06/09/2026
የቆቦ ከተማ አስተዳደር "የእመርታ ቀን" በመስክ ጉብኝት በደመቀ ሁኔታ አከበረ።
ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም (ቆቦ ኮሙኒኬሽን ) የቆቦ ከተማ አስተዳደር "የኢትዮጵያ መንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የተሰናዳውን "የእመርታ ቀን" በግብርና ልማት ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት የተካሄደውን የመስክ ጉብኝት ጨምሮ በታላቅ ድምቀት አክብሯል።
የቀኑን መከበር ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው በዚህ የመስክ ምልከታ ላይ የከተማውና የየቀበሌው ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች፣ የፀጥታ አመራርና አባላት ፣የግብርና ባለሙያዎች እንዲሁም ከሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ነዋሪዎችና ጎብኝዎች በጋራ ተሳትፈዋል።
በጉብኝቱ ወቅት በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች፣ የወቅቱ ሰብል ልማት እንቅስቃሴዎችና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮች የተጎበኙ ሲሆን፣ በተለይም በግብርናው ዘርፍ የሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረገው ሀገራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ጎልቶ ታይቷል።
ዘመናዊ የምርት ማሳደጊያ ዘዴዎችን በመጠቀም፣ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት እና የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቶበታል።
ተሳታፊዎች በበኩላቸው በመስክ ያዩት የምርታማነት እድገትና የልማት እንቅስቃሴ በምግብ ራስን ለመቻል የተያዘውን ግብ ለማሳካት ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም ለአካባቢው አጠቃላይ እድገትና ለወደፊት እመርታ የበኩላቸውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።