South Aari Prosperity Party - Qaats Aari Woobni Paarti

South Aari Prosperity Party - Qaats Aari Woobni Paarti South Aari woreda prosperity party office page

በደቡብ ኣሪ ወረዳ የኤልኒኖን ተፅዕኖ ለመቋቋም “ኤልኒኖን በመስኖ ውሃ አማራጮች እንጠቀም” በሚል መሪ ቃል ሰፊ የመስኖ ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።‎‎         ነሐሴ 2018 ዓ/...
07/09/2026

በደቡብ ኣሪ ወረዳ የኤልኒኖን ተፅዕኖ ለመቋቋም “ኤልኒኖን በመስኖ ውሃ አማራጮች እንጠቀም” በሚል መሪ ቃል ሰፊ የመስኖ ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

‎ ነሐሴ 2018 ዓ/ም
‎ ጋዘር

‎የደቡብ አሪ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ደይዳቆ በዞኑ በጨለጎድ ቀበሌ በኦምበት መስኖ ላይ በተለያዩ ሰብሎች 5 ሄክታር መሬት እየለማ ያለበትን ሁኔታ በቦታው ተገኝተው ተመልክተዋል።

‎በወረዳው የኤልኒኖን ተፅዕኖ ለመቋቋም በውሃ አማራጮች ለማልማት የታቀደው አጠቃላይ የመሄር ዕቅድ፦14,857.5 ሄክታር መሬት መሆኑን የገለጹት አቶ አሸናፊ ደይዳቆ፦ዕቅዱን ለማሳካት በተለያዩ የውሃ አማራጮች የታገዘ ሰፊ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎ በዚህም መሠረት፦
‎* በዘመናዊ መስኖ ፦9,817.1 ሄክታር
‎* በሞተር ፓምፕ ፦1,982.6 ሄክታር
‎* በምንጭ ፦1,230.23 ሄክታር
‎* በወንዝ፦1,111.6 ሄክታር እንዲሁም
‎* በእጅ ጉድጓድ፦716.02 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አብራርተዋል።

‎ወረዳዋ እጅግ ለም መሬት ያላት ከመሆኑም በላይ ወደ ታች ጥቂት ሜትሮች ብቻ ሲቆፈር ውሃ ማግኘት ብርቅ ያልሆነባት ምድር መሆኗን ኃላፊው ጠቁመዋል።

‎በመጨረሻም የውድ የወረዳው ማህበረሰብ አባላት ተረጅነትንና የተረጅነት አስተሳሰብን በጋራ በመታገል፣ በአሁኑ ወቅት የገጠመውን አስከፊውን የኤልኒኖ እና የላኒኖ ተፅዕኖ በትብብርና የባለሙያዎችን የግብርና ምክር ሐሳብ ተግባራዊ በማድረግ ማሸነፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለዚህም ስኬት ሁሉም የአካባቢው ማህበረሰብ አባል የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አቶ አሸናፊ ደይዳቆ ጥሪ አቅርበዋል።

#ደኣወመኮ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ቢሮ  ከኣሪ ዞን ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን  በጋዘር ከተማ አስተዳደር የአትሌቲክስ ስፖርት ምልመላ መጀመሩን  የኣሪ ዞን ባህልና ስፖር...
05/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ቢሮ ከኣሪ ዞን ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን በጋዘር ከተማ አስተዳደር የአትሌቲክስ ስፖርት ምልመላ መጀመሩን የኣሪ ዞን ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ ጋልሽ አሳውቁ።

ነ ሐ ሴ 30/12/2018ዓ,ም
ጂ ን ካ

በዚህ የምልመላ መረሃ- ግብር ላይ የክቡር እንግዳ ሆነው የጋዘር ከተማ አስተዳደር ም/ ከንቲባና የኢኮኖሚ ዘርፍ ክላስተር ኃላፊ አቶ ዘርሁን ሰይድ ከ4ቱ ወረዳና ከ3ቱ ከተማ አስተዳደሮች ለመጡ አትሌቶችና መልማይ እንግዶች እንኳን ወደ ውብቷ ጋዘር ከተማ በደህና መጣቹ መልዕክት በማስተላለፍ የዕለቱ ምልመላው ተጀምሯል።

መረጃው: የኣሪ ዞን ባህልና ስፖርት መምሪያ ነው

05/09/2026
 #እንኳን  #ደስ  #አላችሁ !!እንኳን ደስ አለን !!የደቡብ ኣሪ ወረዳ ብልፅግና የኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት የ2018በጀት  ዓመት አንደኛ ደረጃ በማግኘት የሰርተፍኬት ...
05/09/2026

#እንኳን #ደስ #አላችሁ !!እንኳን ደስ አለን !!

