Jimma Customs Youth Forum

Jimma Customs Youth Forum Peace Has No Alternative

በጅማ ቅ/ፅ/ቤት ለአዲስ የጉምሩክ ባለሙያዎች በሃኒ ላንድ ሆቴል አቀባበል ተደረገ===================ላለፉት ሶስት ወራት ፖሊሳዊ ስልጠና  እና የጉምሩክ አዋጅ፣ መመሪያዎችና ደንቦች...
24/05/2023

በጅማ ቅ/ፅ/ቤት ለአዲስ የጉምሩክ ባለሙያዎች በሃኒ ላንድ ሆቴል አቀባበል ተደረገ
===================

ላለፉት ሶስት ወራት ፖሊሳዊ ስልጠና እና የጉምሩክ አዋጅ፣ መመሪያዎችና ደንቦችን እንዲሁም የአካል ብቃት ስልጠና በደቡብ ፖሊስ ይርለም ከተማ ሙሉ ስልጠና ወስደው ወደ ቅ/ፅ/ቤት ለተመደቡ ሠራተኞች በሃኒ ላንድ
ሆቴል አቀባበል ተደረገ።

በአቀባበል ስነ ስርዓቱ የቅ/ቤቱ ከቡድን አስተባባሪ በላይ ያሉ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ መርጋ ቶለራ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል ።

የቅ/ጽ/ቤቱ የህግ ተገዥነት ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ጀምበሬ ምትኩም በተልእኮዎች ዙሪያ አጠቃላይ ስለ ቅ/ጽ/ቤቱ፣ ስለ እያንዳንዱ ጣቢያዎች ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም ገቢና ወጪ ኮንትሮባንድን አስመልክቶ ያለውን ሁኔታ አስረድተዋል ።

በተጨማሪም የቅርንጫፉ የኢንተለጀንስ እና ኮንቶሮባንድ ስራ ህደት አቶ ሀይሉ ታምሩ አዲስ ባለሙያዎች በጣቢያ አሰራር ማኑዋል ዙርያ ስልጠና በመስጠት ለሰልጣኞቹ የተሰጣቸው ኃላፊነት ከፍተኛ በመሆኑ ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን አደራ በላቀ ሁኔታ እንዲወጡ አስረድተዋል ።

በመጨረሻም አዳዲስ ባለሙያዎች እንድሁም ከቡድን በላይ ያሉ አመራሮች እና ዘርፎች ባሉበት በቅ/ጽቤቱ የትውውቅ ፕሮግራም በተዘጋጀት የእራት ግብዣ በመታደም ተጠናቋል።

የልህቀት ዓመት!!
Year of Excellence !!!

20/05/2023
በታክስና በጉምሩክ ህጎች አሰራሮች ዙሪያ በተማሪዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ውድድር ተጠናቀቀ***************************************በገቢዎች ሚኒስቴር የጅማ ቅ/ጽ/ቤት...
16/05/2023

በታክስና በጉምሩክ ህጎች አሰራሮች ዙሪያ በተማሪዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ውድድር ተጠናቀቀ
***************************************
በገቢዎች ሚኒስቴር የጅማ ቅ/ጽ/ቤት እና በጅማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት አስተባባሪነት ስካሄድ የነበረው በታክስ እና በጉምሩክ ህጎች አሰራሮች ዙሪያ በተለያዩ የደቡብ ምዕራብ እና ከጋምቤላ ክልል የሀገርቱ ክፍሎች በተማሪዎች መካከል ሲካሔድ የነበረው ውድድር በዛሬው ዕለት በሃኒ ላንድ ሆቴል በተደረገው የማጠቃለያ ውድድር ተጠናቋል፡፡

በውድድሩ ከተለያዩ የሀገራችን ደቡብ ምዕራብ ቀጠና እና ከጋምቤላ ክልል የተውጣጡ የአራት ትምህርት ቤት የአሸናፊዎች አሸናፊ ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ተማሪ ዙላል ጀማል ከጅማ አጠቃላይ ት/ቤት አንደኛ ተማሪ ተስፋ ጽዮን ዘለቀ ከአመያ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሁለተኛ ተማሪ እብስት አየው ከጋምቤላ ክልል አለይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሦስተኛ እንድሁም ተማሪ አብዱል ሀክም አብደላ ከሰቃ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከአንደኛ እስከ አራተኛ ደረጃ ይዘዋል፡፡

በውድድሩ ላይ ለተሳተፉ እና ደረጃ ለያዙ ተማሪዎች ታቢሌት እና ስልክ ሽልማት እንዲሁም ተማሪዎቹን ግንዛቤ በማስጨበጥ ለውጤት ላበቁ መምህራን የገንዘብ ሽልማት እንድሁም ተማሪዎች ለሚማሩበት ትምህርት ቤት ከአንደኛ እስከ አራተኛ ሁነው ላጠናቀቁ ደስክቶፕ ኮንፕዩቴር እና ጂፓስ ለእያንዳንዳቸው በሽልማት ፤ በገቢዎች ሚኒስትር የጅማ ጽ/ቤት ስራአስኪያጅ ተወካይ አቶ አብድሳ ኤደሳ እና በጉምሩክ ኮሚሽን የጅማ ቅ/ጽ/ቤት ስራአስኪያጅ አቶ መርጋ ቶለራ እጅ ተቀብለዋል፡፡

በውድድሩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት በጉምሩክ ኮሚሽን ጅማ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስክያጅ አቶ መርጋ ቶለራ፣ የገቢዎች ሚኒስቴር እና በጉምሩክ ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት የተማሪዎች የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር፤ በታክስ እና በጉምሩክ ህጎች ላይ በቂ እውቀት ያለው ትውልድን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ግብሩን በአግባቡ እና በወቅቱ የሚከፍል፣ ኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር እንደዚህ ያሉ ውድድሮች ወሳኝ መሆናቸውን የጠቀሱት የታክስ ስርዓት ዘርፍ ም/ስራአስክያጅ አቶ ነጋሶ አብድሳ በበኩላቸው ፣ በዘላቂነት የታክስ እና የጉምሩክ ስነስርዓት በትምህርት ስርዓት ላይ እንዲካተት ለማድረግ ከትምህርት ሚኒስትር ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በዚህ ውድድር ላይ የገቢዎች ሚኒስቴር ጅማ ቅ/ቤት እና የጉምሩክ ኮሚሽን ጅማ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች፣ የተማሪ ወላጆች፣ መምህራን እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል::

Address

Jimma Town
Jimma

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jimma Customs Youth Forum posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Jimma Customs Youth Forum:

Share