Injibara Communication

Injibara Communication Injibara communication

የመንግስትን እጅ ሳያጠብቁ፣ በራሳቸው አቅምና አደረጃጀት ተዓምር መስራት እንደሚቻል የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር የ05 ቀበሌ ነዋሪዎች በተግባር አሳይተዋል። እንጅባራ | ግንቦት 26/2018 ...
03/06/2026

የመንግስትን እጅ ሳያጠብቁ፣ በራሳቸው አቅምና አደረጃጀት ተዓምር መስራት እንደሚቻል የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር የ05 ቀበሌ ነዋሪዎች በተግባር አሳይተዋል።
እንጅባራ | ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (የእንጅባራ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን)

የቀበሌው አመራሮችና የልማት አስተባባሪዎች እንደገለጹት፤ ይህ የባህላዊ ድልድይ ግንባታ ጊዜያዊ መፍትሄ ቢሆንም፣ ህዝቡ በራሱ ተነሳሽነት ችግሩን ለመቅረፍ ያሳየው ቁርጠኝነት ወደፊት ለሚሰሩ ዘላቂ የኮሪደርና የልማት ስራዎች ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ ነው። "ይህ ጅምር ነው፤ በቀጣይም ከከተማው አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ዘላቂ ድልድይ እስኪሰራ ድረስ ልማታችንን አናቆምም" ሲሉ በኩራት ተናግረዋል።

ይህ በ05 ቀበሌ የታየው ህዝባዊ መነሳሳትና የአንድነት አርአያነት ለሌሎች የእንጅባራ ከተማ ቀበሌዎችም ጭምር ትልቅ ትምህርትና የልማት መቀስቀሻ ደወል ነው። የከተማችንን ውበትና ምቹነት ለመመለስ የመንግስት ጥረት እንዳለ ሆኖ፣ እንደዚህ አይነት የህዝብ ተሳትፎዎች ሲታከሉበት ጉዟችንን ያፈጥነዋል።
ክብር ለቀበሌ 05 ንቁና ልማት ወዳድ ነዋሪዎች!
የእንጅባራ ከተማ ዕድገት በህዝብና በመንግስት የጋራ ክንድ ይረጋገጣል!

የሀገራችን ህገ-መንግስት የመንግስት ስልጣን በህዝቡ ምርጫ እንደሚገኝና ይህም በየአምስት አመቱ እንደሚካሄድ ይደነግጋል ።በዚህ መሠረት 7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ግንቦት 24/2018 ዓ/ም ተካሂዷል...
03/06/2026

የሀገራችን ህገ-መንግስት የመንግስት ስልጣን በህዝቡ ምርጫ እንደሚገኝና ይህም በየአምስት አመቱ እንደሚካሄድ ይደነግጋል ።በዚህ መሠረት 7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ግንቦት 24/2018 ዓ/ም ተካሂዷል ።

የእንጅባራ ነዋሪዎችም በዚሁ ቀን ከ12:00 ሰዓት በፊት ቀድመው ጭምር በመሰለፍ ይሆነናል ያሉትን ፓርቲ ተመርጠዋል ።

በሀገረ መንግስት ግንባታ የማይናወጥ አቋም ያለው የከተማችን ህዝብ ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ጭምር ያደረጋችሁት ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ ምስጋና አቀርባለሁ ።

የእያንዳንዱ ዜጋ ተሳትፎ ለዴሞክራሲ ጥንካሬና ለሀገራችን ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው። በሂደቱ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ለአስፈፃሚዎች፣ ለታዛቢዎች፣ ለድጋፍ ሰጭዎች ሁሉ ምስጋና አቀርባለሁ ።

ተፎካካሪ ፓርቲዎች በእንጅባራ ከተማ የራሳቸውን ታዛቢ በማስቀመጥ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በሙሉ ጨዋነት ላደረጋችሁት ተሳትፎ ምስጋና እናቀርባለን ።

