Kombolcha City Administration Department Of Revenue

Kombolcha City Administration Department Of Revenue This pages Kombolcha City Administration Department Of Revenue official page

ስለ QR ደረሰኝ ማለት?
25/05/2026

ስለ QR ደረሰኝ ማለት?

22/05/2026
የአውት ሶርስ ገቢ ከሚሰበሰቡ የወጣት ማህበራቶች ጋር ምክክር ተደረገ።የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የአውትሶርስ ማለትም የገቢ ተቋሙ ተደራሽ በማያደርግባቸው የገቢ አርዕስቶች ላ...
21/05/2026

የአውት ሶርስ ገቢ ከሚሰበሰቡ የወጣት ማህበራቶች ጋር ምክክር ተደረገ።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የአውትሶርስ ማለትም የገቢ ተቋሙ ተደራሽ በማያደርግባቸው የገቢ አርዕስቶች ላይ ከሚሰበሰቡ የወጣት ማህበራቶች ጋር በባለፋት ወራቶች የተከናወኑ ተግባራትና ባጋጠማቸው ተግዳሮቶች ዙረያ እንዱሁም ሙያዊ ስነ-ምግባርን ተላብሶ አገልግሎት ከመስጠት አኳያ ማህበራቶቹ ሪፓርት አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል ።
በውይይቱ የተሳተፉት ማህበራቶች የተለያዩ ጥያቄና አስተያየቶችን ያነሱ ሲሆን በሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል ።
የመምሪያው ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም አሊ ውይይቱን የመሩት ሲሆን መልካም ስነ-ምግባር በመላበስ የተሰጣችሁን ሃላፊነት በታማኝነት እና ፍትሐዊነት ላይ መሠረት በማድረግ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል ።
ግንቦት 13/2018 ዓ.ምየግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዋና የስራ ሂደት
የኮምቦልቻ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች መምሪያ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ላይክ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!
በፌስቡክ https://www.facebook.com/kombolcha.revenue1
በቴሌግራም https://t.me/komblcharevenue

በወቅታዊ  የገቢ ስራዎች እና በባለፉት አስር ወራት የስራ አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት ተደረገ።የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከአራቱ ክፍለ ከተማ ገቢ ጽ/ቤቶች የማኔጅመንት አባላት ...
20/05/2026

በወቅታዊ የገቢ ስራዎች እና በባለፉት አስር ወራት የስራ አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት ተደረገ።
የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ከአራቱ ክፍለ ከተማ ገቢ ጽ/ቤቶች የማኔጅመንት አባላት ጋር በወቅታዊ የገቢ ስራዎች እና በባለፉት አስር ወራት የስራ አፈፃፀም ላይ ውይይት አድርጓል ።

የክልሉ ደጋፊ ቡድን አባላት አቶ አግማስ ጫኔ እና አቶ አበባው አለበል በውይይቱ የተገኙ ሰሆን ሁሉም ክፍለ ከተሞች በአስር ወሩ ያከናወኗቸውን ተግባራትን ሪፖርት አቅርበው ምክክር ተደርጓል ። በዚህም የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና የነበሩ ክፍተቶችን በመለየት በተገቢው ሁኔታ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል ።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ ሙሀመድ ሰይድ በቀጣይ በአንደኛ እና ሁለተኛ ሩብ አመት ግብራቸውን ያልከፈሉ ግብር ከፋዮችን ማስከፈል ፣ ትክክለኛ የሊዝ መረጃ በመለየት ማስከፈል ፣ ውዝፍ ያለባቸውን ግብር ከፋዮች እንድከፍሉ ማድረግ በአጠቃላይ የኛን ጥረት የሚጠይቅ ሌሎች የገቢ ምንጮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል ።

ግንቦት 12/2018 ዓ.ምየግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዋና የስራ ሂደት
የኮምቦልቻ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች መምሪያ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ላይክ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!
በፌስቡክ https://www.facebook.com/kombolcha.revenue1
በቴሌግራም https://t.me/komblcharevenue

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በመገኘት ድጋፍ አደረገ።የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ታክስ አማካሪ አቶ አግማስ ጫኔ እና የታክስ  መረጃ  አስተዳደር ቡድን መሪ...
19/05/2026