የደቡብ ኣሪ ወረዳ ብልፅግና የኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት የ2018በጀት ዓመት አንደኛ ደረጃ በማግኘት የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።

ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም
ጋዘር

የደቡብ ኣሪ ወረዳ ብልፅግና የኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት በኣሪ ዞን ከሚገኙ ከ7ቱ መዋቅሮች መካከል 1ኛ ደረጃ በማግኘት የ2018በጀት ዓመትን የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗል።

የኮሚሽኑ ቅ/ጽ/ቤት በአንድ ዕቅድ, በአንድ ምዘናና በአንድ ሪፖርት አፈፃፀም በዋናነት በተቋማዊ አሠራር,በሥነ ምግባርና ኢንስፔክሽን ሥራዎች በተለይ:-በኮሚሽኑ 4ቱ ስትራተጂክ ግቦች ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሰራ ስሆኑ ከግቦቹም ዋናዎቹ :-

1/በፓርቲዉ የፖሊቲካ ጤናማነትን ከማስጠበቅ አኳያ=-
2/ከፓርቲዉ ሀብት ,ንብረትና ሠነዶችን ለታለመለት ዓላማ ስለመዋል አጽንኦት ሰጥቶ ከመከታተል አንፃር :-

3/የአባላትና አካላት መብቶችከመከበርና ከማስጠበቅ አኳያ እና
4/ብልሹ አሠራሮችን ከመታገልና በፓርቲዉ መሪ ላይ ሆኖ የፓርቲውን አሠራር ከመትከል አንፃር ያደረገዉን ለኢንስፔክሽን ኮሚሽኑ ትጋትና ቁርጠኝነት ለዚህ ዉጤት እንደበቁ ተገልጿል ።

የተገኘው ዉጤትም የጽ/ቤቱ የሥራ አቅም የሚያሳይ እና የሚጠቁም ከመሆኑም በላይ ሥራዎችን የበለጠ ዉጤት ለማስመዝገብ ተጨማሪ ተነሳሽነትን የሚፈጥር መሆኑንም አመላክቷል ።

በስተመጨረሻም ለዚህ ሰርተፍኬት ሽልማት ዋጋ ለከፈሉትም አካላትን ማመስገን እንወዳለን ።
በተለይ ለወረዳዉ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ,ለወረዳዉ የኮሚሽን ቤተሰብ አመራሮች ,የወረዳችን አስተባባሪ ኮምቴዎች,የወረዳችን የፓርቲ ሥራ አመራሮች ,የወረዳችን አጠቃላይ አመራሮች እንዲሁም ዘወትር ድጋፋችሁና ክትትላችሁ ሁሌም ሳይለየን በጎናችን በመሆን ጽ/ቤታችንን በኢንስፔክሽንና በሱፐርቭዥን የደገፋችሁን የኣሪ ዞን ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎችንና የዞኑን ኮሚሽን ቤተሰብ አመራሮችን በወረዳችን ጽ/ቤት ሥም ምስጋናችን የላቀ ነዉ።

በቀጣይም የተጀመሩ መልካም ተሞክሮዎችንና ቀመሮችን በማስቀጠል የበለጠ ዉጤታማ ሥራ ለማከናወን እንደሆነ ይጠበቃል።

"ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ!!