በምርጫ ሂደት ሰላምና መረጋጋት እንዲጠበቅ ላደረጋችሁት ሁሉ የፀጥታ አካላት (ለመከላከያ ሰራዊት፣ አድማና ጥምር ኃይል) ከልብ እናመሰግናለን። በትጋታችሁ ምርጫው በሰላማዊ ሁኔታ እንዲካሄድ አድርጋችኋል።

ለሀገራችን ሰላምና ዴሞክራሲ ሁሉንም ተፎካካሪ ፓርቲዎች እኩል ሚዛን በማስጠበቅ ያደረጋችሁትን አገልግሎት እናከብራለን፤እናመሰግናለን ።

"ነፃነት የምርጫ ሀይል ነው። ዛሬ የምትመርጠው ነገ የምትኖረው ህይወት ይገነባል" ይላሉ ምሁራን፦ በመሆኑም አሸናፊውን ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ይፋ እስኪያደርግ ድረስ በተለመደ አስተውሎትና ምክክር የጀመርነውን ልማት አጠናክረን በመቀጠል በጋራ እንደምንሰራ እያረጋገጥን በድጋሜ ምርጫው ሌሎች ባዳዎችና ባንዳዎች እንደተነበዩት ሳይሆን ፍፁም ሠላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ በእኔና በከተማ አመራሩ ስም ምስጋና አቀርባለሁ።

የዶክተር ሙሉነሽ ደሴ የምስጋና መልዕክት!! 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ፤ ነፃ፣ ፍትሐዊ፣ ተዓማኒነት ያለው እና ዲሞክራሲያዊ ቅቡልነቱን ያረጋገጠ ሆኖ በቅንጅትና በታላቅ ስኬት ተካሂዷል። ኢትዮጵያ እ...
03/06/2026

የዶክተር ሙሉነሽ ደሴ የምስጋና መልዕክት!!

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ፤ ነፃ፣ ፍትሐዊ፣ ተዓማኒነት ያለው እና ዲሞክራሲያዊ ቅቡልነቱን ያረጋገጠ ሆኖ በቅንጅትና በታላቅ ስኬት ተካሂዷል።

ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ያሸነፈችበት እና የብልፅግና እሳቤ በተግባር የተረጋገጠበት ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን።

ይህ ድል እንዲሁ በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን፣ ህዝባችን ከተጋረጡበት የጽ'ንፈኝ'ነት ትንኮሳዎች፣ ሴራዎችና የፀጥታ ስጋቶች ጋር በጽናት ታግሎ ያመጣው የጋራ ውጤት ነው።

​የክልላችን ህዝብ ታሪክ እንደሌሎች ወንድም ህዝቦች የኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ታሪክ ነው።

ህዝባችን ከጥንት ጀምሮ እንደማንኛው ኢትዮጵያዊ እስከ ዛሬ ድረስ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር፣ አንድነትን ለማጠናከር እና ጠንካራ የሀገረ መንግስት መዋቅር ለመዘርጋት ግንባር ቀደም መስዋዕትነትን ሲከፍል ኖሯል።

​በዚህ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅትም የታየው ይኸው እልህ አስጨራሽ ቁርጠኝነት ነው።

​ምርጫው እንዳይሳካ፣ ህዝብ በሰላም ወጥቶ ድምፁን እንዳይሰጥ እና የዴሞክራሲው ሂደት እንዲስተጓጎል የጽንፈኛ ሃይሎች ከውጭ ጠላቶቻችን ጋር ተቀናጅተው የከፈቱትን ሁለንተናዊ ትንኮሳ ህዝባችን በንቃትና በፅናት አክሽፎታል።

ጥይትና ሁከት ሳይሆን የህዝብ ድምፅ ብቻ ሉዓላዊ ስልጣን እንደሚያጎናጽፍ በተግባር በማሳየት፣ ህዝባችን ለሰላምና ለዲሞክራሲ መፅናት ያለውን ፅኑ አቋም በድጋሚ በዚህ በ7ኛው ምርጫ መስክሯል።

