11/04/2026
በጠበላ ከተማ አስተዳደር አላታ ቀበሌ መንደር 04 በልዩ መጠሪያ ዉሃ ገንዳ ሠፈር በሕብረተሰብ ተሳትፎ 150 ሜተር የመንገድ ከፈታ ተደረገ።
ጠበላ፤ ሚያዝያ 03/2018 ዓ.ም በጠበላ ከተማ አስተዳደር በአላታ ቀበሌ መንደር 04 በልዩ መጠሪያ ዉሃ ገንዳ ሠፈር በሕብረተሰብ ተሳትፎ 150 ሜተር የመንገድ ከፈታ ተደርጓል።
መንገዱ በአከባቢው ህብረተሰብ ዘንድ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የቆየ ስሆን ዛሬ ምላሽ ማግኘቱ እንዳስደሰታቸው የአካባቢ ነዋሪዎች ይናገራሉ።
የአንድ አከባቢ ልማት የማከናውነው በመንግሥት ብቻ ሳይሆን የህብረተሰብ የነቃ ተሳትፎ ወሳኝ እንደሆነም ተገልጿል።
ዛሬ በቀበሌው የተጀመረው ልማት ሥራ በሁሉም ዘርፍ ተጠናክሮ የሚቀጥል ነው ተብሏል።