የደቡብ አሪ ወረዳ ፍ/ቤት የባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም የወጣው አዋጅ ላይ ከአብይ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት አካሄደ።‎‎        ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም‎             ጋዘር  ‎‎...
04/09/2026

የደቡብ አሪ ወረዳ ፍ/ቤት የባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም የወጣው አዋጅ ላይ ከአብይ ኮሚቴዎች ጋር ውይይት አካሄደ።

‎ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
‎ ጋዘር

‎ የደቡብ አሪ ወረዳ ፍ/ቤት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋምና እውቅና ለመስጠት በወጣው አዋጅ ቁጥር 63/2017 ዙሪያ የጋራ ውይይት አካሂዷል።


‎ በውይይቱ ላይ የደቡብ አሪ ወረዳ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አድማሱ ታሪኩ አዋጁ ያለውን አስፈላጊነትና ወጪ ቆጣቢነት እንዲሁም ለባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት እውቅና በመስጠትና የባህል ሥርዓቶችን በማጠናከር ያለውን ሰፊ ሚና ገልጸዋል። በተጨማሪም ሥርዓቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የማቋቋም ሂደቱ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።


‎ በተጨማሪም የአብይ ኮሚቴዎች እንዳነሱት የባህላዊ ፍ/ቤቶች መኖር ቀላልና ወጪ ቆጣቢ የፍትሕ አገልግሎት በማቅረብ ያለውን ከፍተኛ ሚና በመግለጽ የባህላዊ ፍ/ቤቶች አደረጃጀት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት መሰራት እንዳለበት በመጥቀስ የባህላዊ ፍ/ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ ግንዛቤ መስጠት ላይ እና አደረጃጀት መረጣ ላይ ዕቅድ በማቀድ በቅንጅት ወደ ተግባር ለመግባት ተስማምተዋል።

መረጃው የደቡብ ኣሪ ወረዳ ፍርድቤት ነው!

የደቡብ ኣሪ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜ ቀናትን በልዩ ልዩ ኩነቶች ለማክበር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ።‎‎       ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም‎                 ጋዘር‎‎ በደቡብ...
03/09/2026

የደቡብ ኣሪ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜ ቀናትን በልዩ ልዩ ኩነቶች ለማክበር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ።

‎ ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም
‎ ጋዘር

‎ በደቡብ ኣሪ ወረዳ “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የሚከበሩትን የ2018 ዓ.ም የጳጉሜ አምስቱን ቀናት አስመልክቶ የየቀናቱን ስያሜዎች መሠረት ያደረጉ ልዩ ልዩ ኩነቶችን ለመፈጸም የሚያስችል ጉዳዮች ዙሪያ ከወረዳው የጳጉሜ ቀናት አብይ ኮሚቴ ጋር ሰፊ የውይይት መድረክ አድርጓል ።

‎የደቡብ ኣሪ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከወረዳው የጳጉሜ ቀናት አብይ ኮሚቴ ጋር በጋራ ለአከባበሩ አስፈላጊ በሆኑ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በጥልቀት መክረዋል።

‎በውይይቱ ላይ የጳጉሜ አምስቱ ቀናት እንደ አገር የተሰጧቸውን ትርጉም ያላቸውን ስያሜዎች መሠረት በማድረግ በወረዳው ደረጃ ህዝባዊ ተሳትፎንና አንድነትን በሚያጠናክሩ ተግባራት ለማክበር መግባባት ላይ ተደርሷል።

‎ #ደኣወመኮ

የኣሪ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ በሆኑት አቶ ሕዝቅኤል ጋርታ የተመሩ ልዑካን ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመፈፀም  ባስኬቶ  ዞን ገቡ ።ነሐሴ 28/2018ዓ/ም   ኣሪ ዞን/ጂንካ...
03/09/2026

የኣሪ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ በሆኑት አቶ ሕዝቅኤል ጋርታ የተመሩ ልዑካን ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመፈፀም ባስኬቶ ዞን ገቡ ።

ነሐሴ 28/2018ዓ/ም
ኣሪ ዞን/ጂንካ

በመድረኩ የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ የሆኑትን ክቡር ሕዝቅኤል ጋርታን ጨምሮ የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ እንድሁም የዞኑ ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ እንድሁም የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍና ሌሎች አመራሮች እየተሳተፉ ይገኙበታል።

የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት /Ari Zone Prosperity Party Branch Office/