የሀገር የጋራ ድል ትርክትን በማንገብም፣ ከመላው ሀገሪቱ ያሉ ወንድሞቹ ጋር በመሆን ለሀገረ መንግስት ግንባታ ዘብ መቆሙን የክልላችን ህዝብ አረጋግጧል።

​ይህ ታሪካዊ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በድል እንዲጠናቀቅና ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ የሁሉም አካላት ቅንጅት ከፍተኛ ነበረ።

ለዚህም ታላቅ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ የላቀ ምስጋናዬን ለማቅረብ እውዳለሁ:-

የክልላችን አመራሮች ፣ምርጫ አስፈፃሚዎች እንዲሁም ሀገር ውስጥና የውጭ ታዛቢዎች ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን ላሳያችሁት ቁርጠኝነት፣ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ታዛቢዎች ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ላደረጋችሁት ገንቢ ተሳትፎ፣
የህዝብን ደህንነት በመጠበቅና ሰላም እንዲሰፍን ሌት ተቀን ለደከማችሁት የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ የአድማ መከላከል እና የፖሊስ አባሎቻችን እንዲሁም በየደረጃው ለምትገኙ የፀጥታ መዋቅሮች በሙሉ ምስጋናዬ ከልብ ነው።

​የጋራ አንድነታችንና ፅናታችን ሀገራችንን ወደላቀ ከፍታ ማሸጋገሩ አይቀሬ ነው።

​ዶክተር ሙሉነሽ ደሴ
በአብክመ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!!
የአዊ ብልጽግና ፓርቲ ገጽ

የእን/ከ/አስ/መ/ቤት ቀደም ሲል በቁጥር ከተ/መ/875/01/03 በቀን 14/09/2018 ዓ.ም ባወጣው ይፋዊ ማስታወቂያ መሠረት፣ የተራዘመው የመሬት ሊዝ ጨረታ ሰነድ ሽያጭ ሊጠናቀቅ 2 ቀናት...
03/06/2026

የእን/ከ/አስ/መ/ቤት ቀደም ሲል በቁጥር ከተ/መ/875/01/03 በቀን 14/09/2018 ዓ.ም ባወጣው ይፋዊ ማስታወቂያ መሠረት፣ የተራዘመው የመሬት ሊዝ ጨረታ ሰነድ ሽያጭ ሊጠናቀቅ 2 ቀናት ብቻ ቀርተውታል።

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ  ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ...
03/06/2026

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

አማራ ኮሚኒኬሽን

ህዝባችን የሚወክለውን መንግስት በድምፁ እየመረጠ ነው!ግንቦት 24/2018ዓ/ም( እንጅባራ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን)
01/06/2026

ህዝባችን የሚወክለውን መንግስት በድምፁ እየመረጠ ነው!
ግንቦት 24/2018ዓ/ም( እንጅባራ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን)

የህዝብን ጤና በተገቢው መንገድ ለመጠበቅ፣ አክሞ ከማዳን ይልቅ ቀድሞ መከላከል ቀዳሚውና ዋነኛው መርህ ነው!» — እንጅባራ ከተማ አስተዳደር።እንጅባራ | ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (ዕንጅባራ...
29/05/2026

የህዝብን ጤና በተገቢው መንገድ ለመጠበቅ፣ አክሞ ከማዳን ይልቅ ቀድሞ መከላከል ቀዳሚውና ዋነኛው መርህ ነው!» — እንጅባራ ከተማ አስተዳደር።
እንጅባራ | ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (ዕንጅባራ መንግስት ኮሙኒኬሽን)

ለበርካታ ዓመታት የከተማዋና የአካባቢው ማህበረሰብ ደጋግሞ ሲያነሳው የነበረው፣ የወገኖቻችንን ህይወት በታደገው «የደም ባንክ ይሰራልን!» ጥያቄ አሁን ላይ ታሪክ ሊሆን ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል። የከተማው ነዋሪዎች ላቀረቡት አንገብጋቢ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በተጀመረው የተቀናጀ ርብርብ፣ የደም ባንኩ ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ሊጠናቀቅና ለህዝብ አገልግሎት ሊውል ተቃርቧል።
የህዝባችን ጤና የልማታችን መሰረት ነው!

