Awi Zone Environmental Protection

Awi Zone Environmental  Protection Creating awareness around environmental protection and its benefits over community

መጋቢት 13 (March 22) የዓለም የውሃ ቀን ውሃ ህይወት ላለው ነገር ሁሉ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ሀብት ነው። ዓለማችን 71% የሚሆነው መሬት በውሃ የተሸፈነ ነው። ይህ ደግሞ አስተማማኝ በሆ...
21/03/2026

መጋቢት 13 (March 22) የዓለም የውሃ ቀን
ውሃ ህይወት ላለው ነገር ሁሉ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ሀብት ነው። ዓለማችን 71% የሚሆነው መሬት በውሃ የተሸፈነ ነው። ይህ ደግሞ አስተማማኝ በሆነ የተፈጥሮ ዑደት አማካኝነት መጠኑ እንደተጠበቀ እንዲቆይ ተፈጥሮ ግድ ትላለች።
ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶች ውሃ በመባከኑ፣ የውሃ ፍጆታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱ እና የጥራት ይዘቱን በማጣቱ ሳቢያ የንፁህ ውሃ አቅርቦት እጥረት በብዛት ያጋጥማል።
የውሃ መጠን ማነስና የጥራት መጓደል የሰብል ምርትንና ብዝሃ ሕይወትን ይጎዳል። ሃገራችን ይበልጥ እየጎዳት የሚገኘው የኢኮኖሚ አቅማችን አናሳ በመሆኑና ትላልቅ ወንዞችን ጠልፎ የመጠጥ ውሃ ማቅረብ አለመቻሉ ነው።
በውሃ እጥረት ምክንያት ከሚፈጠሩ ዋና ዋና ክስተቶች መካከል፡- የሰብል ምርቶች መቀነስ፣ የቤትና የዱር እንሰሳት ሞት እና ስደት መጨመር፣ የእጽዋቶች መመናመን እና የበረሃ መስፋፋት፣ በመጠጥ ውሃ እጥረት የተነሳ የሰዎች ሞት እና ስደት መጨመር ናቸው።
የንጹህ ውሃ እጥረት ችግርን ለመፍታት ከሚወሰዱት እርምጃዎች ጥቂቶቹ፡- ውሃ መቆጠብ ሲሆን በምድር ላይ ያለ እያንዳንዱ ሰው ማድረግ ይችላል። የውሃ ፍጆታዎችን መጠን መቀነስ፣ የውሃ ፍሳሾችን መከላከል፣ የውሃ ቧንቧዎቹን በወቅቱ መቀየር እና የውሃ ሀብቶችን በምክንያታዊነት መጠቀም አስፈላጊ ነው። የዓለም የውሃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ መጋቢት 13 (March 22) የዓለም የውሃ ቀን በመባል ይከበራል፡፡ የዓለም የውሃ ቀን የተመሠረተው እ.ኤ.አ በ1992 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ከ1993 ጀምሮ በየዓመቱ ይከበራል፡፡ በዚህ ዓመት በዓለም አቀፍ ደረጃ ;ውሃ እና ጾታ; (Water and Gender) በሚል ጭብት ይከበራል፡፡ የዓለም የውሃ ቀን ጭብት “ውሃ በሚፈስበት፣እኩልነት ያድጋል” በሚል ኃይለኛ መፈክር የታጀበ ነው። ይህ ጭብጥ አንድን ተጨባጭ እውነታ ይመለከታል፡ የውሃ እጥረት እና የአካባቢ ጽዳትና ንፅህና እጦት በይበልጥ ሴቶችን እና ልጃገረዶችን ይጎዳል። በብዙ የዓለም ክፍሎች የፆታ ልዩነት እና የውሃ ድህነት በጣም የተሳሰሩ ናቸው። ውሃ ሲቸግር ሸክሙን የሚሸከሙት ሴቶች ናቸው ቀኑ መንግስታትን፣ድርጅቶችን፣ማህበረሰቦችን እና ግለሰቦችን ከውሃጋር በተያያዙ ተግዳሮቶች ላይ የበለጠ እንዲያውቁ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተደራሽነትን እና ጥራትን ለማሻሻል እርምጃ እንዲወስዱ ያበረታታል። ውሃ እንደ ሸቀጥ ብቻ እንዳልሆነ ለማስታወስ ያገለግላል፡፡
; ውሃ ህይወት ነው; እንከባከበው!!!