‎የደቡብ ኣሪ ወረዳ"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት"ለሚለው ሀገራዊ ተልዕኮ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ምክር ቤቱን አቋቋመ።‎‎   ነሐሴ  27/2018 ዓ/ም‎                ጋዘር‎‎የደ...
02/09/2026

‎የደቡብ ኣሪ ወረዳ"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት"ለሚለው ሀገራዊ ተልዕኮ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ምክር ቤቱን አቋቋመ።

‎ ነሐሴ 27/2018 ዓ/ም
‎ ጋዘር

‎የደቡብ ኣሪ ወረዳ"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት"የአደጋ ስጋት ምክር ቤት ማቋቋምና ወቅታዊ የኢልኒኖ ስጋት ለመቋቋምም የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ምክክር መድረክ አካሂዷል።


‎ የእለቱ መድረክ የአደጋ ስጋት ምክር ቤት ማቋቋም፣ በወቅታዊ የአየር መዛባት እና በ2019 ዓ.ም የሥራ ዕቅድ ዙሪያ ያተኮረ ሰፊ የምክክር መድረክ መካሄደ ተችሏል።

‎ በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይም የወረዳው የአደጋ ስጋት ምክር ቤት በይፋ መቋቋሙ የተበሰረ ሲሆን የምክር ቤቱ መቋቋም ዋና ዓላማ በማንኛውም ጊዜ በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሽ ምክንያቶች አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት፣ የውስጥ አቅምን እና ሀብትን በተደራጀ መልኩ በመጠቀም ያለማንም የውጭ ጣልቃ ገብነትና ጥገኝነት የተጎዱ ወገኖችን በፍጥነት ለመደገፍና ለመታደግ የታለመ እንደሆነም የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ደይዳቆ ጠቁመዋል።

‎ ይህንኑ የሀብት ማሰባሰብ ሂደትና ምላሽ የመስጠት ተግባር ምክር ቤቱ በበላይነት እየመራ እንደሚያስቀጥል በመግለጽ በመድረኩ ላይ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ደይዳቆ ባቀረቡት ሪፖርት ሀገሪቱ የጀመረችውን "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" የመሸጋገር ብሔራዊ ተልዕኮ መነሻ በማድረግ በወረዳው የአደጋ ስጋት ጊዜን ለመቋቋም የተሰበሰበውን የእህልና የገንዘብ መጠን ይፋ አድርገዋል።

‎ በዚህ የሀብት አሰባሰብም እስከአሁን ድረስ ከ1,128,800 (አንድ ሚሊዬን አንድ መቶ ሃያ ስምንት ሺህ ስምንት መቶ ብር) በገንዘብ ተሰብስቦ ወደ ባንክ ገብ መሆኑና ከ210 ኩንታል በላይ እህል ተሰብስቦ ወደ እህል ማከማቺያ ማጋዝ መግባቱንም በሪፖርቱ አቅርበዋል።

‎ይህ የተሰበሰበው ሀብት ወረዳው ራሱን በራሱ ለመርዳትና ለአደጋ ስጋት ምላሽ ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል።

‎በሌላ በኩል፣ ወቅታዊውን የአየር መዛባት ተከትሎ ሊከሰት ይችላል ተብሎ ስለሚገመተው የ«ኢልኒኖ» (El Niño) ክስተት ዙሪያም በሰፊው ውይይት ተደርጓል።

‎ ክስተቱ በሰውና በእንስሳት ጤና እንዲሁም በኑሮ ላይ ሊያሰከትል የሚችለውን አደጋና ስጋት ከወዲሁ ለመከላከል ኅብረተሰቡ አስፈላጊውን የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች ላይ እንዲረባረብ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገብሬ ባይስማይ ጥሪ አቅርበዋል።

‎የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ትንሹ ተክሌ ባስተላለፉት የጥንቃቄ መልዕክት፦ሊከሰት ከሚችለው የኢልኒኖ አደጋ ራስንና አካባቢን ለመጠበቅ እያንዳንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ከወዲሁ በንቃት መዘጋጀትና የቅድመ መከላከል ሥራዎችን በተግባር መተርጎም እንዳለበት አሳስበዋል።

የደቡብ ኣሪ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የገጠር መሬት ገቢ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት የግብር ንቅናቄ መድረክ አካሄደ።‎‎      ነሐሴ -27/2018 ዓ/ም‎      ...
02/09/2026