የደጋዋ ገነት እንጅባራ በአዲስ ገጽታ ተሞሽራለች! !የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና ከተማና የተፈጥሮ በረከት ማህደር የሆነችው ውቧ እንጅባራ ከተማ፣ በአረንጓዴውና ማራኪው ተፈጥሮዋ ላይ አሁን...
28/05/2026

የደጋዋ ገነት እንጅባራ በአዲስ ገጽታ ተሞሽራለች! !
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና ከተማና የተፈጥሮ በረከት ማህደር የሆነችው ውቧ እንጅባራ ከተማ፣ በአረንጓዴውና ማራኪው ተፈጥሮዋ ላይ አሁን ደግሞ የዘመናዊነትን ድንቅ ልብስ ደርባለች። ከተማዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ በሚገኘው የኮሪደር ልማትና የመሰረተ ልማት ግንባታ ሳቢያ አዲስና ማራኪ ገጽታን ተላብሳለች።
እንጅባራ ግንቦት 20/2018ዓ/ም (እንጅባራ መንግስት ኮሙኒኬሽን)
የዲች ቦይና የኮብልስቶን ንጣፍ ግንባታ፦ የከተማዋን የፍሳሽ ማስወገጃ ሥርዓት ለማስተካከል የሚረዱ የዲች ቦይ ስራዎች እና ውበትን ከተግባራዊነት ጋር ያጣመሩ የኮብልስቶን መንገዶች በጥራትና በከፍተኛ ፍጥነት እየተገነቡ ይገኛሉ።

የባሕር በሩ ይደመራል************የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ  የአንዲት ታላቅ ሀገር የህልውና፣ የፍትሕ እና የዘላቂ ኢኮኖሚ ደህንነት ጉዳይ ነው። ዛሬ ላይ ይህን አንገብጋቢ ሀገራዊ ...
27/05/2026

የባሕር በሩ ይደመራል
************

የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የአንዲት ታላቅ ሀገር የህልውና፣ የፍትሕ እና የዘላቂ ኢኮኖሚ ደህንነት ጉዳይ ነው። ዛሬ ላይ ይህን አንገብጋቢ ሀገራዊ ፍላጎት ለመመለስ የሚኬድበት መንገድ በዜሮ ድምር (Zero-sum game) የፖለቲካ ሸፍጥ እና ጉልበት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን፣ "መደመር" በሚለው እሳቤ ላይ የቆመ ነው።

የባሕር በሩ ይደመራል፤ ይህ መደመር ግን የሌላውን ሉዓላዊነት በመጋፋት አሊያም በማስገደድ መንጠቅ ማለት አይደለም። ይልቁንም፣ የጋራ ተጠቃሚነትን (Win-Win)፣ የወል እውነትን ማዳበርን እና የላቀ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደትን ማረጋገጥ ነው።

የመረጃ እና የኢኮኖሚ እውነታዎች ሲፈተሹ
ጉዳዩን በመረጃ ስንመዝነው፣ የባሕር በሩ ለኢትዮጵያ የቅንጦት ሳይሆን የእስትንፋስ ያህል ወሳኝ መሆኑን እንረዳለን።

• የህዝብ ብዛት እና ገበያ፡- ከ130 ሚሊዮን በላይ ብርቱ እና ወጣት ህዝብ ያላት፣ እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚውን አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የያዘች ሀገር፣ የባሕር በር አልባ ሆና መቀጠሏ ተፈጥሯዊም ኢኮኖሚያዊም ግድፈት ነው።