26/02/2026

Interaction in Ecosystem.

26/02/2026

የተፈቀዱ ኘላስቲኮች የትኞቹ ናቸው?
በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 መሰረት የፕላስቲክ ማሸጊያ ማለት እቃዎችን ከብክለት ለመከላከል ወይንም ከሌላ ነገር ጋር እንዳይቀላቀል ለማድረግ በእቃው አምራች ጥቅም ላይ የሚውል ከፕላስቲክ የሚዘጋጅ መጠቅለያ ወይም መያዣ ነው የሚል ትርጉም ተሰጥቶታል። በዚህም መሰረት የምግብ፣ የባልትና ውጤቶችን፣ ለላውንደሪ አገልግሎት እና ሌሎች ምርቶችን ለማሸግ የሚውሉ የፕላስቲክ ማሸጊያዎች በአዋጁ የተፈቀደ ሲሆን የእነዚህ ማሸጊያዎች የቆሻሻ አያያዝ በአዋጁ እና አዋጁን ተከትለው በሚወጡ የማስፈፀሚያ ህጎች የሚተገበር ይሆናል።
ፅዱ ኢትዮጵያን ባህል እናድርግ!
የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን

17/02/2026

በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 መሰረት “የፕላስቲክ ከረጢት” ማለት አነስተኛ ጥግግት ያለው፣ በቀላሉ በስብሶ ከአፈር ጋር የማይዋሃድ እና ሌሎች ምርቶችን ለመያዝ የሚያገለግል ነው በሚል ትርጉም እንደተሰጠው ይታወቃል፡፡ በዚሁ ትርጉም ላይ“….አነስተኛ ጥግግት….” የሚለው ሀረግ የፕላስቲክ ከረጢቶች የሚሰሩበት የፖሊመር ጥግግት አነስተኛ መሆንን፤ ከዚህም ጋር በተያያዘ አንፃራዊ የስስነት ባህሪ ለመግለፅ እና ከሌሎች ከፕላስቲክ ከተሰሩ በጣም ጠንካራ የእቃ መያዣዎች (ጀሪካኖች፣ የመዋቢያ ዕቃ መያዣዎች፣ የፕላስቲክ ውሀ መያዣዎች እና የለስላስ መጠጥ መያዣዎች) የተለዩ መሆኑን ለማመላከት ነው፡፡ በተሻረው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ አዋጅ ቁጥር 513/1999 መሰረት የፕላስቲክ ከረጢቶች ደረጃ ውፍረትን መሰረት ያደረገ የነበረ ሲሆን በዚሁ መሰረት ውፍረታቸው ከ0.03 ሚሊ ሜትር በላይ የሆኑ እና በስብሰው ወደ አፈርነት የሚቀየሩትን ብቻ ማምረት ወይም ወደ ሃገር ውስጥ ማስገባት የሚፈቅድ ነበር፡፡ ሆኖም በሀገር አቀፍ ደረጃ የፕላስቲክ ከረጢት አጠቃቀማችን ባለፉት 19 ዓመታት በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ፤ ከዚህም ጋር በተያያዘ በሰው እና በእንስሳት ጤና እንዲሁም በመሰረተ ልማት በተለይም የመንገድ የፍሳሽ ቦዮችን በመዝጋት በከተሞች የጎርፍ አደጋዎችን ሲያስከትሉ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በአብዛኛው ሲመረቱ የነበሩ የፕላስቲክ ከረጢቶች በአዋጁ የተቀመጠውን ዝቅተኛ መስፈርት የማያሟሉ እና በቀላሉ ወደ ቆሻሻነት የሚቀየሩ ነበሩ፡፡ ይህንንም ከግምት ውስጥ በማስገባት በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 የፕላስቲክ ከረጢቶች አጠቃቀም እና አመራረት ላይ ሙሉ ክልከላ የተደረገ ሲሆን ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሙሉ ትግበራ ላይ ይገኛል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ “አነስተኛ ጥግግት” የሚለው ሀረግ በተለምዶ ስስ ፌስታሎችን ብቻ የሚከለክል እና ወፍራም የሆኑ በተለምዶ እንደ ኩርቱ ፌስታሎች በአዋጁ ያልታገዱ መሆኑን የሚገልፁ የተዛቡ መረጃዎች እየተዘዋወሩ እንደሆነ ለመረዳት ችለናል፡፡ በመሆኑም በአዋጁ መሰረት በየትኛውም የውፍረት ደረጃ የሚገኝ ለምርት መያዣ የሚያገለግል የፕላስቲክ ከረጢት ሙሉ በሙሉ የተከለከለ መሆኑን በመረዳት ህብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት እጅግ አበረታች በሆነ መልኩ እያደረገ የሚገኘውን የፕላስቲክ ከረጢትን ከአገልግሎት ውጭ የማድረግ እና ተኪ በሆኑ ከወረቀት እና ከጨርቅ በተሰሩ የምርት መያዣዎች የመጠቀም ልምድ አጠናክሮ እንዲቀጥል እናሳስባለን፡፡

