የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Jajura
  • የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት

የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት

በጃጁራ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች አፈፃፀም ተገመገመጃጁራ፦ ነሐሴ 28/12/2018 ዓ/ም (የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን )በጃጁራ ከተማ አስተዳደር...
03/09/2026

በጃጁራ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች አፈፃፀም ተገመገመ

ጃጁራ፦ ነሐሴ 28/12/2018 ዓ/ም (የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን )

በጃጁራ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የመንግስትና የፓርቲ ሥራዎች አፈፃፀም የእስከ አሁን ሥራዎች አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት መደረጉ ተገለፀ ።

መድረኩን የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ለይኩን ሱልዶሎና የከተማ አስተዳደሩ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክባሞ አባይነህ በጋራ መርተዋል ።

ለውይይት መነሻ የሚሆን የገቢ አሰባሰብ ፣ የንግድ ምዝገባና እድሳት ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፣ የግብርና ፣ የሠላምና ፀጥታ ሥራዎች ፣ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ሥራዎች እና የፓርቲ ሥራዎች አፈፃፀም ሪፖርት በጃጁራ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ሀንድሶ በኩል ቀርቧል ።

የቀረበውን የአፈፃፀም ሪፖርት መነሻ በማድረግ አመራር ፑሉ በስፋት ውይይት በማድረግ የነበሩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠልና ድክመቶችን በማረም በሁሉም ዘርፍ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል ።

በመድረኩ የከተማ አስተዳደሩ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላትና አመራር ፑሉ ተገኝተዋል ።

በጃጁራ ከተማ የጳጉሜን ቀናትን ለማክበር የጋራ የሥራ አቅጣጫ ተቀመጠጃጁራ ፦ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን )፦ በጃጁራ ከተማ አስተዳደር የአምስቱ ...
03/09/2026

በጃጁራ ከተማ የጳጉሜን ቀናትን ለማክበር የጋራ የሥራ አቅጣጫ ተቀመጠ

ጃጁራ ፦ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን )፦

በጃጁራ ከተማ አስተዳደር የአምስቱ የጳጉሜን ቀናት አከባበርን በማስመልከት በተዘጋጀው የማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ የከተማው አመራር ፑል ተወያይቶ የጋራ የሥራ አቅጣጫ አስቀመጠ።

በመድረኩ የተገኙት የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ለይኩን ሱልዶሎ እንደገለጹት፤ የጳጉሜን ቀናት አከባበር በሀገርም ሆነ በከተማ ደረጃ በኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶችን ለሕዝቡ ለማስገንዘብና አጉልቶ ለማሳየት የሚያስችል ነው።

በመድረኩ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀመጡት የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክባሞ አባይነህ በበኩላቸው፤ የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት በሀገርና በከተማ ደረጃ "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ-ግብሮች እንደሚከበር ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያመጣቻቸውን ዘርፈ-ብዙ ድሎች በማስቀጠል፣ ፈተናዎችን በጽናትና በፈጠራ በመሻገር በአሁኑ ወቅት በማንሰራራት ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ አብራርተዋል።

የዘንድሮው በዓል ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን በመጠቀም በስኬት እንደሚመራ ተመላክቷል።

የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት መርሃ-ግብር እንደሚከተለው ተከፋፍሎ ይከበራል፦

ጳጉሜን 1፦ የእመርታ ቀን
ጳጉሜን 2፦ የማንሰራራት ቀን
ጳጉሜን 3፦ የጽናት ቀን
ጳጉሜን 4፦ የኅብር ቀን
ጳጉሜን 5፦ የነገ ቀን

የጳጉሜን ቀናት ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ስኬቶች የሚደመሩበትና ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያ መሆኑ ተመላክቷል።

በመጨረሻም በአምስቱ የጳጉሜ ቀናት የሚከናወኑ መርሐግብሮች የተሳኩ እንዲሆን በከተማ እና በቀበሌ የሚገኙ አመራሮችና መላው ሕዝቡ ሚናውን እንዲወጡ ከመድረኩ አቅጣጫ ተቀምጧል ።

03/09/2026

የክልሉ መንግስት በገጠር እና በከተሞች የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ሁሉን አቀፍ ስራዎች ተጠናክረው
እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ

(ሆሳዕና፣ነሐሴ 27/2018)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ የዘንድሮውን የጳጉሜ ቀናት አስመልክቶ በጽ/ቤታቸው መግለጫ ሰጥተዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ የዘንድሮውን የጳጉሜ ቀናት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡

በሂደት ያጋጠሙ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በጽናት እየተሻገረች ስለመምጣቷም ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

