03/09/2026
የበና ፀማይ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ለጤና ጣቢያ ኃላፊዎች የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ተጠሪዎች እና የጽ/ቤት ባለሙያዎች የወረዳ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች ላይ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተገለፀ
✅ነሐሴ፦28/2018 ዓ.ም (በፀወመኮአ)
ቀይ አፈር
========================
✍️ስልጠናውም በወረዳው ጤና ጽ/ቤት ለጤና ጣቢያ ኃላፊዎች ፣ የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ተጠሪዎች እና የጽ/ቤት ባለሙያዎች የወረዳ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች ስልጠና እንዲሁም ወቅታዊ የወባና ስርዓተ ምግብ አለመመጣጠን ክስተት አስተዳደር ውይይት እየተደረገ መሆኑን ተገለፀ።
✍️ስልጠናውም በዘርፉ የወረዳ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች እና በቀጣዮ በ2019 ዓ.ም የትኩረት አቅጣጫዎች በወረዳው ውስጥ ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ከAMREF እና JSI MIHR የ4ኛ ሩብ አመት ግብረ መልስ እና የወባና የምግብ እጥረት ልየታና ህክምናን አጠናክሮ ከመስራት አኳያ ያለውን ወቅታዊ ሂደቶች ላይ ያተኩራል ተብሏል ።
✍️ይኸውም ስልጠና የደቡብ ኦሞ ዞን ጤና መምሪያ ባለሙያ በሆኑት በአቶ አልዲ ኦይታ እና ዋሲሁን ጌታሁን በጋራ በመሆን ለተከታታይ ለሁለት ቀናት እንደምሰጥ ተገልጿል።
✍️በወረዳ ደርጃ ተግባራት በብቃትና በስፋት ማስፈፀምና መፈፀም እንዲቻል በማህበረሰቡ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ከማድርግ ኢፍትሃዊነት እና ጥራት ባለው መልኩ ለማህበረሰቡ ከማዳረስ አኳያ ጠንከር ያለ አቅጣጫ ከመሆኑ አንጻር ከጤና ጣቢያ አንስቶ እስከ ጤና ኬላ ደረጃ በቼክሊስት መሰረት በትኩረት እንደሚሰራና ግብረ መልስ ተጠናክሮ የሚቀርብ መሆኑን ጭምር የበና ፀማይ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሴ ኦይታ አሳውቀዋል ።
👉የመረጃ ምንጭ የበና ፀማይ ጤ/ጽ/ቤት ነው