ምንጭ፡-ኢፌዲሪ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጠን

10/02/2026

How Trees Clean the Air?

86ኛው "የአገው ፈረስ ባህል" ክብረ በዓል የአብሮነት ቅርስ የሰላም ውርስ በሚል መሪ ቃል በእንጅባራ ከተማ በደማቅ ተከበረ።ምስል ከአዊ ኮሙኒኬሽን።
31/01/2026

86ኛው "የአገው ፈረስ ባህል" ክብረ በዓል የአብሮነት ቅርስ የሰላም ውርስ በሚል መሪ ቃል በእንጅባራ ከተማ በደማቅ ተከበረ።
ምስል ከአዊ ኮሙኒኬሽን።

"የአገው ፈረስ ባህል"ክብረበዓል የአገው ፈረስ ባህል በአገር አቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት በ2015 ዓ.ም የተመዘገበ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት ሳይንስና ባህል ድርጅት (UN...
24/01/2026

"የአገው ፈረስ ባህል"ክብረበዓል
የአገው ፈረስ ባህል በአገር አቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት በ2015 ዓ.ም የተመዘገበ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት ሳይንስና ባህል ድርጅት (UNESCO) ለማስመዝገብ አስፈላጊው ሁሉ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
የአገው ፈረስ ባህል ክብረ በዓል ጥር 23/2018 ዓ.ም ለ86ኛ ጊዜ በደመቀ ሁኔታ በእንጅባራ ከተማ ይከበራል፡፡ስለሆነም ከዋዜማው ጀምሮ በዓሉ በተለያዩ ዝግጅቶች ስለሚከበር እርስዎም የበዓሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከአክብሮት ጋር ተጋብዘዋል፡፡

