21/03/2026
መጋቢት 13 (March 22) የዓለም የውሃ ቀን
ውሃ ህይወት ላለው ነገር ሁሉ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ሀብት ነው። ዓለማችን 71% የሚሆነው መሬት በውሃ የተሸፈነ ነው። ይህ ደግሞ አስተማማኝ በሆነ የተፈጥሮ ዑደት አማካኝነት መጠኑ እንደተጠበቀ እንዲቆይ ተፈጥሮ ግድ ትላለች።
ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶች ውሃ በመባከኑ፣ የውሃ ፍጆታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱ እና የጥራት ይዘቱን በማጣቱ ሳቢያ የንፁህ ውሃ አቅርቦት እጥረት በብዛት ያጋጥማል።
የውሃ መጠን ማነስና የጥራት መጓደል የሰብል ምርትንና ብዝሃ ሕይወትን ይጎዳል። ሃገራችን ይበልጥ እየጎዳት የሚገኘው የኢኮኖሚ አቅማችን አናሳ በመሆኑና ትላልቅ ወንዞችን ጠልፎ የመጠጥ ውሃ ማቅረብ አለመቻሉ ነው።
በውሃ እጥረት ምክንያት ከሚፈጠሩ ዋና ዋና ክስተቶች መካከል፡- የሰብል ምርቶች መቀነስ፣ የቤትና የዱር እንሰሳት ሞት እና ስደት መጨመር፣ የእጽዋቶች መመናመን እና የበረሃ መስፋፋት፣ በመጠጥ ውሃ እጥረት የተነሳ የሰዎች ሞት እና ስደት መጨመር ናቸው።
የንጹህ ውሃ እጥረት ችግርን ለመፍታት ከሚወሰዱት እርምጃዎች ጥቂቶቹ፡- ውሃ መቆጠብ ሲሆን በምድር ላይ ያለ እያንዳንዱ ሰው ማድረግ ይችላል። የውሃ ፍጆታዎችን መጠን መቀነስ፣ የውሃ ፍሳሾችን መከላከል፣ የውሃ ቧንቧዎቹን በወቅቱ መቀየር እና የውሃ ሀብቶችን በምክንያታዊነት መጠቀም አስፈላጊ ነው። የዓለም የውሃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ መጋቢት 13 (March 22) የዓለም የውሃ ቀን በመባል ይከበራል፡፡ የዓለም የውሃ ቀን የተመሠረተው እ.ኤ.አ በ1992 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ከ1993 ጀምሮ በየዓመቱ ይከበራል፡፡ በዚህ ዓመት በዓለም አቀፍ ደረጃ ;ውሃ እና ጾታ; (Water and Gender) በሚል ጭብት ይከበራል፡፡ የዓለም የውሃ ቀን ጭብት “ውሃ በሚፈስበት፣እኩልነት ያድጋል” በሚል ኃይለኛ መፈክር የታጀበ ነው። ይህ ጭብጥ አንድን ተጨባጭ እውነታ ይመለከታል፡ የውሃ እጥረት እና የአካባቢ ጽዳትና ንፅህና እጦት በይበልጥ ሴቶችን እና ልጃገረዶችን ይጎዳል። በብዙ የዓለም ክፍሎች የፆታ ልዩነት እና የውሃ ድህነት በጣም የተሳሰሩ ናቸው። ውሃ ሲቸግር ሸክሙን የሚሸከሙት ሴቶች ናቸው ቀኑ መንግስታትን፣ድርጅቶችን፣ማህበረሰቦችን እና ግለሰቦችን ከውሃጋር በተያያዙ ተግዳሮቶች ላይ የበለጠ እንዲያውቁ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተደራሽነትን እና ጥራትን ለማሻሻል እርምጃ እንዲወስዱ ያበረታታል። ውሃ እንደ ሸቀጥ ብቻ እንዳልሆነ ለማስታወስ ያገለግላል፡፡
; ውሃ ህይወት ነው; እንከባከበው!!!