተቀበረበት መቃቢር ጠባቂዎች የርሱን ትንሣኤ ልከለክሉት አልቻሉም። በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ።
ትንሣኤው ደግሞ ከጭንቀት ወደ ደስታ፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከችግር ወደ ተስፋ የሚያመራ መልዕክት ነው።
እኛም እንደ ሀገር አሁን የሚገጥመንን የውስጥና የውጪ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን የነገ ሀገራችን ትንሣኤ ለማየት እርስበርስ በመደጋገፍ የሚንናፍቀውን የሀገራችንን ትንሣኤ እውን ሊናደርግ ይገባናል።
የወላይታ ዞን ሕዝብ ከሚታወቀው የአንድነትና የእርስ በርስ መረዳዳት ባህል ጋር ተያይዞ፣ በዚህ በዓል ወቅት የተቸገሩትን መርዳት፣ ከጎረቤትና ከወገን ጋር ፍቅርን መጋራት እንዲሁም ሰላምን መጠበቅ እንድንቀጥል አሳስባለሁ።
በተጨማሪም፣ በዓሉን በምናከብርበት ጊዜ ሕግን መከበር፣ ደህንነታችንን መጠበቅና አካባቢያችንን በንፁህነት መጠበቅ ሁላችንም የምንጋራው ኃላፊነት መሆኑን እንዳለበት እገነዘባለሁ።
በድጋሚ፣ እንኳን ለዚህ ክቡር የስቅለትና የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፤ በዓሉ ለሁላችም ሰላም፣ ፍቅር፣ ጤናና በረከት ይሁንላችሁ!

መልካም በዓል!
ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ
የወላይታ ዋና ዞን አስተዳዳሪ

 የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ ትናንት ምሽት 1.00 ሰዓት በደረሰዉ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ በሞቱት 7 ሰዎች ሞት የተሰማቸዉን ጥልቅ...
10/04/2026



የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ ትናንት ምሽት 1.00 ሰዓት በደረሰዉ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ በሞቱት 7 ሰዎች ሞት የተሰማቸዉን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።

አደጋዉ ባዴሳ ከተማ ዉስጥ ሰዎች እንቅስቃሴ እያደረጉ ባሉበት ሰዓት በመሆኑ የከፋ እንደሆነ የተናገሩት አዛዡ ከጋሞ ዞን ከሰል ጭኖ ሲጓዝ የነበረዉ ተሳቢ መኪና በዴሳ ከተማ ቁልቁለት ላይ የአደጋዉ ምክንያት ባልታወቄ ሁኔታ በከባድ ፍጥነት መንገድ ስቶ ከፊት ለፊት የነበረዉ ፎርስ ባጃጅ ላይ የነበሩ 2 ሁለት ወንድ በባለ ሁለት እግር ሞተር የነበሩ ሁለት ሰዎች አንድ ወንድ በአደጋ ከተጎዱ ቤቶች አራት ወንድ እና በተሳቢዉ ዉስጥ የነበሩ አንድ ወንድ አንድ ሴት በጠቅላላ 7 (ሰባት) ሰዎች በአደጋዉ በመሞታቸዉ የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል።

በአደጋዉ ከሞቱት በተጨማሪ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸዉ ወንድ ሁለት ሴት 2 አራት ሰዎች ከባድ ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን ቀላል ወንድ 1 ሴት 1 ለህክምና ወደ ባዴሳ ሆስፒታል ተልከዉ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸዉ መሆኑን ጠቅሰዉ ከህመማቸዉ በፍጥነት እንዲያገግሙ ፈጣሪ እንዲረዳቸዉ ተመኝቷል።

በአደጋዉ በንብረት ላይ የደረሰዉን ጉዳትና የአደጋዉን መንስኤ በማጣራት በተከታይ እንገልጻለን ብለዋል።

በመጨረሻም በአደጋዉ ምክንያት በሞቱ ወንድሞች ፈጣሪ ነፍሳቸዉን በአጸደ ገነት እንዲያሳርፍ ያዘኑ በተሰቦች ወዳጅ ዘመዶችና መላዉ የበዴሳ ከተማና ዳሞት ወይዴ ወረዳ ህዝብ በሙሉ ፈጣሪ መጽናናት እንዲሰጥ እመኛለሁ።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ።

በወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰባት ሰዎች ህይውት አለፈ።በአደጋው በአራት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ሲደረስ በሁለት ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት አስከትሏል።በደቡብ ኢት...
10/04/2026

በወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰባት ሰዎች ህይውት አለፈ።

በአደጋው በአራት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ሲደረስ በሁለት ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት አስከትሏል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ ትላንት ምሽት አንድ ሰዓት አከባቢ ከሶዶ ወደ ሀዋሳ ይጓዝ የነበረ ተሳቢ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ በከተማው ውስጥ ቀኙን በመልቀቅ በፍጥነት እያሽከረከረ መንገድ ላይ ቆመው የነበሩ ሞተር ሳይክልና ባጃጅ በመግጨት መንገድ ጥሶ በመውጣት ሶስት መኖሪያ ቤቶችን ደርምሶ መግባቱ የዞኑ ፖሊስ መረጃ አመላክቷል።

በዚህ አደጋም መንገድ ላይ ከነበሩ ተሽከርካሪዎች የባጃጁ ሾፌር ወድያው ህይወቱ ሲያልፍ የሞተር ሳይል አሽከርካሪው ከባድ የአካል ጉዳት ማስተናገዱ የተገለጸ ሲሆን ተሽከርካሪው የተጫናቸው ቤቶች ውስጥ ያሉ ሰዎችን የመታደጉ ስራ ፈታኝ እንደሆነ ተገልጿል።

አደጋው ከደረሰበት ሰዓት አንስቶ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ የተሳቢው አሽከርካሪና መንገድ ላይ የገጨው የባጃጅ ሾፌርን ጨምሮ የሰባት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በአራት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት እንዲሁም በሁለት ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መመዝገቡን የዞኑ ፖሊስ ያደረሰን መረጃ አመላክቷል።

በንብረት ላይ የደረሰው የጉዳት መጠንና የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ አከባቢው ተደጋጋሚ መሠል የትራፊክ አደጋዎች የሚከሰቱበት መሆኑን ጠቅሶ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

መረጃ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ነው

አቶ ቸርነት ይስሐቅ የጠበላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ  #ቻሌንጁን በመቀላቀል 2,000 ብር ድጋፍ አድረገዋል። ከልብ እናመሰግናለን!
09/04/2026

አቶ ቸርነት ይስሐቅ የጠበላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ #ቻሌንጁን በመቀላቀል 2,000 ብር ድጋፍ አድረገዋል። ከልብ እናመሰግናለን!

አቶ ወገኔ ታደለ የጠበላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ  #ቻሌንጁን በመቀላቀል 2,000 ብር ድጋፍ አድረገዋል። ከልብ እናመሰግናለን!
09/04/2026

አቶ ወገኔ ታደለ የጠበላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ #ቻሌንጁን በመቀላቀል 2,000 ብር ድጋፍ አድረገዋል። ከልብ እናመሰግናለን!

Address

Humbo Tebela

Telephone

+464610481

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጠበላ ከተማ አስተዳደር / Tebela Town Administration posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share