09/01/2026

የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 የመጨረሻ ክፍል
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ዴንጋጌዎች
፳፫. የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አገሌግልት ክፍያ
፩/ ማንኛውም ሰው ለደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አገልግሎት ክፍያ የመፈጸም ግዴታ አለበት፡፡
፪/ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አገልግሎት ክፍያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ ይወሰናል።
፳፬. አስተዳደራዊ እርምጃዎች
ባለስልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ላይ ተፈጻሚ የሚሆን፣የክልል የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በክልል ደረጃ ተፈጻሚ የሚሆን መመሪያ በማውጣት ይህን አዋጅ በመተላለፍ በሚፈፀሙ የሚከተሉት አስተዳደራዊ ጥፋቶች ላይ የሚወሰድ አስተዳደራዊ እርምጃን እንደአካባቢ እና ነባራዊ ሁኔታው እያዩ ይወስናለ፡-
፩/ ከጉድፍ መጣያ ቦታ ውጭ በመኪና መንገድ፣ በእግረኛ መንገድ፣ በፓርኮችና በመሳሰሉ ቦታዎች ጉድፎችን መጣል፤
፪/ ከባለስልጣኑ ወይም ከክልል የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ፍቃድ ሳያገኝ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስራ ላይ መሰማራት፤
፫/ በዚህ አዋጅ ከተቀመጠው አግባብ ውጭ የደረቅ ቆሻሻን በማቃጠል ማስወገድ፤
፬/ በቆሻሻ ማሰባሰቢያ ማዕከል የተቀመጠ የቆሻሻ መያዣን ማውደም ወይም ጉዳት ማድረስ፤ ፭/ ደረቅ ቆሻሻን ከተሽከርካሪ፣ከመኖሪያ ቤት ወይም ከማንኛውም ቅጥር ግቢ አውጥቶ ወደ አልተፈቀደ ቦታ መወርወር፣ማስቀመጥ ወይም ማከማቸት፤
፮/ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ፣ አሰባሰብና አጓጓዝ ላይ እክል መፍጠር፤
፯/ ሳያስፈቅዱ አካባቢን የሚያቆሽሽ የማስታወቂያ ሥራ ማከናወን፤
፰/ የሞቱ እንስሳትን ለእነዚህ ተብለው ከተወሰኑ ቦታዎች ውጭ መጣል፤
፱/ በዚህ አዋጅ አንቀፅ ፲፬ በልዩ ሁኔታ ከሚፈቀድ ለአንድ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውል ፕላስቲክ በሚቃረን ሁኔታ ለአንዴ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውል ፕሊስቲክ፡-
ሀ) መጠቀም ወይ ለመጠቀም ይዞ መገኘት፤
ለ) ማምረት ወይም ወደ ሃገር ውስጥ ማስገባት፣ለገበያ ማቅረብ ወይም መሸጥ፣ ለንግድ ዓላማ ማከማቸት ወይም ይዞ መገኘት፤
፲/ ሌሎች በጥናት የሚለዩ መሰል ጥፋቶች።
፳፭. የወንጀል ተጠያቂነት
፩/ ማንኛውም ሰው የፕሊስቲክ ከረጢት፡-
ሀ) ከተጠቀመ ወይም ለመጠቀም ይዞ ከተገኘ ከሁለት ሺህ ብር በማያንስና ከአምስት ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፤
ለ) ካመረተ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ካስገባ፣ ለገበያ ካቀረበ ወይም ከሸጠ፣ ለንግድ አላማ ካከማቸ ወይም ይዞ ከተገኘ ከሀምሳ ሺህ ብር በማያንስና ከሁለት መቶ ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከአምስት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣሌ፡፡
፪/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተመለከቱትን የወንጀል ድርጊቶች የፈጸመዉ ህጋዊ ሰውነት ያለዉ ድርጅት በሚሆንበት ጊዜ የገንዘብ ቅጣቱ በንዑስ አንቀጹ የተመለከተዉን ሶስት እጥፍ ይሆናሌ፡፡
፫/ በዚህ አንቀጽ የተመለከተው የወንጀል ተጠያቂነት በዚህ አዋጅ እና አዋጁን ተከትሎ በሚወጣ መመሪያ መሰረት ሊወሰዱ የሚችሉ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን የሚያስቀር አይሆንም።
፳፮. ደንብና መመሪያ የማውጣት ሥሌጣን
፩/ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህንን አዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ደንቦችን ሊያወጣ ይችላል፡፡
፪/ ባለሥሌጣኑ ይህን አዋጅ እና በዚህ አዋጅ መሰረት የሚወጣውን ደንብ ለማስፈፀም የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን ሊያወጣ ይችላል፡፡
፳፯. የተሻሩና ተፈፃሚነት የሌላቸው ሕጎች
፩/ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ አዋጅ ቁጥር ፭፻፲፫/፩ሺ፱ሺ፺፱ በዚህ አዋጅ ተሽሯል፡፡
፪/ ይህንን አዋጅ የሚቃረን ማንኛውም አዋጅ፣ደንብና መመሪያ ወይም ልማዳዊ አሰራር በዚህ አዋጅ የተደነገጉትን ጉዳዮች በተመለከተ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡
፳፱. አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ
ይህ አዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጸና ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ ሐምሌ ፳፬ ቀን ፪ሺ፲፯ ዓ.ም
ታዬ አፅቀ ስላሴ
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ፕሬዘዲንት

"እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችን ለመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤አደረሰን!!!"በዓሉን ስናከብር የእርድ ተረፈ-ምርቶችን በአግባቡ በማስወገድ አካባቢያችንን ...
06/01/2026

"እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችን ለመድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤አደረሰን!!!
"በዓሉን ስናከብር የእርድ ተረፈ-ምርቶችን በአግባቡ በማስወገድ አካባቢያችንን ከብክለት እንጠብቅ!

03/01/2026

የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 ቀጣይ ክፍል...
ክፍል አምስት
የአስፈፃሚ ወይም ሌሎች ተቋማት ተግባርና ኃሊፊነት
፲፱. የከተማ አስተዳደር ግዴታ
በዚህ አዋጅ ሌሎች ድንጋጌዎች የተመለከተው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም የከተማ አስተዳደር፡-
፩/ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ መሰረተ ልማቶች በከተማ ፕላን በግልፅ ማመላከት፤
፪/ ዝቅተኛውን የአስተዳደር እርከኑንና የአካባቢውን ማህበረሰብ መነሻ ባደረገ አሳታፊ የአሰራር ዘዴ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ ዕቅድ አዘጋጅቶ የመተግበር፤
፫/ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ እና የአካባቢ መንከባከቢያ የግንዛቤ ማስፋፊያ መርሃ ግብር የማቀድና የማከናወን፤
፬/ ከደረቅ ቆሻሻ አያያዝ ጉድለት ሊደርስ የሚችል ብክለትን መከላከል የሚያስችል ስራ መከናወኑን የማረጋገጥ፤
፭/ የጉድፍ ማስቀመጫዎችን በመንገድ ዳር እና ህዝብ በሚያዘወትርባቸዉ ቦታዎች ማስቀመጥ፤ በየጊዜዉ መፅዳታቸዉን ማረጋገጥ፤
፮/ የመንገድ ፅዳት ሥርዓት የመዘርጋት፤
፯/ አካባቢን የሚያቆሽሹ የማስታወቂያ ሥራዎችን የመቆጣጠር፤
፰/ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ ላይ ወቅታዊ የአካባቢ ኦዲት በማከናወን ሪፖርቱን ለባለ ሥልጣኑ ወይም ለክልል የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤቶች ማቅረብ፤
፱/ አግባብነት ያላቸው ወጪ ቆጣቢ እና ለአጠቃቀም ምቹ የሆኑ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝን የሚያግዙ ቴክኖልጂዎች ሥራ ላይ መዋላቸውን የማረጋገጥ፤
፲/ በከተማዉ ዉስጥ የሚገኙ የወንዝ ዲርቻዎች፣ የገበያ ቦታ፣ የህዝብ ማዘዉተሪያ ቦታዎች፣ አረንጓዳ ስፍራዎች እና መሰለል ቦታዎችን ማፅዳት እና ቆሻሻ እንዲይጣልባቸዉ የመቆጣጠር፤
፲፩/ ዘሊቂነት ያለው የቆሻሻ አያያዝ ተግባራትን ማከናወኛ ፋይናንስ ምንጭና ሥርዓት መዘርጋት እና መኖሩን የማረጋገጥ፤
፲፪/ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያሳድግ የማበረታቻ ሥርዓት የመዘርጋት፤