ሀገራችን በአሁኑ ወቅት ሁለንተናዊ ለውጦችን በማስመዝገብ በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ መሆኗን አቶ ዘሪሁን አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ 3ኛ አመቱን ማስቆጠሩን የገለጹት ኃላፊው በነዚህ አመታት በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች ለቀጣይ ስራ መነቃቃት መፍጠሩን አስረድተዋል።

ያለፉት ዓመታት ጉዞ ድልም ፈተናም እንደነበረው የገለጹት ኃላፊው ተግዳሮቶችን በጽናት በመሻገር ረገድ የክልሉ መንግስት የነበረው ቁርጠኝነት የላቀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በየዓመቱ የጳጉሜ ቀናትን ለውጡንና የለውጡን ትሩፋቶች በሚያመላክቱ ስያሜዎች እና መሪ ሐሳቦች የግንዛቤ ፈጠራ ንቅናቄዎች ሲሠሩ መቆየቱን አቶ ዘሪሁን ጠቅሰዋል፡፡

በክልሉ በሁሉም መስክ የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች የላቀ ውጤት መመዝገቡን አቶ ዘሪሁን በመግለጫቸው አብራርተዋል።

የክልሉ መንግስት በገጠር እና በከተማ የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ሁለንተናዊ የልማት እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኃላፊው በመግለጫቸው ጠቅሰዋል።

በዋናነት በምግብ ዋስትና፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በመሰረተ ልማት በማህበራዊ አገልግሎቶች እና በሌሎችም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ እንደሚሰራም አብራርተዋል።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር ውስጥ ወደ ዓዲሱ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ ነው ሲሉም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የጳጉሜን ወር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ አንኳር ስኬቶችን የምንመዝንበትና ከወረቶቻችን ጋር የምንደምርበት፣ ድክመቶችን የምንገመግምበት እና ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ ዐዲስ ተስፋን የምንሰንቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው ብለዋል።

የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ ሀገራችን የምትገኝበትን ታሪካዊና ፖለቲካዊ ሁኔታዎች ታሳቢ ያደረገ ስለመሆኑም ኃላፊው በመግለጫቸው አብራርተዋል።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት የሚከበረው ሀገራችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ የሕዝብ ይሁንታ ያገኘው ፓርቲ መንግሥት የሚመሠርትበት፣ የተመረጠው መንግሥት ከሕዝብ የተጣለበትን ከፍተኛ ኃላፊነትና አደራ ለመወጣት በሚዘጋጅበት ወቅት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።

መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር እየተካሄደ ያለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ውጤቶችን ወደ ትግበራ ለማስገባት ጠንካራ ዝግጅት መደረግ ባለበት ታሪካዊ ወቅት መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር በዋናነት በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ ይሆናል ብለዋል።

የጳጒሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል የጋራ መሪ መልእክት ይከበራሉ ሲሉም ኃላፊው ጠቁመዋል።
ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፣
ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን፣
ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን፣
ጳጉሜን 4- የኅብር ቀን እና
ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎች እንደ ቅደም ተከተላቸዉ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበሩ አቶ ዘሪሁን በመግለጫቸው አመላክተዋል።

የዛሬ ንባብ የነገ አቅም ነው፤የዛሬ ቤተመጽሐፍት ደግሞ የነገ ትውልድ መሠረት መገንቢያ፣የፈጠራና የምርምር ማዕከል ነው፥ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)ጃጁራ፣ነሀሴ 28/2018(የከተማ አስተዳደሩ መንግስት...
03/09/2026

የዛሬ ንባብ የነገ አቅም ነው፤የዛሬ ቤተመጽሐፍት ደግሞ የነገ ትውልድ መሠረት መገንቢያ፣የፈጠራና የምርምር ማዕከል ነው፥ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)

ጃጁራ፣ነሀሴ 28/2018(የከተማ አስተዳደሩ መንግስት ኮሙኒኬሽን)

በሀዲያ ዞን ጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር በ15 ሚሊዮን 665 ሺህ ብር በላይ የገንዘብ ወጪ በዲያስፖራ አባላትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባው ዘመናዊ ዲጂታል የህዝብ ቤተ-መጽሐፍት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።

በዕለቱ በክቡር እንግድነት የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)እንደገለፁት፤ዛሬ የተመረቀው ዲጂታል የህዝብ ቤተመጽሐፍት ድንጋይ ሳይሆን የቀጣይ ትውልድ የዕውቀት ተስፋ፣ተማሪዎች እውቀታቸውንና ክህሎታቸውን የሚያሳድጉበት የዕውቀት ማዕከል ነው።

ቤተመጻሕፍት መጽሐፍት የሚቀመጥበት ብቻ አይደለም
የአንድ ልጅ ህልም የሚጀምርበት፣የተማሪዎች አስተሳሰብ የሚቀርጽበት ፣ጥያቄዎች ምላሽ የሚያገኙበት ፣የፈጠራና የምርምር ማዕከል ነው።

