03/06/2026
የመንግስትን እጅ ሳያጠብቁ፣ በራሳቸው አቅምና አደረጃጀት ተዓምር መስራት እንደሚቻል የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር የ05 ቀበሌ ነዋሪዎች በተግባር አሳይተዋል።
እንጅባራ | ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (የእንጅባራ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን)
የቀበሌው አመራሮችና የልማት አስተባባሪዎች እንደገለጹት፤ ይህ የባህላዊ ድልድይ ግንባታ ጊዜያዊ መፍትሄ ቢሆንም፣ ህዝቡ በራሱ ተነሳሽነት ችግሩን ለመቅረፍ ያሳየው ቁርጠኝነት ወደፊት ለሚሰሩ ዘላቂ የኮሪደርና የልማት ስራዎች ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ ነው። "ይህ ጅምር ነው፤ በቀጣይም ከከተማው አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ዘላቂ ድልድይ እስኪሰራ ድረስ ልማታችንን አናቆምም" ሲሉ በኩራት ተናግረዋል።
ይህ በ05 ቀበሌ የታየው ህዝባዊ መነሳሳትና የአንድነት አርአያነት ለሌሎች የእንጅባራ ከተማ ቀበሌዎችም ጭምር ትልቅ ትምህርትና የልማት መቀስቀሻ ደወል ነው። የከተማችንን ውበትና ምቹነት ለመመለስ የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ፣ እንደዚህ አይነት የህዝብ ተሳትፎዎች ሲታከሉበት ጉዟችንን ያፈጥነዋል።
ክብር ለቀበሌ 05 ንቁና ልማት ወዳድ ነዋሪዎች!
የእንጅባራ ከተማ ዕድገት በህዝብና በመንግስት የጋራ ክንድ ይረጋገጣል!