፲፫/ ዓመታዊ የተቀናጀ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዘገባ ማዘጋጀት እና ለባለሥልጣኑ ወይም ለክልል የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት እና ለከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ወይም ለክልል የከተማ እና መሰረተ ልማት መስሪያ ቤት የማቅረብ፤
፲፬/ ደረቅ ቆሻሻን መልሶ ለመጠቀም፣መልሶ ዑደት በማድረግ እና በማስወገድ ስራ ላይ የሚሰማሩ ሰዎችን ለማበረታታት የሚያስችል እርምጃዎችን የመዉሰድ፤ግዴታ አለበት፡፡
፳. የገጠር ቀበሌ አስተዳደር ግዴታዎች
፩/ ማንኛውም የገጠር ቀበሌ አስተዳደር፡-
ሀ) በገጠር ቀበሌዎች የሚመነጭ የደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ መያዙንና መወገደን የማረጋገጥ፤
ለ) የደረቅ ቆሻሻ ዝውውርን የመቆጣጠር፤ግዴታ አለበት፡፡
፪/ ለከተማ አስተዳደሮች በዚህ አዋጅ የተሰጡ ሀላፊነቶች እንደአስፈሊጊነቱ ለገጠር ቀበሌ አስተዳደሮችም ይሰራለ::
፳፩. በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ የኢንተርፕራይዞች እና የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ
፩/ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ የሚሰማሩ የኢንተርፕራይዞች እና የግሉ ዘርፍ ከባለሥሌጣኑ ወይም አግባብነት ካለው የክልል አካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ፈቃድ ማውጣትና ፍቃዳቸውን በየዓመቱ ማሳደስ አለባቸው፡፡
፪/የከተማና የገጠር አስተዳደሮች እንደ አስፈሊጊነቱ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አገልግሎቶችን በጥቅል ወይም በተናጠል ለግል ባለሀብቶች፣መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ወይም ኢንተርፕራይዞች ሊያስተላልፉ ይችላሉ፡፡
፫/ የከተማ አስተዳደሮች በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞችና የግል ተቋማት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አለባቸው፡፡
፳፪. የሙያ ደኀንነት፣ጤንነትና የሥራ አካባቢ
፩/ ማንኛውም በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ የተሰማራ ተቋም የሠራተኞችን ደኅንነትና ጤንነት በሚገባ ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ እርምጃዎችን መውሰድ ይኖርበታል፡፡
፪/ በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ወይም በሌሎች ህጎች ላይ የተደነገገው የሙያ ደኀንነት፣ ጤንነትና የሥራ አካባቢ መስፈርቶች በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ ለተሰማሩ ሰዎችም ተግባራዊ ይሆናል፡፡
ክፍል ስድስት ይቀጥላል …

