South Omo Zone Government Communications

South Omo Zone Government Communications This page belongs to the newly structured South omo zone gov't at Dimeka.

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዱር እንስሳት ጥበቃ ሽፋንን ለማሳደግና ተፈጥሮን በዘላቂነት ለመንከባከብ የተቀናጁ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሚገኝ ተገለፀነሐሴ 24/2018 ዓ.ም የተፈጥሮ ጸጋዎችንና ...
30/08/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዱር እንስሳት ጥበቃ ሽፋንን ለማሳደግና ተፈጥሮን በዘላቂነት ለመንከባከብ የተቀናጁ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሚገኝ ተገለፀ

ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም

የተፈጥሮ ጸጋዎችንና የዱር እንስሳት ሀብትን በዘላቂነት በመንከባከብ የጥበቃ ሽፋንን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኘውንና 197 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን "ታማ" የማህበረሰብ የዱር እንስሳት ጥበቃ ቦታ አያያዝና በቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የመከረበትን የቦርድ ስብሰባ በጂንካ ከተማ አካሂዷል።

የቦርድ መድረኩን የመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወይንቱ መልኩ፤ የክልሉን የዱር እንስሳት ጥበቃ ሽፋን ለማሳደግ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ጠቁመው፥ "ታማ" የማህበረሰብ ጥብቅ ስፍራ ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን አብራርተዋል።

ኃላፊዋ አክለውም፣ በአካባቢው የሚገኙትን የኦሞ እና የማጎ ብሔራዊ ፓርኮች ሕልውናና የሥነ-ምህዳር ትስስር ዘላቂ በሆነ መንገድ ለማስቀጠል የ"ታማ" ጥብቅ ስፍራ እንክብካቤ ወሳኝና ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በታማ የማህበረሰብ የዱር እንስሳት ጥበቃ ስፍራ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ተግባራትን አስመክተው ማብራሪያ የሰጡት የማህበረሰቡ ዋና አስተባባሪ አቶ ባርኬዴ ኩሉሜደሬ ሰፊ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የቦርዱ አባላትም የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም፣ ጥብቅ ስፍራው የተጣለበትን አገራዊና አካባቢያዊ ኃላፊነት ይወጣ ዘንድ ሁሉ አቀፍ ክትትልና ሙያዊ ድጋፍ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በተጨማሪም የቦርዱ አባላት በታማ ጥብቅ ስፍራ መተዳደሪያ ደንብ እና እስከ አሁን በተከናወኑ አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸሞች ላይ ጥልቀት ያለው ውይይት አካሂደዋል።

በቀጣይም ከአካባቢው ማህበረሰቦች ጋር የሚደረገው የጋራ ምክክር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተገለጸ ሲሆን፤ ከደቡብ አሪ ወረዳ የአሪ ማህበረሰብ ተወካዮች እንዲሁም ከሣላማጎ ወረዳ ከዲሜ፣ ከባጫ እና ከሙርሲ ማህበረሰቦች የተወጣጡ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች በተገኙበት በታማ የዱር እንስሳት ጥበቃ ስፍራ የጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ሰፊ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

30/08/2026
በምክክር የተሟሸው የመግባባት ዴሞክራሲ ነሐሴ 24፣ 2018  ዓ.ም በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሒደት ውስጥ ለረጅም ዓመታት ምላሽ ሳያገኙ የዘለቁ ጥያቄዎች መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ በተለይም ከፖለቲካ...
30/08/2026

በምክክር የተሟሸው የመግባባት ዴሞክራሲ

ነሐሴ 24፣ 2018 ዓ.ም

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሒደት ውስጥ ለረጅም ዓመታት ምላሽ ሳያገኙ የዘለቁ ጥያቄዎች መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ በተለይም ከፖለቲካ አካታችነት መጓደል ሳቢያ በርካቶች ሃሳባቸው እና ጥያቄያቸው ሳይደመጥ ቆይቷል፡፡

ይህም “ኢትዮጵያ ሁላችንም አላዳመጠችንም” የሚል ብሶት እና ቁጭትን መውለዱ አልቀረም፡፡

ለዚህ አብነትም ወደ ሀገራዊ ምክክሩ መክፈቻ ዕለት ወደ ኋላ እንመለስ፤ ሙዶ አኮን አስታወሳችኋት? ከደቡብ ኦሞ ዞን የካራ ማሕበረሰብ ተወካይ ሆና ምክክሩ ላይ የተሳተፈች ሴት ናት።

