የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት /Ari Zone Prosperity Party Branch Office/

  • Home
  • Ethiopia
  • Jinka
  • የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት /Ari Zone Prosperity Party Branch Office/

የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት /Ari Zone Prosperity Party Branch Office/ ይህ የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት /Ari Zone Prosperity Party Branch Office/ ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው

12/09/2026

በብሪክስ የቤተሰብ መድረክ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ከኢራኑ ፕሬዚዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ጋር ተወያይተናል።

‎ከጉባኤው ጎን ለጎን ባደረግነው ውይይት በቀይ ባሕር አካባቢ ባሉ ወቅታዊ ሁነቶች እና አጠቃላይ በቀጣናው የደኅንነት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ የውይይትን አስፈላጊነት እና የቀጣናውን መረጋጋት እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መክረናል።

Yaa'ii BRICS cinatti Haammattoo maatii 'BRICS' keessatti Pirezdaantii Iraan Masoud Pezeshkian waliin marii'anneerra.

Mariin keenyas kan xiyyeeffate haala yeroo naannawaa Galaana Diimaa jiruufi haala nageenya waliigalaa naannichaa irratti kan xiyyeeffate yoo ta'u, barbaachisummaa mariifi akkaataa tasgabbii naannawaa sanaa dhugoomsuun danda'mu irratti marii'anneerra.

Met with President Masoud Pezeshkian of Iran on the sidelines of the BRICS Summit, as part of the BRICS family.

Our discussions focused on developments in the Red Sea and the broader regional security situation, including the importance of dialogue and regional stability.

🇪🇹 🇮🇷

10/09/2026
10/09/2026
የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ  ጽ/ቤት በወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈፃፀም ዙሪያ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የብይነ ...
10/09/2026

የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈፃፀም ዙሪያ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የብይነ መረብ ምክክር እና ግምገማ ማካሄዱን አስታወቀ።

ጳጉሜ 4/2018ዓ/ም
ኣሪ ዞን/ጂንካ

በተደረገዉ ግምገማ ነክ ምክክርም አጠቃላይ በየመዋቅሩ ወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈፃፀም እና የመዋቅሮች ነባራዊ ሁኔታን በተለይም የበጎ ተግባራት እና የጳጉሜ ቀናት አከባበር ህዴቶች ከዕቅድ አንፃር ያለዉ ተፈፃሚነት
በጥልቀት ለመዳሰስ መቻሉንና ተሞክሮ ለመቀመር የተቻለበትን ዕድል የፈጠረ እንደነበረም የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት የተከበሩ አቶ ሕዝቅኤል ጋርታ ተናግረዋል ።

አክለዉም በዓመቱ የማጠቃለያ ሥራዎች የሃያ ቀናት ዕቅድ አፈፃፀም ብቻ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ ኩኔቶችን በመጠቀም እንደ ማዕድ ማጋራት፣የአልባሳትና የቁሳቁስ ድጋፍ፣የደም ሊገሳና የጽዳት ሥራዎች እንድሁም ስፖርታዊ ዉድድሮችን ጨምሮ በተደረጉ አሳታፊና አስተሳሳሪ መርሃግብሮች ተስፋ ሰጪ የሆነ ተጨባጭ ለዉጥ ለማምጣት መቻሉንና በርካታ አቅመ ደካማና አረጋውያን ተደራሽ ለማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል ።

በስተመጨረሻም የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን የክረምት ወራትን በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ወጣቱንና ሴቶችን ጨምሮ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በእኩል የሚሳተፉበት ምቹ ዕድል በመፍጠር የበጋውን ወራት ሳይቀር ዓመቱን ሙሉ ለመስራት መታቀዱንና በተለያዩ ዘርፎች በመንቀሳቀስ ያልተዳሰሱ አካላትንም በሽፋን ተደራሽ ለማድረግ አቅጣጫ መቀመጡንና ግብም መጣሉን አመላክተዋል ።