የሠደድ እሳት ምንድን ነው?እሳት ጠላትም ወዳጅም ሊሆን ይችላል፡፡የሰደድ እሳት ማለት በደን ላይ ተፈጥሮአዊ በሆነና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚደርስ የደን ቃጠሎ ሲሆን በአብዛኛው የሚከሠተው በ...
30/12/2025

የሠደድ እሳት ምንድን ነው?
እሳት ጠላትም ወዳጅም ሊሆን ይችላል፡፡የሰደድ እሳት ማለት በደን ላይ ተፈጥሮአዊ በሆነና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚደርስ የደን ቃጠሎ ሲሆን በአብዛኛው የሚከሠተው በአገራችን ቆላና ቆላ ቀመስ በሆኑ ዘርዛራ ደኖች፤በቁጥቋጦና በግጦሽ ስፍራዎች ነው፡፡
ሰደድ እሳት በአካባቢ ላይ የሚያደርሰው ተፅዕኖ ፡-
የደን ሰደድ እሳት በአካባቢ ላይ የሚያደርሰው ተፅዕኖ ቅለት ወይም ክብደት የሚወሰነው በአካባቢው በሚገኘው የአፈር አይነት፤የአፈር እርጥበት፤በተከሰተው እሳት ስፋት እና የተከሰተበት ወቅት እንዲሁም እሳቱ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በአካባቢው በሚኖረው እርጥበት አዘል የአየር ሁኔታ ነው፡፡
በማዕድን ይዘቱ የላቀ አፈር ለእሳት የመበገር ባህርይ በብስባሽ ከዳበረው ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ነው፡፡በማዕድን ይዘቱ የበለፀገ አፈር ከእሳት ጋር ሲገናኝ እንፋሎቱ ወደ አፈር ውስጥ ሰርጎ ስለሚገባ ለእሳት በፍጥነት መስፋፋትና በምድር ውስጥ ለውስጥ መዛመት አያመችም፡፡በብስባሽ የዳበረ አፈር ግን አፈሩ በቀላሉ እንዲቀጣጠልና እንዲነድ አመቺ ሁኔታ ከመፍጠሩ በተጨማሪ እሳት በጥልቀት ወደ ምድር ውስጥ ዘልቆ በመግባት እንዲስፋፋ ያደርጋል፡፡እንደዚህ አይነቱ እሳት ለማጥፋት እጅግ ከባድ በመሆኑ ሳይጠፋ ለረጅም ጊዜ ሊቆይ ይችላል፡፡
የሰደድ እሣት መንስኤዎች
የሰደድ እሳት የሚከሰትባቸውን ምክንያቶች በሁለት አብይ ክፍሎች መመደብ ይቻላል፡፡እነዚህም ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ተብለው ይጠቀሳሉ፡፡የሠው ልጅ ደህንነቱን ለማረጋገጥ የተሻለ ኢኮኖሚ ወይም ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት በሚያካሂደው ተግባርና ይህንንም ሲያደርግ በቸልተኝነትና ሳያስበው የሚያስነሣው የሰደድ እሳት መንስኤው ራሱ የሰው ልጅ በመሆኑ አደጋው ሰው ሰራሽ አደጋ ተብሎ ይጠቀሳል፡፡
ከዚህ በተቃራኒው ከሰው ልጅ ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ጉዳዮችና ካለምንም የሰው ልጅ ጣልቃ ገብነት የሚከሰት የሰደድ እሳት ተፈጥሮአዊ ተብሎ ይታወቃል፡፡
ሀ) በተፈጥሮአዊ ክስተት፡-
ቁጥቋጦና ደን ባሉባቸው አካባቢዎች ለረዥም ወራት የሚቆይ ደረቅና ሞቃታማ የአየር ሁኔታ ለሰደድ እሳት አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ደረቅና ሞቃታማ አየር የዛፎችን ቅጠልና ቅርጫፍ እንዲሁም አነስተኛ ተክሎችንና ሳርን በማድረቅ እሳት ሲነሳም በቀላሉ እንዲቀጣጠል በማድረግ ለሰደድ እሳት መዛመት አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመብረቅና ዛፎች እርስ በርስ በሚያደርጉት ፍትጊያ የሰደድ እሳት መነሻ መክንያት ይሆናሉ፡፡በእንዲህ አይነት ተፈጥሮአዊ ምክንያት የሚነሳ የሰደድ እሳት በአገራችን ደረቅና ቆላማ አካባቢዎች ከፍተኛ የደን ውድመት ሲያደርስ ቆይቷል፡፡
ለ) በሰው ሰራሽ ምክንያቶች የሚከሰት የሰደድ እሳት፡-