ሙዶ በቀጥታ ስርጭት ዓለም እየተመለከተው በነበረው የሀገራዊ ምክክር ድግስ እንዲህ አለች፡- “ለብዙ ዘመናት ታሪክን ከሩቅ ቆመን እንመለከት ነበር። ተናጋሪዎች እና ወሳኞች ሌሎች ነበሩ።

ዛሬ ግን ሀገሬ እንድናገር ጠርታኛለች።” በርግጥም ሀገራዊ ምክክሩ እንደሙዶ ሁሉ ሰሚ ብቻ የነበሩ በርካቶችን ተናጋሪ በማድረግ አዳምጧቸዋል። ለዘመናት የጠብና ቁርሾ ምክንያት የሆኑ ችግሮች እንዲፈቱ በር መክፈት ችሏል።

አለመግባባት አለመደማመጥ ፈተና ነው። ባለመግባባት መንገድ ብዙ ትውልዶች የገነቡት ተስፋ ለመፍረስ ከወር ያነሰ ጊዜ ሊበቃው ይችላል።

በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ሰላም፣ ፖለቲካዊ መረጋጋት እና የጋራ ሀገራዊ እድገት ለመገንባት በሚደረገው ረዥም ጉዞ ውስጥ፣ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ታሪካዊና ስልታዊ ምዕራፍ ሆኖ ተመዝግቧል።

በተለይም የዚህ ሂደት ስኬት፣ የመደመር መንግሥት አንግቦት የተነሳውን "የመግባባት ዴሞክራሲ" ፍልስፍና ከንድፈ ሀሳብ አልፎ በተግባር ያረጋገጠ ትልቅ ማሳያ ሆኗል። የመደመር አስተሳሰብ ዋነኛ ምሰሶ ሀገራዊ ጉዳዮችን በጋራ መግባባት፣ በጋራ ባለቤትነት እና በሰለጠነ የውይይት መንገድ መፍታት እንደሆነ በተደጋጋሚ ተረጋግጧል።

ታሪካዊው የምክክር ሂደት፣ የተወሰኑ የፖለቲካ ልሂቃን ብቻ የተደራደሩበትና የተስማሙበት ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ አልነበረም። ይልቁንም በልሂቃን ብቻ ሳይሆን ከመላው ሀገሪቱ ማዕዘናት የመጡ አርሶ አደሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እና አጠቃላይ ማህበረሰቡ በቀጥታ የተሳተፉበት ህብር ድምጾች የሰሙበትና አካታች ሂደት ነበር።

ኖቤል ተሸላሚው አርተር ሊዊስ “ብዝሃ ማንነት ባላቸው ሀገራት ሁሉ ካልተደመጠ አደጋ ነው” ይላል። ለዚህም ባህላዊውና አሸናፊው ሁሉንም የሚወስድበት ፖለቲካ በተከፋፈሉና በርካታ ብሔረሰቦች ባሏቸው ሀገራት ውስጥ እሳት ላይ ነዳጅ እንደ መጨመር ጽንፈኝነትንና መገለልን ሲጋብዝ መኖሩን ዋቢ ያደርጋል።

የመደመር ፍልስፍና ግን "እኔ ሳልሸነፍ አንተም ሳትሸነፍ በጋራ ማሸነፍ እንችላለን" በሚል የጋራ እሴት ላይ የቆመ ነው። ይህ አስተሳሰብ እያንዳንዱ ዜጋ በሀገሩ ጉዳይ ላይ እኩል ድምፅና ባለቤትነት እንዲኖረው ያደርጋል፤ ማንም ዜጋ ከጠረጴዛው ውጭ እንዳይቀር በር ይከፍታል። እንደሙዶ አኮ አይነት ዜጎችም በሀገራቸው ጉዳይ ሰሚ ብቻ ሳይሆን ውሳኔ ሰጪና ተናጋሪ እንዲሆኑ ያደርጋል።

መደመር በሃይልና በጫና ከመሸናነፍ ይልቅ በስክነትና በምክክር የወል ትርክትን መፍጠርን ያስቀድማል፤ ያረጀ ቂምና ጥርጣሬ በምክክር እሳት እንዲቀልጥ የማድረግ መርህም አለው።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ለመግባባት ዲሞክራሲ መረጋገጥ ትልቅ ማሳያ ሆኖ በኢትዮጵያ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።