የደቡብ ኣሪ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የገጠር መሬት ገቢ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት የግብር ንቅናቄ መድረክ አካሄደ።

‎ ነሐሴ -27/2018 ዓ/ም
‎ ጋዘር

‎የደቡብ ኣሪ ወረዳ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት የገጠር መሬት ገቢ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት የገጠር መሬት ግብር ንቅናቄ መድረክ በዛሬው ዕለት አካሂዷል።

‎ በመድረኩ ላይ የገጠር መሬት ግብር በሕገ-መንግሥቱ አዋጅ በተቀመጠለት መሠረት በአግባቡ የሚሰበሰብ መሆኑን የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስምኦን ተይዳክ ገልጸው፦ በቀጣይ በፊታችን ባሉ ጊዜያት ውስጥ የገጠር መሬት ግብር ሳይንዛዛ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰብስቦ ለታለመለት አላማ እንድውል ለማድረግ እንደ ጽ/ቤቱ ሙሉ በሙሉ ሀላፊነት ወስዶ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

‎በመድረኩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገብሬ ባይስማይ ባስተላለፉት መልዕክት፦የገጠር መሬት ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መሰብሰብ በቀጣይ በወረዳው የሚሰሩ ዘላቂ የልማት ሥራዎችን ለማፋጠን ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

‎አክለውም ግብር የመክፈል ግዴታን መወጣት ራስን በራስ የማስተዳደርና የአካባቢን ልማት በባለቤትነት የመደገፍ መገለጫ በመሆኑ መላው የወረዳችን አርሶ አደር የተጣለበትን አገራዊና ሕጋዊ ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቀርባለሁ።

‎በዚሁ የንቅናቄ መድረክ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገብሬ ባይስማይ፣የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ትንሹ ተክሌ፣ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ደይዳቆ፣ እና የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስምኦን ተይዳክን ጨምሮ የሚመለከታቸው ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ተገኝተው ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።

#ደኣወመኮ

የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሄደነሐሴ 26/2018ዓም ጂንካበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ስር በአሪ ዞን ፍትህ መም...
01/09/2026

የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን ለመከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሄደ

ነሐሴ 26/2018ዓም ጂንካ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ስር በአሪ ዞን ፍትህ መምሪያ የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽህፈት ቤት አማካኝነት ለታዋቂ የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚዎችና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ማሰራጨትን ለመቆጣጠርና ለመከላከል በወጣው አዋጅ ቁጥር 1185/2012 ዓ.ም እና በሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን የአሪ ዞን ፍትህ መምሪያ አቃቤህግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ብርሀኑ አለማየሁ በጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ላይ ሰነዶችን አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

የጂንካ ከተማ ፍትህ ፅሀፈት ቤት ሀላፊ አቶ ህዝቄል አምባው መድረኩ የሚዲያ ተጠቃሚዎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ የሚያጋሯቸው መረጃዎች ህጋዊ መስመርን የተከተሉ እንዲሆኑና የህብረተሰቡን ሰላምና አንድነት እንዳይጎዱ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና መጫወት እንዳለባቸው ግንዛቤ መስጠትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

የጂንካ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ካሌብ ከብቲመር አሁንላይ የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃ በሚድያ ላይ በግልፅ እየተፃፈ ሲሆን ይህም በህግ አግባብ ተጠያቂ የሚያደርግ መሆኑን ተረድተው ማህበረሰቡ ሊታረም ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎችም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ከቀን ወደቀን እየጨመረ የመጣና በግልፅ በፌስቡክና በሌሎችም ማህበራዊ ሚድያዎች እየተደረገ በመሆኑ ማህበረሰቡ ስለ አዋጁ ግንዛቤውን አግኝቶ ሊታረምና ህጉም ተግባራዊ መሆን ቢችል ለውጥ ይመጣል ሲሉ አስተያየታቸውን ሠጥተዋል።

#ኣዞመኮአ

Address

South Omo
Jinka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Aari Prosperity Party - Qaats Aari Woobni Paarti posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share