• የሎጂስቲክስ ወጪ፡- ኢትዮጵያ በየዓመቱ ለወደብ ኪራይ እና ተያያዥ የሎጂስቲክስ ወጪዎች የምታወጣው በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ውድ ሀብት፣ ብሔራዊ የዕድገት ጉዟዋን ክፉኛ የሚፈታተን ማነቆ ነው።

• የንግድ ጥገኝነት፡- ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነው የገቢ እና ወጪ ንግዷ በተወሰኑ ኮሪደሮች ላይ ብቻ የተንጠለጠለ መሆኑ፣ ከሀገራችን የህዝብ ቁጥር ዕድገት እና ከታቀደው የኢንዱስትሪ ሽግግር ጋር በፍጹም የሚመጣጠን አይደለም።

የመደመር እሳቤ እና የአፍሪካዊ ልማት ትስስር

ከመደመር እሳቤ አንፃር፣ ኢትዮጵያ እያቀረበች ያለው ጥያቄ "ኑ አብረን እንደግ፤ የኔ ግዙፍ የገበያ አቅምና የናንተ የውኃ በር ተደምሮ የቀጣናውን ህዝብ ከድህነት ያውጣ" የሚል የሰለጠነ የትብብር ጥሪ ነው። የመደመር ፍልስፍና መነሻው ነባር አቅሞችን አዋህዶ፣ የጎደለውን ሞልቶ፣ በጋራ ማደግ ነው። የባሕር በሩ ወደ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ ሲደመር፣ ቀጣናዊ ትብብርና ወንድማማችነትን በላቀ ደረጃ ያሰፋል።

ይህ እሳቤ የአፍሪካን ሕዳሴ እና የኢኮኖሚ ትስስር በተግባር ለማሳየት የሚያስችል ኃይለኛ መሳሪያ ነው። የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በወደብ፣ በመንገድ፣ በባቡር እና በኃይል አቅርቦት ሲተሳሰሩ፣ ሰው ሰራሽ የቅኝ ግዛት ድንበሮች ያመጡት መከፋፈል ይሽራል። የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ፣ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ማዕቀፍ ውስጥ ትልቁን ትርጉም የሚሰጥ፣ ኢትዮጵያውያን እና አፍሪካውያን የራሳቸውን የልማት ጥያቄ በራሳቸው አቅም የመፍታት ብቃታቸውን የሚያረጋግጥ ፓን-አፍሪካዊ ራዕይ ነው።

ኢትዮጵያ በቀጣናው ፖለቲካ የዕዳ ሸክም (Liability) ወይስ የልማት ሞተር (Asset)?

በዚህ ቀጣናዊ ስሌት ውስጥ ሊሰመርበት የሚገባው ትልቁ ሀቅ የኢትዮጵያ ደካማ መሆን ለጎረቤቶቿ የሚያመጣው መዘዝ ነው። 130 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሀገር በድህነት እና በኢኮኖሚ መታፈን ውስጥ ከቆየች፣ የቀጣናው ሰላም፣ ደህንነት እና መረጋጋት አደጋ ላይ መውደቁ አይቀሬ ነው።

ተፈጥሯዊ የመተንፈሻ በሯ የተዘጋባት እና ከድህነት ጋር የምትታገል ኢትዮጵያ፣ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የእዳ ሸክም እና የተደራራቢ ቀውስ ምንጭ መሆኗ አያጠራጥርም። የሃብት እጥረት እና የኢኮኖሚ መቆለፍ የሚያስከትለው የህዝብ ፍልሰት እና የፀጥታ ስጋት፣ የሌላውን ሀገር ደጃፍ ማንኳኳቱ የማይቀር የተፈጥሮ ሕግ ነው።