የታሪክ መዛግብት እንደሚያሳዩት፣ በሀገሪቱ ቀደም ሲል የተደረጉ በርካታ የፖለቲካ ሽግግሮች የጥቂት ልሂቃን ድራማና የይስሙላ ስምምነት በመሆናቸው ዘላቂ ሰላም ማምጣት አልቻሉም ነበር።

የአሁኑ ምክክር የቀየረው ይሄንን መንገድ ነው። በሂደቱ ከአራቱም የሀገሪቱ ማዕዘናት የተወጣጡ ዜጎችን፣ አርሶ አደሮችን፣ የእጅ ጥበብ ባለሙያዎችን፣ አባገዳዎችን፣ የሃይማኖት መሪዎችንና የሲቪክ ማህበራትን ድምፅ ከመንደር እስከ ዋና ከተማ ሰምቷል። ሴቶች፣ ወጣቶችና የአካል ጉዳተኞችም በውይይቱ ላይ የራሳቸውን ህመም፣ ፍላጎትና የመፍትሔ ሀሳብ በነፃነት አቅርበዋል።

እኒህ ዜጎች ከቀረቡት 400 አጀንዳዎች ውስጥ በ396 ያህሉ ተስማምተዋል። ይህም 99 በመቶ ማለት ነው።

የሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ስኬታማ መሆን ለመግባባት ዲሞክራሲ መረጋገጥ በርካታ ዘላቂ ድሎችን የሚያስገኝ ነው። በህዝብና በመንግስት ተቋማት መካከል የታጣውን እምነት መልሶ በመገንባት ህጋዊነትን ያጠናክራል፤ የወደፊት የህግና የስርዓት ማሻሻያዎችም የብዙኃኑን ፍላጎት ያካተቱ እንዲሆኑ መንገድ ይጠርጋል። ከሁሉም በላይ ደግሞ የግጭት መንስኤዎችን ከስራቸው በመመርመርና በመፍታት ለልማት የሚመች ዘላቂ ሰላማዊ ሁኔታ ይፈጥራል።

በጎ ፍቃድ ለማህበራዊ እረፍት ነሐሴ 24፣ 2018  ዓ.ም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሰብዓዊና ማህበራዊ ጠቀሜታው ባለፈ የተረጋጋ ማህበረሰብን ለመፍጠርና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትና እድገት እንዲኖ...
30/08/2026

በጎ ፍቃድ ለማህበራዊ እረፍት

ነሐሴ 24፣ 2018 ዓ.ም

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሰብዓዊና ማህበራዊ ጠቀሜታው ባለፈ የተረጋጋ ማህበረሰብን ለመፍጠርና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትና እድገት እንዲኖር የሚያስችል አገልግሎት ነው፡፡

አብሮነትን፣ እርስ በርስ መደጋገፍን፣ አንድነትንና መተሳሰብን የሚያጠናክር በመሆኑ በጎ ፈቃደኛ ትውልድ በመገንባት ረገድ ባለፉት ዓመታት በትኩረት ሲሰራ ቆይቷል፡፡

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በኢትዮጵያ በማህበረሰቡ ውስጥ ለረጅም ዘመናት በተለያዩ ባህላዊ የመተጋገዝ ልምዶች ሲከናወን የቆየ ነው።

ለአብነትም ዕድር፣ ዕቁብ፣ ደቦን ጨምሮ የልማት ሥራዎችና የጋራ የመረዳዳት ባህሎች የበጎ ፈቃድ መንፈስ ጠንካራ መሠረት ናቸው።

በተለይም በቅርብ ዓመታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከግለሰቦች የግል ተነሳሽነት በመሻገር የተደራጀ ሀገራዊ እንቅስቃሴ እየሆነ መጥቷል።

ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ተማሪዎች፣ የሙያ ባለሙያዎችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ዕውቀታቸውንና ሙያቸውን በመስጠት ለማህበረሰብ ችግሮች መፍትሔ ለማበርከት ተሳትፈዋል።

በቅርብ ዓመታት በጎ ፈቃደኞች በአረንጓዴ ልማት፣ በደን ልማትና በዛፍ ችግኝ ተከላ ላይ በስፋት ተሳትፈዋል።

በከተሞች የሚከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች፣ የወንዞችና የውሃ አካላት ዳርቻ ጽዳት፣ የችግኝ ተከላና እንክብካቤ የበጎ ፈቃደኞች ዋነኛ ተሳትፎ የታየባቸው ዘርፎች ናቸው።