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በመገኘት ድጋፍ አደረገ።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ታክስ አማካሪ አቶ አግማስ ጫኔ እና የታክስ መረጃ አስተዳደር ቡድን መሪ አቶ አበባው አለበል
ከመምሪያው የማኔጅመንት አባላት ጋር በቸክሊስት የተደገፈ በአስር ወሩ የተከናወኑ ተግባራት ላይ ውይይት አካሂዷል ።
መምሪያው በባለፉት አስር ወራት ከመደበኛና አገልግሎት ገቢ 1, 901, 731, 537 ብር ወይም የእቅዱን 80.29 በመቶ ገቢ መሰብሰብ ችሏል።
የክልሉ ደጋፊ ቡድን አባላት የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በቀሪ ወራቶች የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ በመግለፅ የጋራ ሀሳብ በመያዝ ውይይቱ ተጠናቋል።

ግንቦት 11/2018 ዓ.ምየግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዋና የስራ ሂደት
የኮምቦልቻ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች መምሪያ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ላይክ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!
በፌስቡክ https://www.facebook.com/kombolcha.revenue1
በቴሌግራም https://t.me/komblcharevenue

19/05/2026
ማስታወቂያ ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘራችሁ የደረጃ" ሀ" ግብር ከፋዮች የQR  ደረሰኝ ታትሞ የመጣላችሁ በመሆኑ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ቢሮ ቁጥር 104 እየመጣችሁ መ...
14/05/2026

ማስታወቂያ
ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘራችሁ የደረጃ" ሀ" ግብር ከፋዮች የQR ደረሰኝ ታትሞ የመጣላችሁ በመሆኑ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ቢሮ ቁጥር 104 እየመጣችሁ መውሰድ እንደምትችሉ እንገልጻለን።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ
ግንቦት 6/2018 ዓ.ም

14/05/2026
መምሪያው  የ3ኛ ሩብ አመት አፈፃፀም ገመገመ።የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ3ኛ ሩብ አመት አፈጻጸም ከመምሪያ ጠቅላላ ሰራተኞችና ከክፍለ ከተማ ገቢ ጽ/ቤቶች የማኔጅመንት አባ...
29/04/2026

መምሪያው የ3ኛ ሩብ አመት አፈፃፀም ገመገመ።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ3ኛ ሩብ አመት አፈጻጸም ከመምሪያ ጠቅላላ ሰራተኞችና ከክፍለ ከተማ ገቢ ጽ/ቤቶች የማኔጅመንት አባላት ጋር ገምግሟል ።

በዚህም በዘጠኝ ወሩ የተከናወኑ የቁልፍና አበይት ተግባራት በዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል ።
መምሪያ በበጀት አመቱ ከመደበኛ እና አገልግሎት ገቢ 2, 368, 605, 434 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ በባለፉት ዘጠኝ ወራት ከመደበኛ እና አገልግሎት ገቢ 1,702, 665, 519 ብር መሰብሰብ መቻሉን ተገልጿል ።
በተጨማሪም 1463 ግብር ከፋዮች የግብር/ታክስ ቅሬታ ያቀረቡ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ምላሽ መስጠት መቻሉን ተመላክቷል።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ ሙሀመድ ሰይድ በባለፉት ዘጠኝ ወራት የተሻለ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተናግረው ግምገማው የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል እና የነበሩ ክፍተቶችን በመለየት አሁን ላይ ካለው የበለጠ ስራ ለመስራት ያግዛል ብለዋል። ስለሆነም በቀጣይ ትክክለኛ የመረጃ ማጥራት ስራ በመስረት በሮያሊቲና ጫት ገቢ እንዱሁም ውዝፍ ያለባቸውን ግብር ከፋዮች ትኩረት ሰጥቶ የማስከፈልና ህግ የማስከበር ስራ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

የመምሪያው ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም አሊ በበኩላቸው ከመምሪያ እስከ ክፍለ ከተማ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር መልካም ስነምግባርን ተላብሶ አገልግሎት በመስጠት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ መትጋት ይገባል ብለዋል።
በመጨረሻም በሩብ አመቱ የተሻለ አፈፃፀም ለነበራቸው ባለሙያዎች የምስክር ወረቀት በማበርከት ውይይቱ ተጠናቋል ።

ሚያዚያ 21/2018 ዓ.ም
የግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዋና የስራ ሂደት
የኮምቦልቻ ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች መምሪያ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ላይክ እና ሸር በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!
በፌስቡክ https://www.facebook.com/kombolcha.revenue1
በቴሌግራም https://t.me/komblcharevenue

Address

Administration Building
Kembolcha

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251930026582

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kombolcha City Administration Department Of Revenue posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share