በመሆኑም ቤተመጽሐፍቱ የአንድ አካል ሳይሆን የህዝብ የጋራ ሀብት በመሆኑ ህዝቡ የልማት የዳር ተመልካች ሳይሆን የልማት ተሳታፊና ባለቤት እንዲሆን ቤተመመጽሐፍት ግንባታው በአጭር ጊዜ ለአገልግሎት እንዲበቃ ትልቅ አስተዋጽኦ የበረከቱ አካለትን አመስግነዋል።

በመጨረሻም ክቡር ዶክተር ዲላሞ አንዳንድ ያልተሟሉ ግብዓቶች እንዲሟሉ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የሀዲያ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን

03/09/2026
የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ስኬቶች በሚያሳይ መልኩ ይከበራሉ - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትየጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ማንሰራራት እና የተገኙ ሁለንተናዊ ስኬቶችን በሚያሳይ ...
02/09/2026

የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ስኬቶች በሚያሳይ መልኩ ይከበራሉ - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን ማንሰራራት እና የተገኙ ሁለንተናዊ ስኬቶችን በሚያሳይ መልኩ እንደሚከበሩ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ የ2018 የጳጉሜን ቀናት ስያሜዎችን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል እንደሚከበሩ ተናግረዋል።

ጳጉሜን 1 "የእመርታ ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ እለቱ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ የእድገት ጉዞ በመውጣት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች የሚዘከሩበት መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ኢትዮጵያ ያስመዘገበቻቸው እመርታዊ ለውጦች የሚዘከሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።

ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ እለቱ ኢትዮጵያ ወደ ሁለንተናዊ ልማት የተሸጋገረችበትን ጉዞ በሚያሳዩ ሁነቶች እንደሚከበር ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ከጎታች ማነቆ የወጣችበትና ማንሰራራቷም የሚገለጥበት መሆኑን አንስተዋል።
ጳጉሜን 3 "የጽናት ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ ታሪካዊ ጽናትን ማስቀጠልን የምናሳይበት ነው ብለዋል።

የጽናት ቀን ጀግኖች የሚወሱበትና አዳዲስ ጀግኖች የሚፈጠሩበት መሆኑን ገልጸዋል። በእለቱ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ የሰንደቅ አላማ የመስቀል መርሀ-ግብር እንደሚከናወንም ገልጸዋል።

ጳጉሜን 4 "የህብር ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ አንድነትን በሚያጸኑ ተግባራት እንደሚከናወን ገልጸዋል። የትብብር እና የምክክር እሴትን በሚያጎለብቱ ሁነቶች እንደሚከበር ተናግረዋል።

በእለቱ ለ150 ሺህ ሰዎች ነጻ የጤና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። የስፖርት፣ የተማሪዎች ድጋፍ፣ ማዕድ ማጋራት እና ደም ልገሳ በእለቱ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል መሆናቸውን አንስተዋል።

ጳጉሜን 5 "የነገ ቀን" በሚል እንደሚከበር ገልጸው፤ የዲጂታል መሰረተ ልማት እና የሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) መነሻ ባደረጉ ዝግጅቶች እንደሚከበር ተናግረዋል።(ኢዜአ)

የጃጁራ ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ቡድን የሆማቾ ከተማን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈጃጁራ (ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም) — የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን በያሆ...
02/09/2026

የጃጁራ ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ቡድን የሆማቾ ከተማን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት አሸነፈ

ጃጁራ (ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም) — የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን

በያሆዴ ካፕ እግር ኳስ ውድድር የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ቡድን የሆማቾ ከተማ አስተዳደርን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት በከፍተኛ የበላይነት ማሸነፉ ተገለፀ።

ጨዋታው ከተጀመረበት የመጀመሪያ ደቂቃ አንስቶ የማጥቃት ጨዋታን መርሆ ያደረገው የጃጁራ ከተማ እግር ኳስ ቡድን፣ የተሳለጠ የኳስ ቁጥጥር እና የፊት መስመር ውጤታማነትን በመጠቀም አራት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል። ለጃጁራ ከተማ የማሸነፊያ ግቦችን ነጋሽ ታደሰ፣ ማሙሽ በቀለ ፣ ከነዓን ለቻሞ እና ንጋቱ ላምባሞ እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ጎል ማስቆጠራቸውም ተገልጿል ።

የሆማቾ ከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ቡድን በበኩሉ ከሽንፈት ያልታደጋችውን አንድ ማጽናኛ ጎል ያስቆጠሩ ቢሆንም፣ ጨዋታው በጃጁራ ከተማ አስተዳደር ሙሉ አሸናፊነት ሊጠናቀቅ ችሏል።

02/09/2026

Address

Jajura

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጃጁራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share