በበጎ ፈቃድ እንቅስቃሴ ዜጎች በከተሞች የጎዳና ጽዳት፣ የቆሻሻ ማስወገድ፣ በህዝብ ቦታዎችን ማስዋብና የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች የማህበረሰብ ተሳትፎን ከማጠናከር ባለፈ ለከተሞች የኑሮ ጥራት አስተዋጽኦ አድርገዋል።

በጎ ፈቃደኞች በችግር ላይ ለሚገኙ ዜጎች ምግብ፣ ልብስና ሌሎች የመሠረታዊ ፍላጎት ድጋፎችን በማቅረብ ረድተዋል።

የደም ልገሳ በጎ ፈቃደኝነት በቀጥታ የሰው ሕይወትን ከሚያድኑ ተግባራት አንዱ ነው።

በተለያዩ አካባቢዎች በጎ ፈቃደኞች ትምህርት ቤቶችን በማደስ፣ የመማሪያ ቁሳቁሶችን በማበርከትና ተማሪዎችን በትምህርት በመደገፍ እየተሳተፉ ይገኛሉ።

ይህም የትምህርት ዕድልን ከማስፋት ባለፈ የወጣቱን ተሳትፎ በሀገራዊ ልማት ላይ እንዲጨምር አድርጓል።

በተፈጥሮ አደጋ፣ በመፈናቀል ወይም በሌሎች አስቸኳይ ሁኔታዎች ጊዜ በጎ ፈቃደኞች የምግብ፣ የልብስ፣ የመጠለያና ሌሎች ድጋፎችን በማድረስ ለተጎዱ ወገኖች እገዛ አድርገዋል።

የበጎ ፈቃድ ሥራ የተለያዩ አካባቢ፣ ብሔርና ማህበራዊ ዳራ ያላቸውን ዜጎች በአንድ ዓላማ ዙሪያ ያሰባስባል።

አንድ ሰው ለሌላው በጎ ሲያደርግ የመተማመንና የመተሳሰብ ስሜት ይጠናከራል፤ ይህም ማህበራዊ መከፋፈልን ለማስቀረትና የጋራ ሀገራዊ ስሜትን ለማጎልበት ይረዳል።

በጎ ፈቃድ ችግረኛን መርዳት ብቻ ሳይሆን የሚተማመን፣ የሚተባበር፣ ለልማት የሚሳተፍና የተረጋጋ ማህበረሰብ የመገንባት መሣሪያ ነው።

በዚህ ሂደት የሚገነባው የመተማመንና የትብብር ባህል ደግሞ ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ልማትና ለሀገራዊ እድገት ጠንካራ መሠረት ይሆናል።

በማሌ ወረዳ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬትን በማስመልከት በምርጫው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተደረገ ::ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ማሌበደቡብ ኦሞ...
29/08/2026

በማሌ ወረዳ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬትን በማስመልከት በምርጫው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተደረገ ::

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ማሌ

በደቡብ ኦሞ ዞን በምርጫው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የክልል የዞን የወረዳ የቀበሌ አመራሮች ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበረሰብ ክፍሎች እና የቀበሌ መዋቅሮች በዛሬው ዕለት በወረዳው እውቅናና ምስጋና ተበርክቶላቸዋል ::

የተሰጠው ዕውቅናም ሆነ ምስጋና ለወደፊቱ ይበልጥ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ ጠንክረን እንዲንሰራ ሞራል ሰጥቶናል ስሉ አንዳንድ ዕውቅና የተሰጣቸው አካላት ገልፀዋል ::

በማሌ ወረዳ "እኔም ለማሽነሪ ግዥ አሻራዬን አኖራለሁ" በሚል መሪ ቃል ማሽነሪዎችን ለመግዛት የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ  ::​ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ማሌ)​በደቡብ ኦሞ ዞን የማሌ ወረዳ ማ...
29/08/2026

በማሌ ወረዳ "እኔም ለማሽነሪ ግዥ አሻራዬን አኖራለሁ" በሚል መሪ ቃል ማሽነሪዎችን ለመግዛት የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ ::

​ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ማሌ)

​በደቡብ ኦሞ ዞን የማሌ ወረዳ ማህበረሰብ "እኔም ለማሽነሪ ግዥ አሻራዬን አኖራለሁ" በሚል መሪ ቃል ግሬደር እና ሎደር ማሽነሪዎችን ለመግዛት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ንቅናቄ መድረክ ተካሄደ ።