በተቃራኒው፣ በመደመር እሳቤ ኢትዮጵያ ማደግ እና መበልፀግ ስትችል የቀጣናው የፀጥታ እና የኢኮኖሚ ዋስትና ትሆናለች። የባሕር በር አግኝታ ኢኮኖሚዋ ሲያገግም፣ አካባቢዋን በኢንቨስትመንት እና በንግድ ልውውጥ ጎትታ ታወጣለች። የኢትዮጵያ ብልፅግና የጎረቤቶቿም ብልፅግና ነው።

የባሕር በሩ ወደ ኢትዮጵያ ይደመራል። ይህ መደመር ግን የጥላቻን እና የጥርጣሬን ግድግዳ የሚያፈርስ፣ የወል እውነትን የሚያነግስ፣ የጋራ ፀጥታን የሚያረጋገጥ እና የቀጠናውን ህዝቦች በተስፋ ብርሃን በደመቀ የብልፅግና ጠረጴዛ ዙሪያ የሚያሰባስብ ነው። መደመር ከሌላው መቀነስ ሳይሆን ማብዛት መሆኑን፣ ማግለል ሳይሆን ማካፈል መሆኑን የባሕር በሩ ጥያቄ በተግባር ያረጋግጣል።

በአዶኒያስ ወ/አረጋይ

💻🏢በክልሉ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው ኮምፒውተሮች ተሰራጩ። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው ኮምፒውተሮችን ለዞኖች እና ለከተማ አ...
27/05/2026

💻🏢በክልሉ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው ኮምፒውተሮች ተሰራጩ።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገባቸው ኮምፒውተሮችን ለዞኖች እና ለከተማ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያዎች ድጋፍ አድርጓል።

በድጋፉ ላይ የተገኙት በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ደ.ር) ዘላቂ የኢኮኖሚ ግንባታን ለማረጋገጥ እና ሰላምን ለማጽናት በዕውቀት የለማ የሰው ኀይል መገንባት ወሳኝ መኾኑን ገልጸዋል።

ዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በጽናት መሻገር የሚችሉ እና ዘመኑን የዋጁ ዜጎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግም ነው የተናገሩት። መንግሥት ነገን አስቦ እየሠራ እንደኾነም ጠቁመዋል።

​የትምህርት ጥራትን ለማምጣት እና ትምህርትን ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም ጥሪ አቅርበዋል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኅላፊ ጥላሁን ወርቅነህ
የጸጥታ ችግሮች በትምህርት ዘርፉ ላይ ፈተና ቢኾኑም ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ የትምህርት ግብዓቶችን ለማሟላት ታቅዶ ሥራዎች እየተከናወኑ መኾኑን ገልጸዋል።

​የትምህርት ሥርዓቱን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን እና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ 2ሺህ 135 ኮምፒውተሮች ድጋፍ ተደርጓል ነው ያሉት።

በቀጣይም ቴክኖሎጂውን በሁሉም ትምህርት ቤቶች ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሠራ አስረድተዋል።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ኅላፊ ሙሉዓለም አቤ (ዶ.ር) ድጋፉ የሚሰጠውን የኦንላይን ፈተና ስኬታማ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። ድጋፉ ቁልፍ ችግሮችን የፈታ ነው፤ ብቁ ትውልድ ለማፍራትም ያግዛል ነው ያሉት።

​የሰሜን ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ምክትል ኅላፊ
የሺወርቅ ድረስ ክልሉ ያደረገው ድጋፍ የነበረውን የኮምፒውተር እጥረት የሚቀርፍ እና በኦንላይን ፈተና ለመስጠት ለሚደረገው ዝግጅት በትክክለኛው ጊዜ የደረሰ ትልቅ ግብዓት ነው ብለዋል። ለተደረገላቸው ድጋፍም አመሥግነዋል።

#ድጋፍ #ኢትዮጵያ🇪🇹
አሚኮ

Address

Awi Zone Injibara
Injibara

Telephone

+251582270279

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Injibara Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share