ሰው ሰራሽ በሆነ ምክንያት የሚደርስ የሰደድ እሳት ሲባል ሆን ተብሎ ደን ለማቃጠል ታስቦ የሚፈፀም ድርጊትን ብቻ የሚያመለከት አይደለም፡፡በሰው ልጅ ቸልተኝነትና መዘናጋት ምክንያት የሚደርስ የሰደድ እሳትም ምድቡ በዚህ በሰው ሰራሽ ምክንያት ውስጥ ነው፡፡ሰው ሰራሽ ለሆኑ የሰደድ እሳት መነሳት ምክንያቶች በርካታ ናቸው፡፡ በዚህ ፅሁፍ የምንዳሰስው በአገራችን በተደጋጋሚ ለከፍተኛ የደን መጥፋት ምክንያት የሆኑት አራት ሰው ሰራሽ ተግባራትን ብቻ ነው፡፡ሰው ሰራሽ የሰደድ እሳት የሚነሳው የእርሻ መሬት ለማስፋት ፤ከሰል ለማክሰል ፤ከባህላዊ ማር ቆረጣና ከአደን ጋር የተገናኙ ስራዎች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
በደን ውስጥ የተከለከሉ ድርጊቶች
በሚመለከተው አካል ደንብና መመሪያ መሰረት እውቅና ከተሰጠው የደን አጠቃቀም በስተቀር በመንግስት ደን ውስጥ፡-
• የደን ወሰን ምልክቶችን ማጥፋት፣ማበላሸት ወይም ማዛባት፣እሳት መለኮስ ወይም ለእሳት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ
ተግባራትን መፈፀም ወይም በማናቸውም ሌላ ሁኔታ በደን ላይ ጉዳት ማድረስ፣የቤት እንስሳትን በደን ውስጥ ለግጦሽ ማሰማራት፣ያለ ህጋዊ ፈቃድ አደን ማካሄድ፣ በሚመለከተው አካል ካልተፈቀደ በስተቀር በመንግስት ደን ክልል ውስጥ መስፈር፣የእርሻ ቦታ ማስፋፋት፣የማዕድን ስራ ማካሄድ፣ የመንገድ ስራ፣ የግድብና የአፈር ቁፏሮ እንዲሁም የድንጋይ መሰብሰብ፣ ስራ ማካሄድ የተከለከለ ነው፡፡
ሰደድ እሳትን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት
 በደን ውስጥ ወይም በአካባቢው የሚኖሩ፣የሚሰሩ፣የሚተላለፉ ሁሉ ተቀጣጣይ ነገሮች እንዳይይዙና እሳት እንዳይነሳ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ግንዛቤ ማስጨበጥ፡፡
 በልዩ ልዩ ምክንያቶች ተቆርጠው የተከማቹ የዛፍ ቅሪቶች ማለትም ሳር፣ቅጠላ ቅጠል፣ቅርፊትና ቅርንጫፎች ደርቀው ለእሳት መነሳት ምክንያት እንዳይሆኑ አስቀድሞ ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር በመተባበር ማስወገድ፣
 በደንና በእርሻ ማሳ እንዲሁም በመኖሪያ ሰፈርና በደን መካከል የእሳት መከላከያ መስመሮችና መንገዶችን አስቀድሞ መስራት ፤በየጊዜው መጠገን፣
 በደን ወሰን ዙሪያ ሊያቋቁሙና በፍጥነት መሬቱን በመሸፈን ከስር የሚበቅለውን ሳርና ቁጥቋጦ ሊቆጣጠሩ የሚችሉ የዛፍ ዝርያዎችን አጠጋግቶ መትከል፣
 እንደማሳሳትና ምልመላ የመሳሰሉ ተግባራትን ለእሳት ምቹ የሆነው ወቅት እስኪያልፍ ድረስ ማዘግየት ወይ አስቀድሞ በማከናወን የዛፍ ቅሪቶችን ማስወገድ፣
 ሣር በሚበዛበት ደን ወቅቱን ጠብቆ ሣሩ ታጭዶ እንዲነሣ ማድረግ፡፡ በደኑ ላይ ጉዳት የማያስከትል መሆኑ ከተረጋገጠ ከብቶች ገብተው እንዲግጡ ማድረግ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ስለሆነም ከዚህ ወር ጀምሮ ከፊታችን ያሉት ወራት ሞቃታማ በመሆናቸው በደን ሀብቶቻችን ላይ ሰደድ እሳት ተነስቶ ጉዳት እንዳያደርስ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን እናስገነዝባለን፡፡
ምንጭ፡- አካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ከሚሽን (በቀድሞው ስያሜ)

28/12/2025

Address

Amhara Region
Injibara

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Awi Zone Environmental Protection posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Awi Zone Environmental Protection:

Share