​​የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ህዝቡ ካነሳቸው ዋና ዋና የልማት ጥያቄዎች መካከል የመንገድ መሰረተ ልማት ዋነኛው በመሆኑ ይህ የማሽነሪዎች ግዥ ገንዘብ ማሰባሰብ ንቅናቄ ተዘጋጅቷል ብለዋል ።

አቶ አልጋጋ አክለውም የማሽነሪ ግዥ ኢንሸቲቩ በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ መጀመሩን ጠቅሰው፣ ህዝቡ የልማት ጠያቂ ብቻ ሳይሆን የልማቱ ንቁ ተሳታፊና ባለቤት መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።

​የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው በወረዳው የሚታየውን የመንገድ ዘርፍ ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ በማህበረሰቡ ትብብርና አቅም ማሽነሪዎችን ለመግዛት የሚያስችል ኢኒሼቲቭ መቀረጹን ገልፀዋል ::

በአጠቃላይ የ1 ግረደር እና 1 ሎደር ማሽነሪዎች ግዥ 114 ሚሊዮን ብር እንደሚፈጅ ሰነዱን ባቀረቡበት ወቅት ገልፀው በተባበረ ክንድ ማሳካት እንደሚቻል ገልፀዋል ::

​የማሽነሪ ግዥ ንቅናቄውን በይፋ ያስጀመሩት አቶ ንጋቱ ዳንሳ፤ በወረዳው ከሚነሱ የልማት ጥያቄዎች መካከል የመንገድ ችግር ጎልቶ እንደሚወጣ ጠቁመው፣ ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ማህበረሰቡ በጋራ በመቀናጀት ማሽነሪዎችን ለመግዛት የሚያስችለውን ኢኒሸቲቭ መደገፍ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።

በወረዳው ካለው የመንገድ ችግር የተነሳ ማህበረሰቡ ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየተዳረገ መሆኑን በርካታ የመድረኩ ተሳታፊዎች አንስተው ኢኒሼቲቡ በመጀመሩ መደሰታቸውን ገልፀዋል ::

ተሳታፊዎቹ አያይዘውም በዓይነት በገንዘብ ኢኒሼቲቩን ለመደገፍ በርካታ ሰዎች በመድረኩ ቃል ገብተዋል ::

በማሌ ወረዳ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬትን በማስመልከት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው ::​ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ማሌ)​ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው 7...
29/08/2026

በማሌ ወረዳ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬትን በማስመልከት የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው ::

​ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ማሌ)

​ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው 7ኛው ምርጫ በወረዳው በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ በማሌ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አዘጋጅነት የተዘጋጀው የእውቅና እና የምስጋና መርሃ ግብር በወረዳው ዋና ከተማ ሌሞ ጌንቶ በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል።

​በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪ እና የፖለቲካና ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ዳንሳ፣ የክልሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ዳርጌ ዳሼ፣ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ፣ የማሌ ወረዳ ተወላጅ የሆኑ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።

የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ እንደገለጹት፤ መርሃ ግብሩ የብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት ለማበሰርና ለህዝቡ ምስጋና ለማቅረብ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው፣ በምርጫው ወቅት ህዝቡ ያነሳቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ አስተዳደሩ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

​የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው፤ ብልፅግና ፓርቲ በወረዳው በምርጫው አብላጫ ድምፅ አግኝቶ እንዲያሸንፍ ህዝቡ ላደረገው ያልተቆጠበ ድጋፍ እና ንቁ ተሳትፎ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

አቶ ማዕከል አክለውም በምርጫው ወቅት በማህበረሰቡ የተነሱ አጣዳፊ የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝና በአሁኑ ወቅትም የሚጨበጡ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን አብራርተዋል።

​የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ እና የፖለቲካና ህዝብ ግኑኝነት ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ንጋቱ ዳንሳ ባስተላለፉት መልእክት፤ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት የተጠናቀቀበት፣ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ አሰራር የጎለበተበት እንዲሁም በርካታ በጎ ልምዶችና ትምህርቶች የተወሰዱበት አጋጣሚ እንደነበር ገልጸዋል።

​በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ በምርጫው ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት የማበርከት ስነ-ስርዓት እንደሚከናወንም ተገልጿል ።

29/08/2026
በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ምክር ቤት 1ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ካንጋተን)በደቡብ ኦሞ ዞን የኛንጋቶም ወረዳ ሽግግር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 1ኛ መደበ...
29/08/2026

በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ምክር ቤት 1ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ካንጋተን)