09/09/2026
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በተገኙበት ጳጉሜ 4 ቀንን "የህብር ቀን" በሚል ስያሜ በጂንካ ከተማ በአደባባይ በስፖርታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከበረ ።         ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም    ...
09/09/2026

የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በተገኙበት ጳጉሜ 4 ቀንን "የህብር ቀን" በሚል ስያሜ በጂንካ ከተማ በአደባባይ በስፖርታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከበረ ።

ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም
ኣሪ ዞን/ጂንካ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ እንደገለጹት፣ “ድር ብያብር አንበሳ ያስር” የሚሉት የአባቶች ተረክ ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ትርጉም ያለዉና የአብሮነትን ጠቀሜታ እና ሚና የሚያንፀባርቅ ከመሆኑም በላይ
የይቻላልን መንፈስ የሚያጎናጽፍ አዎንታዊ መልዕክት እንዳለዉና በየትኛውም ሁኔታ አስተሳሳሪ ትርክትን መከተል እንጂ ከፋፋይ የሆኑ ነጠላ ትርክቶች ሰለባ መሆን ሀገራዊ እሴቶቻችንን ከመበረዝ በላይ ሕብረ ብሔራዊነትን የሚሸረሽርና የሀገር ሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ፈተና ልሆን እንደሚችል አስገንዝበዋል።

በተለይም ባለፈው በኣሪ ዞን የተከሰተውን የማርበርግ በሽታ በጋራ በመስራት በአጭር ጊዜ መቆጣጠር መቻላችን የአንድነትና የትብብር አቅማችንን እና የአንድነት እንድሁም የመደማመጥንና የመከባበርን ዋጋ ከፍ ከሚያደርጉ እዉነታዎች አንዱ ማሳያ እንደሆነም ተናግረዋል።

በዚህ ሂደት ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦችን ለማጠናከር የቅን ልቦች በጎ አድራጎት ማህበር የተለያዩ አካላትን በማስተባበር ቤት መገንባቱ የህብር ቀንን እሴት የሚያሳይ ተግባራዊ ምሳሌ መሆኑንም አቶ እንዳሻው ገልጸዋል።

የታመሙትን መጠየቅ፣ የተቸገሩትን መርዳትና በችግር ጊዜ አብሮ መቆም የህብር ቀን ሰው ተኮር እሴቶችን በተግባር የሚያሳዩ ተግባራት መሆናቸውንም አክለዋል።

የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አብረሃም አታ በበኩላቸው፣ ሁሉም ዜጋ ሀገራዊ አንድነትን ልያጠናከር በሚችል ጤናማ መስተጋብር ልጋመድ እንደሚገባና በበሕብር በዓላማ ፅናት በመቆም የታፈረችና የተከበረች ሉዓላዊት ሀገርን ለትዉልድ ለማቆዬት በሚዛናዊ የእይታ መርህ ላይ ልቆም እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።

“ ከጥንትም ጀምሮ የሰለጠኑ ኃያላን የነበሩ ወራሪ ጠላቶችን በዓለም አደባባይ በማንበርከክና ድል በመንሳት የመላዉ ጥቁር ሕዝብ ኩራትና የነፃነት ተምሳሌት የሆነች ሀገር ማፅናት የተቻለዉም በተለመደዉ ኢትዮጵያዊ የአይበገረነት መንፈስ መሆኑን ገልፀዉ አንድነት የዛሬዉ ትዉልድም ቋንቋና መገለጫ ልሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።


በተጨማሪም አንድነት የሠላምና እና የልማት መሠረት መሆኑን በመግለፅ እንደ ሀገር እምርታዊ ዕድገት ለማምጣትም ቀዳሚዉን ስፍራ እንደሚይዝም ጠቁመዋል ።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ውባለም ገዛህኝ በበኩላቸው፣ የህብር ቀንን ስናከብር ሁላችንም እርስ በርስ በመጠያየቅ፣ በመተሳሰብና አብሮነታችንን በማጠናከር ቀኑን ልዩ ትርጉም ባለው መልኩ ማክበር እንደሚገባ ገልጸዋል።