በደቡብ ኦሞ ዞን የኛንጋቶም ወረዳ ሽግግር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በኛንጋቶም ወረዳ ማካሄድ ጀምሯል።

ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎው በአስር አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል፦

አጀንዳ 1 6ኛ ዙር 7ኛ ዓመታዊ 4መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ለም/ቤት አባላት ይቀርባል

አጀንዳ 2 የኛ/ወ/ም/ቤት የ2018 ዓ/ም አፈፃፀም ሪፖርት ለም/ቤት አባላት ይቀርባል

አጀንዳ 3 የኛ/ወ/ም/ቤት የ2019 ዓ/ም ዕቅድ ለም/ቤት አባላት ይቀርባል

አጀንዳ 4 የኛ/ወ/አስ/ር የሴ/መ/ቤቶችየ2018 አፈፃፀም ሪፖርት ለም/ቤት አባላት ይቀርባል፣

አጀንዳ 5 የኛ/ወ/አስ/ር የሴ/መ/ቤቶች የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ለም/ቤት አባላት ይቀርባል

አጀንዳ 6 የኛ/ወ/ፍ/ቤት የ2018 12 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ለም/ቤት አባላት ይቀርባል : በቀረበዉ ሪፖርት ላይ ዉይይት

አጀንዳ 7 የኛ/ወ/ፍ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ይቀርባል፤

አጀንዳ 8 የኛ/ወ/የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ለም/ቤት አባላት ይቀርባል፤

አጀንዳ 9 ሹመት ማፅደቅ

አጀንዳ 10 ዋናአፈጉባኤናዋናአስተዳደሪ የ2018 በጀት ዓመት የግብስምምነት ይፈራረማሉ

የደቡብ ኦሞ ዞን አስተዳደር ለኮይቤ የመጀመረያ ደረጃ ሆስፒታል የአንቡላንስ ድጋፍ አደረገ :: ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ማሌየደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በማሌ ወረዳ ለ...
29/08/2026

የደቡብ ኦሞ ዞን አስተዳደር ለኮይቤ የመጀመረያ ደረጃ ሆስፒታል የአንቡላንስ ድጋፍ አደረገ ::

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም ማሌ

የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በማሌ ወረዳ ለኮይቤ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንድ አቡላንስ አበርክተዋል::

አንቡላንሱ የተገኘው ከክልሉ ጤና ቢሮ ለዞኑ የተደረገ ድጋፍ ሲሆን በሆስፒታሉ ገዝፈው ከሚታዩ ችግሮች መካከል አንዱ የአንቡላንስ እጥረት መሆኑን በመገንዘብ ዞኑ በካብኔ በማስወሰን ድጋፍ ማድረጉን አቶ ማዕከል ገልፀዋል ::

የተሰጠውን አንቡላንስ ለረዥም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ለማድረግ በጥንቃቄ መጠቀም ያስፈልጋልም ብለዋል ::

የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ በበኩላቸው ሆስፒታሉ በወረዳው በጀት በሚተዳደርበት ወቅት ከፍተኛ የሀብት እጥረት እንደነበረው አስታውሰው በዞኑ ስር እንዲተዳደር በመደረጉ ማገገሙን ተናግረዋል

አቶ አልጋጋ አክለውም ​በሆስፒታሉ የአንቡላንስ ችግር ለመቅረፍ በወረዳው ያሉ አንቡላንሶችን አዟዙረው ስጠቀሙ እንደነበር ተናግረው ዞኑ ላደረገው የአንቡላንስ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል ::

በሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አምባቸው አሰፋ በሆስፒታሉ የአንቡላንስ እጥረት በመኖሩ በወሊድ ወቅት እናቶችን ወደ ጤና ተቋማት ለማድረስ እንደሚቸገሩ ተናግረዋል ::

የተደረገው የአንቡላንስ ድጋፍ ትልቅ ችግር እንደቀረፈላቸው በመግለፅ ዞኑ እያደረገ ስላለው ድጋፍ አመስግነዋል ::

በሆስፒታሉ ማቆያ ካሉ እናቶች መካከል አንዳንዶቹ እንደገለፁት በአንቡላንስ እጥረት ምክንያት ወደ ጤና ተቋማት ለመሄድ እንደሚቸገሩ ገልፀው የተደረገው ድጋፍ እጅግ በጣም እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል ::

Address

SNNPRS-Ethiopia
Jinka

Telephone

+251903983112

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Omo Zone Government Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to South Omo Zone Government Communications:

Shortcuts

Share