በዕለቱ የደም ልገሳና ነፃ የምርመራ አገልግሎት ተሰጥቷል። በወንዶችና በሴቶች የተካሄደው የ5 ኪ.ሜ ሩጫም ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለወጡ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያ ሽልማት ሥነ-ሥርዓት ተከናውኗል።

በቀጣይም የማዕድ ማጋራት፣ አቅመ ደካማዎችን መርዳት እንዲሁም የእግር ኳስ የፍጻሜ ጨዋታ በጂንካ ሁለገብ ስታዲየም የሚካሄዱ ይሆናል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አመራርና ባለሙያዎች፣ የኣሪ ዞን አመራርና ሠራተኞች፣ የጂንካ ከተማ አመራርና ሠራተኞች፣ የጸጥታ አካላት እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

የኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ በአዲሱ  የትምህርት አመራር መረጣና ምልመላ መሠረት ለተመዘገቡ ዕጩ የትምህርት አመራር በሚዜናዉ ሕገ ደንብ ዙሪያ ኦሬንቴሽን ሰጠ።ጳጉሜ 4/2013ዓ/ም     ኣሪ...
09/09/2026

የኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ በአዲሱ የትምህርት አመራር መረጣና ምልመላ መሠረት ለተመዘገቡ ዕጩ የትምህርት አመራር በሚዜናዉ ሕገ ደንብ ዙሪያ ኦሬንቴሽን ሰጠ።

ጳጉሜ 4/2013ዓ/ም
ኣሪ ዞን/ጂንካ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ከፍተኛ ባለሙያ እና በጂንካ ማዕከል የሚሰጠዉ የትምህርት አመራር ሚዜና ደጋፊ የሆኑት የተከበሩ አቶ ናታን ላቢሶ እንደተናገሩት የትምህርት አመራሮች በአቅምና በአመለካከት ጥራት የነጠሩ ልሆኑ እንደሚገባ ገልፀዉ በቀጣይም ትዉልድን የማሻገርና የሀገርን ህሊዉና እየተፈታተነ የሚገኘዉን የትምህርት ስብራት ችግር በዘላቂነት የመፍታት ሀገራዊ ጥሪ የቀረበላቸዉ ተተኪዎች መሆናቸዉን በማስገንዘብ ለሁሉም ተፈታኞች መልካም ምኞታቸዉንም ገልጸዋል ።

በመድረኩም የኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት የተከበሩ አቶ እልፊዮስ ባድሜ እንደተናገሩት እንደሀገር ላለፉት በርካታ ዓመታት ለሀገር ህሊዉና አደጋ የነበረዉን የትምህርት ስብራት ፈተና ታርክ ለማድረግ እና ከሥር መሠረቱ ለማጥራት የተጀመረ ሀገራዊ ንቅናቄ ምዕራፍ ከፋች ሂዴት የትምህርት አመራርን ማጠናከር መሆኑን ከግምት በማስገባት የተጀመረ ተግባር መሆኑን በመገንዘብ ለትውልድ ቀረጻ አደራ የተጣለበት ተረኛ ባለአደራነታቸዉን ልዘነጉ እንደማይገባም አስገንዝበዋል ።

አክለዉም በዚህ ዓመት የመጀመሪያውን የትምህርት አመራር ሚዜና ብቻ ኣሪ ዞንና ደቡብ ኦሞ ዞንን ጨምሮ በጂንካ ዩኒቨርስቲ እና በጂንካ ፖሊ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ከ 300 በላይ ዕጩ የትምህርት አመራሮች እንደሚታደሙ ጠቁመዉ ፈተናዉም በበይነ መረብ በኦን ላይን እንደሚሰጥም ገልፀዋል።

Address

South Omo
Jinka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት /Ari Zone Prosperity Party Branch Office/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share